Get Mystery Box with random crypto!

أبو سعيد

የቴሌግራም ቻናል አርማ abuseidibnuhussen — أبو سعيد أ
የቴሌግራም ቻናል አርማ abuseidibnuhussen — أبو سعيد
የሰርጥ አድራሻ: @abuseidibnuhussen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 320
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ቁርኣን እና ሐዲሥን እንዲሁም የደጋግ ቀደምቶችን ፈለግ መሰረት ባደረገ በፅሁፍ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ይቀርብበታል።
📝አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-26 06:07:11 ~ዘካቱል ፊጥር~~~
ክፍል ሁለት
① ዘካቱል ፊጥር ምን ያህል ገንዘብ ያለው ሰው ላይ ነው ግዴታ የሚሆነው???
ዘካቱል ፊጥር እንደ ዘካተል ማል ግዴታ የሚሆንበት የሀብት መጠን አልተቀመጠለትም ይልቁንም ዘካቱል ፊጥር ግዴታ የሚሆነው ለራሱና ወጪያቸውን ለሚሸፍንላቸው ሰዎች የኢዱን ለሊትና ቀን መሰረታዊ ፍላጎቶችን አሟልቶ የተረፈ እህል ወይ ገንዘብ ባለው ሰው ላይ ሁሉ ነው።
②ዘካቱል ፊጥር ከምን አይነት እህል ነው የሚሰጠው?????
ዘካተል ፊጥር ከምን አይነት እህል ነው የሚሰጠው የሚለውን አስመልክቶ በኢስላም ሊቃውንቶች መካከል ከአንድ በላይ አቋም የተንፀባረቀ ቢሆንም የተሻለው አቋም ሰውዬው ባለበት አካባቢ ሰዎች እንደ ቀለብነት የሚጠቀሙትን የእህል አይነት ማውጣት ይችላል የሚለው አቋም ነው።ስለዚህ አካባቢያችን ላይ ሰዎች በስፋት እንደቀለብ የሚጠቀሙትን የአህል አይነት ማውጣት እንችላለን ማለት ነው።
③ለዘካተል ፊጥር የምናወጣው የእህል መጠን ምን ያህል ነው?????
ለዘካተል ፊጥር የምናወጣው የእህል መጠን ምን ያህል ነው የሚለውን አስመልክቶ" ክፍል አንድ " ላይ እንዳየነው በኢብኑ ዑመር ሐዲስ ላይ በግልፅ ተቀምጧል።ስለዚህ በሐዲሱ መሰረት የምናወጣው የእህል መጠን አንድ ቁና ይሆናል ማለት ነው።ይሁን እንጂ ይህ መስፈሪያ(ቁና) አብዛሃኛው አካባቢያችን ላይ ስሙን ከመስማት በዘለለ በሰፊው አገልግሎት ላይ የሚውል የመስፈሪያ አይነት አለመሆኑ፤እንዲሁም ሐዲሱ ላይ የተፈለገው የመልዕተኛው ﷺቁና መሆኑ ነገሩን አወዛጋቢ ያደርገዋል።ነገር ግን ዑለሞች ይህን ውዝግብ ለመቅረፍና ነገሩን ቀለል ለማድረግ ሲሉ ኪታቦቻቸው ላይ ወደ ኪሎ ግራም ቀይረው አስቀምጠውት እናገኛለን።ከነዚህም ዑለሞች መካከል ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ሷሊሕ አልዑሰይሚን( ዓለይሂ ረሕመቱሏህ) ይገኙበታል፤ይህንን አጥንተው አንድ የመልችክተኛው ﷺቁና ወደ ኪሎ ግራም ሲቀየር 2 ኪ.ግ ከ 40 ግራም እንደሆነ ይናገራሉ።ይህም የሆነው ጥሩ የሚባለውን የስንዴ አይነት ተጠቅመው እንደሆነም ይገልፃሉ።ይህ የዑለሞች ልፋት አወዛገቢ የነበረውን ነገር ቀለል ያደረገልን ቢሆንም አሁንም የተወሰነ አሻሚ ነገር ቀርቷል።"ምንድነው ደሞ የቀረው አሻሚ ነገር!!?? " ከተባለ ፤ እንደሚታወቀው ሁሉም የእህል አይነት ከ ቁና ወደ ኪሎ ግራም ሲቀየር 2 ኪ.ግ ከ 40 ግራም ይመጣል ማለት አይደለም።ምክንያቱም ሁሉም እህል እኩል የሆነ ክብደት የላቸውም።እናም ይህንንም ለመቅረፍ የተወሰኑ የእህል አይነቶችን ከቁና ወደ ኪ.ግ ቀይረው ኪታቦቻቸው ላይ ያሰፈሩ ዑለሞቻችንም አልጠፉም( አሏህ መልካም ምንዳቸውን ይክፈላቸውና)።ስለዚህ አቅማችን የሚፈቅድ ከሆነ ከዚህ ሁሉ ድካም ለመትረፍ እና ለሚስኪኖችም ከማዘን አኳያ የምናወጣውን የእህል መጠን 3 ኪ.ግ ብናደርገው እኛም እር፞ፍ ሚስኪኖችም ጥግ፞ብ ይላሉ።ግዴታ ከሆነብን በላይ ሆኖ የተረፈውን ተጨማሪ ሶደቃ ነይተን እንሰጥ።
④ ዘካቱል ፊጥር የተደነገገበት ሚስጥር( ጥበብ) ምንድነው??????
ዘካቱል ፊጥር የተደነገገበት ጥበብ በግልፅ ሐዲስ ላይ ተቀምጦ እናገኘዋለን።ይህም:—
عن ابن عباس" فرض رسول الله زكاة الفطر طهرة للصائم من اللغو والرفث وطعمة للمساكن" (رواه أبو داود وبن ماجاه)
" የአሏህ መልዕክተኛ ﷺለፆመኞች ከውዳቂ ንግግሮችና ተግባራት የሚጠሩበት፤ ለሚስኪኖች ደሞ ምግብ ይሆን ዘንድ ዘካተል ፊጥርን ግዴታ አድርገዋል"( አቡዳውድ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል)
በሐዲሱ መሰረት ዘካቱል ፊጥር የተደነገገው ለነዚህ ሁለት የተቀደሱ አላማዎች ነው ማለት ነው።ስለዚህ ፆመኛ ሆነን ሳለ ለፈፀምናቸው ጉድለቶች ማበሻ ነውና ዘካተል ፊጥራችን በአግባቡ እናውጣ።
~ ወሏሁ ኣዕለም~~~
ኢንሻአሏህ ይቀጥላል
184 viewsأبو سعيد, 03:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 09:57:05 ~ ዘካቱል ፊጥር ~
ክፍል አንድ
ዘካቱል ፊጥር የረመዷን ፆም በሚጠናቀቅበት ወቅት ግዴታ የሚሆን የዘካ አይነት ነው።ዘካቱል ፊጥር ሙስሊም በሆነ ባሪያም ይሁን ነፃ፣ወንድም ይሁን ሴት፣ህፃንም ይሁን ትልቅ ላይ ግዴታ ተደርጓል።ይህን አስመልክቶ እንዲህ የሚል ሐዲስ ተዘግቦ እናገኛለን: —
عن ابن عمر قال" فرض رسول الله ﷺ زكاة الفطر صاع من تمر أو صاع من شعير على العبد والحر،والذكر والأنثى، والصغير والكبير،من المسلمين" (متفق عليه)

" መልዕተኛው ﷺ ዘካተል ፊጥርን ከተምር ወይም ከገብስ አንድ ቁና ከሙስሊሞች በባሪያውም በነፃውም፣ በወንዱም በሴቱም፣በትንሹም በትልቁም ላይ ግዴታ አድርገዋል" ( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
በሐዲሱ ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው ዘካቱል ፊጥር በሚከተሉት ሰዎች ላይ ግዴታ ይሆናል:—
① ባሪያዎች እና ነፃ የሆኑ ሰዎች ላይ
ባሪያ ከሆነ እራሱ የሚያንቀሳቅሰው ገንዘብ ስለማይኖረው ዘካውን የማውጣት ግዴታ በሐላፊው ላይ ይሆናል።ባሪያ ያልሆነ ሰው ደሞ ከራሱ ገንዘብ ዘካውን የሚያወጣ ይሆናል።
②ወንድ እና ሴት
ዘካቱል ፊጥር ፆታ የሚለይበት ኢባዳ አይደለምና በሴቱም በወንዱም ላይ ግዴታ ይሆናል።ሴት ልጅ ብር ካላት ለራሷ ታወጣለች ከሌላት ደግሞ ልጅ ስትሆን በወላጆቿ፣ ሚስት ስትሆን ደሞ በበሏ ላይ ግዴታ ይሆናል።
③ሕፃናት እና ትላልቅ ሰዎች
ዘካቱል ፊጥር እድሜም የማይገድበው በትንሹም በትልቁም ላይ ግዴታ የሆነ ትልቅ ኢባዳ ነው።ሕፃናት ገንዘብ ካላቸው ከራሳቸው ገንዘብ ዘካውን እናወጣላቸዋለን፤ ከሌላቸው ደሞ የነሱን ሌሎች መሰረታዊ ወጪዎችን የመሸፈን ሐላፊነት ያለበት ሰው ( ለምሳሌ: ወላጆች) ላይ ይሆናል ግዴታው።ለሕፃናት ዘካቱል ፊጥርን ማውጣት ግዴታ ሲሆን ለተፀነስ ልጅ ዘካውን ማውጣት ግን ግዴታ ሳይሆን የተወደደ ተግባር ነው።ይህም ተግባር( ለፅንስ ዘካተል ፊጥርን ማውጣት) ከኸሊፋው ዑስማን ቢን ዐፋን ተገኝቷል።

ማሳሰቢያ
✘ በአሁኑ ጊዜ ያሉ በደሞዝ ተስማምተው የሚሰሩ የቤት ሰራተኞች ባሪያ የሚለው ውስጥ የሚካተቱ አይደሉምና ለነሱ ዘካ የማውጣት ግዴታ አሰሪያቸው ላይ የለበትም።ዘካውን እራሳቸው ከደሞዛቸው ማውጣት ይኖርባቸዋል።አሰሪው ግን በራሱ ፍቃደኝነት ቢያወጣላቸው ምንም ከልካይ ነገር የለም።
✘ ለፅንስ ዘካ ለማውጣት ፅንሱ 120 ቀን ወይም አራት ወር የሞላው መሆን አለበት ምክንያቱም ከአራት ወር በፊት ሩሕ ስለማይነፋበት እንደ ሰው አይቆጠርምና።
✘ ዘካቱል ፊጥርን ለማውጣት ሰውዬው ወሩን ፆመኛ ሆኖ ያሳለፈ መሆን አለበት አይባልም።ለምሳሌ አንዲት ሴት በወሊድ ደም ምክንያት ወሩን ሙሉ መፆም ባትችል፤ በሕመምም ይሁን በሌላ ሸሪዓዊ ዑዝር ያልፆሙ ሰዎች ዘካቱል ፊጥር ግዴታ የለባቸውም አይባልም።ይልቁንም ከሌላው ሰው ( ወሩን ፆመኛ ሆነው ካሳለፉት ) እኩል ዘካቱል ፊጥርን የማውጣት ግዴታ ይኖርባቸዋል።
✘ እራሳቸውን ችለው የሚኖሩ ልጆች ዘካውን የማውጣት ግዴታ እራሳቸው ላይ እንጂ ወላጆቻቸው ላይ አይደለም።

ወሏሁ ኣዕለም ~~~
ኢንሻአሏህ ይቀጥላል
189 viewsأبو سعيد, 06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 10:50:08 ትኩረት ለፈጅር ሰሏት
~~
የብዙዎቻችን ረመዷን ላይ ያለን ጥረት የሚመሰገን ነው። የተራዊሕ ሰላት እንሰግዳለን፤ የመጨረሻው አስርት ሌሊቶች ላይ ተሓጁድንም እንጨምራለን… ما شاء الله ነገር ግን ከዚህ ሁሉ ጥንካሬያችን ጋር ሱብሒ ሰላት ሲደርስ ብርታታችን የሚከዳን ቀላል አይደለንም። እውነት የሌሊት ሰሏቶች ላይ ስንሽቀዳደም የነበረው ለአሏህ ብለን ነው?? ወይስ ሰው ያደረገው እኔንም አይለፈኝ ብለን??… እውነት ለአሏህ ብለን ከነበረ ሱና ላይ በርትተን ግዴታው ላይ አንዘናጋም! ስለዚህ ተሓጁድን ትተን ፈጅር መስገድ ይሻለናል ሳይሆን ሁለቱንም መስገድ ይሻለናል እላለሁ። ሁለቱንም መስገድ ጭራሽ የማንችል ከሆነ ግን ግድ የለም ተሓጁዱን ትተን ፈጅሩን መስገድ የተወደደ ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው። ምክንያቱም "ግዴታዎችን ከመወጣት በላይ ወደ አሏህ የሚያቃርብ የተሻለ መልካም ነገር የለም" ብሏል ጌታችን አሏህ በሐዲሥ አልቁድሲይ። ፈጅር ሰሏት መስገድ ግዴታ ሲሆን ተራዊሕ ወይም ተሓጁድ ሰሏት መስገድ ግን የተወደደ ሱና ነው። በመሆኑም ትኩረት ለፈጅር ሰሏት

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
343 viewsأبو سعيد, edited  07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-21 20:46:33 ☞ የረመዷን መጨረሻ አስርት ሌሊቶች ይለያሉ!
~~
የተከበራችሁ ፆመኛ ወንድምና እህቶች ሆይ! የረመዷን ድፍን ሀያ ቀናት ከመቅፅበት ተሰናበትናቸው። የተጠቀመባቸው አሏህን ያመስግን፤ የተሳነፈባቸው ነፍሱን እንጂ ማንንም እንዳይወቅስ። ይልቅ እነዚህን አስርት ሌሊቶች ቀበቶዋችንን ጠበቅ በማድረግ እንነሳ፤ አጨራረሱን እናሳምር፤ ለይለተል ቀድርን እንጠባበቅ፤ የሌሊት ሰሏት ላይ እንበርታ፤ የቁርኣን ፕሮግራማችን እናሻሽል፤ የእንቅልፍ ጊዜያችን እንቀንስ፤ የዱንያ እርፍትን ሳንሰዋ የአኼራውን ዘልዓለማዊ እረፍት ማግኘት ይቸግረናል፤ "መልእክተኛው ﷺ እነዚህን አስርት ሌሊቶች ህያው ያደርጓቸው ነበር" ብለን ከማውራት አልፈን ተግባራዊ እናድርገው።
አሏህ የተግባር ሰው ያድርገን! ለይለተል ቀድርንም ይወፍቀን!

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
256 viewsأبو سعيد, edited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 00:31:09 በፅሁፍ ተጀምሮ የነበረው "ረመዷንና ቁርኣን" የተሰኘው ርእስ በዚህ ድምፅ መቋጨቱ ታሳቢ ይደረግ!
343 viewsأبو سعيد, edited  21:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 00:27:56 ቁርኣንን በማንበብ ከፍተኛ አጅር እንደሚገኝ ማወቅ ብቻ በቂ አይደለም። በተግባር ማሳየት ተገቢ ይሆናል! ይህንን የተመለከተ አጭር ማስታወሻ #ከወንድም_አቡ_ሰዒድ!

የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
የዚህ ግሩፕ ዓላማ ቂርኣትና ዳዕዋ እንዲሁም አንዳንድ መልዕቶች ለማስተላለፍ ነው
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
319 viewsأبو سعيد, 21:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-06 00:01:53 የፆም ኣዳቦች ክፍል ሁለት
በወንድም ሙሐመድ ኸይሩ

የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
የዚህ ግሩፕ ዓላማ ቂርኣትና ዳዕዋ እንዲሁም አንዳንድ መልዕቶች ለማስተላለፍ ነው
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
321 viewsأبو سعيد, 21:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-06 00:01:41 የፆም ኣዳቦች ክፍል አንድ
በወንድም ሙሐመድ ኸይሩ

የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
የዚህ ግሩፕ ዓላማ ቂርኣትና ዳዕዋ እንዲሁም አንዳንድ መልዕቶች ለማስተላለፍ ነው
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
268 viewsأبو سعيد, 21:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 17:02:55 «የቀደምት አበዎች ሁኔታ በረመዳን»
ከረመዷን ለመጠቀም ይህንን ሙሓደራ እንዲከታተሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን!
በወንድም አቡ ሰዒድ


የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
የዚህ ግሩፕ ዓላማ ቂርኣትና ዳዕዋ እንዲሁም አንዳንድ መልዕቶች ለማስተላለፍ ነው
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
273 viewsأبو سعيد, 14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 19:43:03
የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
የዚህ ግሩፕ ዓላማ ቂርኣትና ዳዕዋ እንዲሁም አንዳንድ መልዕቶች ለማስተላለፍ ነው
https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group
249 viewsأبو سعيد, 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ