2023-06-04 16:50:25
ከአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተሰጠ አጭር መግለጫ
ውድ የማህበራችን አባላትና ደጋፊዎችቻን ማህበራችን የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ማህበር ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የማህበረሰባችን ባህል፣ ቋንቋና እሴት በማስተዋወቅ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ጠፍቶ የነበረው አዳብና በፌስቲቫል ደረጃ በማስጀመርና ማህበራዊ ሚዲያና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ላይ በማስተዋወቅ፣ ወጣቱ ባህሉ እንዲጠብቅና በባህሉ እንዲኮራ በማንቃትና በማደራጀት ፣ዪምር ዪምር፣ እንዞሪቴንና ሌሎች እሴቶቻችን በቴሌቪዥን ጣቢያና በማህበራዊ ሚዲያ በማስተዋወቅ ትላልቅ ስኬቶችና ለውጦችን አስመዝግበናል።
ማህበሩ በአሁን ሰዓትም አዳብና ፌስቲቫል ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ቀርፆ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።
ነገር ግን ውድ የማህበራችን አባላትና ደጋፊዎች ማህበራችን ያቀዳቸው ፕሮጀክቶችን በሙሉ አቅሙ ለማስፈፀምና ተግባር ላይ ለማዋል የገንዘብ አቅም ውስንነት አለበት።በመሆኑም ባህላችን የማሳደግ የሁሉም ተወላጅ ኃላፊነትና ድርሻ ስለሆነ በአጠቃላይ የጉራጌ ተወላጆች በተለይ የክስታኔ ተወላጆች የማህበሩ አባል በመሆንና በማገዝ አብረን ባህላችን እንድናሳድግ ጥሪ እናቀርባለን።
የማህበራችን ነባር አባል የሆናቹ የ2015ዓ.ም ዓመታዊ የአባልነት መዋጮ በማህበሩ ሂሳብ ቁጥር በማስገባት ስሊፕ ለማህበሩ አስተባባሪዎች እንድትልኩና አባልነታቹ እንድታድሱ ይሁን።
መታወቂያ ያሎሰዳቹ የማህበሩ ፅ/ቤት ወይም አቅራቢያቹ ባለ አስተባባሪ በኩል እንድትወስዱ እናመቻቻለን።
እስከ ሴኔ 30 ዓመታዊ የአባልነት መዋጮ የማይከፍል የማህበሩ አባል በማህበሩ ህገ ደንብ መሰረት ከአባልነቱ የሚሰረዝ ይሆናል።
አሜሪካና ፣አውሮፓና አረብ ሀገራት ያላቹ ተወላጆች የማህበሩ አባሎ በመሆን ከጎናችን እንድትሆኑና የድርሻቹን እንድታበረክቱ ጥሪ እናቀርባለን።
ባለሀብቶች ማህበሩን በገንዘብና በቁሳቁስ በማገዝ አሻራቹን አኑሩ
የሀገር ሽማግሌዎች ምሁራን ምክርና አቅጣጫ በማሳየት አግዙን።
የአባልነት መዋጮ ለመክፈልና ማህበሩን ማገዝ ለምትፈልጉ
የማህበራችን ባንክ አካውንት
1000397603141
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
127SAV3403
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ
የአዳብና በክስታኔ ዓለም አቀፍ ወጣቶች
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ
ግንቦት 27/2015
ለበለጠ መረጃ
0916298674
0910186703
404 views13:50