Get Mystery Box with random crypto!

አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ abune_abib — አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
የቴሌግራም ቻናል አርማ abune_abib — አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
የሰርጥ አድራሻ: @abune_abib
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 123
የሰርጥ መግለጫ

❤ ክርስቶስ ሆይ ሕይወቴን ላንተ ❤

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-18 09:15:21 #የምወደው_ልጄ_ይህ_ነው!!

በጥምቀት በዓል በታላቅ ፍቅር ሲያመሰግኑ በነበሩት ወጣቶች አንጻር የሚከተለው #ተግሳጽ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወጣ- "የምወደው ልጄ ይህ ነው!"
<< የምወደው ልጄ ይህ ነው! ባንተስ ደስ የምለኝ መቼ ነው?? >>
( በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ)

በእርግጥ ያንተን ያህል የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ መውጣት አይችልም፤ ኦሪት ዘፍጥረት የቱ ጋር እንደሆነ, ዜና መዋእልም የት እንደሚገኝ አያውቅም። ምናልባት ከራእይ ዮሐንስ ሀይለ ቃል ለማንበብ መዝ.ዳዊት ላይ ገልጦ ይዳክር ይሆናል፤ ምንም ምስጥር አያውቅም፤ ለአንድምታው,ለትርጓመውም እንግዳ ይሆናል፤ መላእክት ጻድቃን ሰማዕታትን አይለይም።

ጊዮርጊስ ሰማዕቱን ከመላእክት አንዱ አድርጎ ያስበዋል፤ ለየትኛውም ሃይማኖታዊ ጥያቄ መልስ መስጠት አይችልም፤ ዛሬም የእርሱ ጥያቄ ዓሣ ፆም አለው ወይስ የለውም ? የምል ልሆን ይችላል፤ በማህሌት እና በሰዓታት በቅዳሴና በወረብ መካከል ያለው ልዩነት አይገባውም! ለእርሱ በቤ/ክን ውስጥ የሚሰማ ዜማ ሁሉ ቅዳሴ ነው፤ ስለ ስርዓተ ቤ/ክን ምንም አያውቅም በእርሱ አስተሳሰብ በፆም ቀን ፀበል መጠጣት ፆሙን አያፈርስም፤ የምያማትበውም አንተ በምታውቀውና በምታብራራው ሥርዓት ሳይሆን እጅን በማወዛወዝ ልሆን ይችላል፤ የሰንበት ት/ቤትን ተከታታይ ት/ት አልተማረም ፤ በጉባኤ አባልነትም አልተመዘገበም፤ በየትኛውም ምድብ አያገለግልም፤ ከየተኛው መንፈሳዊ ት/ቤት አልተመረቀም፤ ይሁንና የምወደው ልጄ ይህ ነው።

የሚዘምረው መዝሙርም ሥርዓተ ቤ/ክን ያልጠበቀ ነው፤ ሽብሸባውም እንዲሁ፤ አለባበሱም ብዙ ጉድለት አለበት፤ ነጠላውን እንደዋዛ ይጠመጥመዋል እንጅ በትምህርተ መስቀል አያደርግም፤ አረማመዱም የምንፈሳዊ ሰው አይደለም ፀጉሩን የተንጨባረረ እና የተጠቀለለ ነው፤ የምውልበት ሥፍራ መልካም ላይሆን ይችላል፤ በሰው ሁሉ የተጠላ የተተፋ፤ ይሁን ግን ልንገርህ -የምወደው ልጄ ይህ ነው።

አናንያ ሆይ < የሳኦልን ክፉ አትንገረኝ ፤ የእርሱን የቀደመ ጭካኔውንና በሰው ዘንድ ያለውን ክፉ ስም አትንገረኝ፤ ጌታ ሆይ መጥፎ ነው >እያልክ አትወትውተኝ ሁሉንም አውቀዋለሁ፤ ነገር ግን ካንተ ይልቅ የሚሰማኝ የምፈራኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው።

አንተ በቤቴ ኖረህ ሳትሰማኝ ቃሌንና ትእዛዜን ተለማምደህ ቸል ብለህ ስትኖር፣ የተናገርኩትን ትእዛዝ ቸል ሳይል የምፈፅም የእኔ ምርጥ እቃ- የምወደው ልጄ ይህ ነው።
አንተ የለመድከውን አንተ የተዳፈርከውን መቅደሴን በሩቅ እያየ የምፈራ የምንቀጠቅጥ ሳነሳው የምነሳ ሳስቀምጠው የምቀመጥ ምርጥ እቃዬ -የምወደው ልጄ ይህ ነው።

እርግጥ ነው ዜማ አያውቅም እኔን ግን ያውቀኛል፤ ምንም ጥቅስ አልያዘም ትህትናን ግን ይዙዋል፤ የቅዳሴን ተሰጦ አይመልስም እኔ ስጠራው ግን ይመልስልኛል: እኔ ግን ይፈራኛል: ስለ ስሜ ስተጋ አይታክትም፤ ስለ ክብሬ ሲንከራተት አልተማረረም፤ ያንተን ቸልተኛውን ትእዛዝና ተገሳፅ በትህትና ተቀበለ እንጅ እኔን አክብሮ አከበረህ እንጅ ለታቦት ማለፍያ መንገድ ስደለድል፤ ቆሻሻ ሲዝቅ አፈር ሲሸከም ካንተ ያገኘውን ጥቅስ በየመንገዱ ሲሰቅል ድንጋይ ሲሸከም በፊቱ ላይ ደስታን እንጅ አንዳች ምሬት አላየሁበትም። ስሜታዊ ሆኖ ነው: ስላልበሰለ ነው አትበለኝ የቤቴ ቅናት የምትበላው ለእኔ የታመነ የምወደው ልጄ ይህ ነው።

ስሜታዊ መሆንስ እንዳንተ ማንቀላፋት ነው፤ መብሰልስ ቸልተኝነት ነው ስምኦን ሆይ ስለሱ አንዳች ክፉ አትንገረኝ ኃጥአተኛ ነው እንድህ አድርጓል አትበለኝ አንተ ያልሠራሀውን አልሠራም እኔ ያየሁትን ክፋቱን አይደለም፤ በንስሐ በትህትና ማጎንበሱን ነው። ለክብሩ ሳይሳሳ በእንባ እግሮቼን አጥቧል ምንጣፍ አንጥፎ ሳር ጎዝጉዞ በአደባባይ ከፊቴ ስደፋ ያን ጊዜ ነው የልጄን ልብ ያየሁት:: ስለሱ አንዳች ክፉ አትንገረኝ - የምወደው ልጄ ይህ ነው።

አንተ መዘመር ሰልችቶሃል ፤ ማጨብጨብም ደክሞሃል፤ እርሱ ግን ስያመሰግን ብውል ብያድር አይጠግብም። ምናልባት ጀማሪ ስለሆነ ነው ትል ይሆናል፤ አንተ ፈፃሚ ስለሆንክ ነው የተሰላቸህው? አንተ መዝሙር ምታጠናው ከበሮ ለመምታት ብቻ ይሆናል ፤እርሱ ግን በባዶ እጁ በማመስገኑ ደስተኛ ነው። አንተ እንዴት እንደምሸበሸብ እያወክ ታበላሸዋለህ ፤ እርሱ ግን ላገኘው ሁሉ እንዲህ ነው የሚሸበሸበው እያለ ይጨነቃል፤ ልክ ነህ ጀማሪ ነው፥ ስሜታዊ ነው፤ ያልበሰለ ነው ፤ ነገር ግን የምወደው ልጄ ይህ ነው። ባንተ ደስ አልተሰኘሁም፤ በተማርኸው መጠን አልኖርክም በዘራሀው መጠን አላፈራህም፤ ስለ ቅናቱ በእርሱ ደስ የምለኝ - የምወደው ልጄ ይህ ነው። ባንተስ ደስ የምለኝ መቼ ነው????????????

ይህን የእግዚአብሔር ተግሳጽ ከመቀበል ጋር አንድ መልእክት ይቀራል:: እነዚህ ወጣቶች ቀድሞም በቃለ እግዚአብሔር ተኮትኩቶው አላደጉም:: ምንም በጥሩ ምግባር ባይታወቁም በልባቸው ግን እንደ እሳት የሚንቀለቀል ሃይማኖት አላቸው:: ፈሪሃ እግዚአብሔር አላቸው::

እኛ ወደ እነርሱ ባንሄድ እነሱ ግን ወደኛ መጥተዋል:: ሌላ ምን እንላለን:: ነብዩ <መንፈሱ ሰብስባቸዋልና ከነዚህ አንድ አትጠፋም > እንዳለ ያለ ቀሽቃሽ የሰበሰባቸው የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲጠብቃቸው እንዲያጸናቸው እንመኛለን:: በጎች ኑረው በረት ጠበባ አይባልምና ቤተ ክርስቲያንም መዋቅሯን አጠናክራ እንደምትቀበላቸው ተስፋ እናደርጋለን::

ለወጣቶቹ ግን < ምንነው ለጥምቀት ብቻ > ከሚል ምክር ጋር አንድ ቃለ ሐዋርያ እንጥቀስ::
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለም። " ዕብራውያን 6፥10

ወጣት ሆይ! አንብበህ ስታበቃ ተገሳፁ ላንተ እንደሆነ አስተውል!! "እኛስ ለታቦት ሥራ አለብን" ብለው እራሳቸውን ዝቅ ያደረጉ ወንድሞችህ "የምወደው ልጄ ይህ ነው" ተብለዋል። አንተም ከእነርሱ ተማርና የምወደው ልጄ አንተ ነህ ለመባል ያብቃህ!

#ጸሐፊ :- ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የምወደው ልጄ ይህነው !

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
•➢ ሼር // SHARE

•✥• @ABUNE_ABIB •✥•
•✥• @ABUNE_ABIB •✥•
•✥• @ABUNE_ABIB •✥•


@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
56 viewsB Belete , 06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-18 09:11:13 ከተራ ማለት ምን ማለት ነው | ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ

#ከተራ ማለት “ከተረ” ከበበ ዙሪያውን ያዘ ካለው ከግዕዝ
ቃል የተገኘ ነው፡፡ከተራ ማለት ከበባ እጀባ ማለት ነው፡፡
ይኸውም ታቦተ ሕጉ በጳጳሳት፣ በሊቃውንት፣ በቀሳውስት፣
በዲያቆናት እንዲሁም በምእመናን ተከቦ ታጅቦ መጓዙን
የሚያመለክት ገላጭ ቃል ነው፡፡

፪ኛ ከተራ ማለት ከተረ ሰበሰበ ዐጠረ ማለት ሲሆን
ይኸውም ወራጁን ውኃ ሰብስበው ወይም ገድበው
በየሰበካው ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ ወይም
በድንኳን የሚያድሩበት የተለያዩ የውኃ አካላት ተጠርገው
ሚከተሩበት ስለሆነ ነው፡፡ ይህም ስፍራ ‹‹ባሕረ
ጥምቀት›› ወይም ‹‹የታቦት ማደሪያ›› እየተባለ ይጠራል፡፡
ውኃ መሰብሰቢያ ምቋመ ማይ ማለት ነው፡፡

የከተራ በዓል ጥንት ከነገሥታቱ ጀምሮ የሀገር መሪዎች
በቀዳሚነት ተሰልፈው የሚያከብሩት ብሔራዊ በዓል
ከመሆኑ የተነሣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ የአከባበር ሥነ
ሥርዓት አለው፡፡ ይኸውም ባህላዊው ከሃይማኖታዊው
ሥርዓት በመነሣት የሚከናወን ሆኖ ማህበረ ሰቡ ደስታውን
ፍቅባሕላዊ ሚገልጥበት የአለባበስ የአጨዋወት ሥርዓት
አለው፡፡

*_ባሕላዊ አከባበሩ_*
እዩት እዩት ሲያምር
የበአታ ደብር።
እንኳን ለታቦት ለደጉ ጌታ
ይጨበጨባል ለጋለሞታ፡፡
ሁሉም ያምረኛል በመር በመሩ፤
እነ መምሬ ቅኔ ሲመሩ፡፡
በሕይወት ግባ በሕይወት፤ የአገሬ ታቦት፡፡
ሲያምር ዋለ ሲያምር፤ የሀገራችንደብር፡፡
እየው ወሮአት ሲገባ፤ ጌታ ባለአበባ፡፡
አለው አለው አበባ፤ የአገሬ ታቦት ሲገባ፡፡
ርግቤ በቀሚሱ ላይ፤ ርግቤ በካባው ላይ፤
የሰላም ምልክት ይዛ ልትታይ፡፡
ልብሱ አረፈረፈ ልብሱ አረፈረፈ፤
ርግብ በራሱ ላይ ዐረፈ፡፡ እያሉ የደብራቸውን ታቦት
ያመሰግናሉ።
በዚህ መልኩ ታቦቱን በልዩ ልዩ ቃላት ያሞግሳል፡፡
ሴቶችም እንደዚሁ በበኩላቸው ከወላጆቻቸው ሲዋረስ
በመጣው መሠረት ነጫጭ የሀገር ልብሳቸውን ለብሰው
ከዋክብት መስለው መቀነታቸውን በወገባቸው ሸብ አርገው
የታቦት ዜማ ያሰማሉ፡፡

*_ሃይማኖታዊ አከባበሩ_ ፡፡*

ጥር ፲ ቀን ከቀኑ በአራት ሰዓት በመላው አጥቢያ አብያተ
ክርስቲያናት ዋዜማ ይቆማል፡፡ ከሰዓት በኋላ ታቦታቱ
በተለያየ ሕብር በተሸለሙ የክህነት አልባሳት በደመቁ
ካህናትና የመጾር መስቀል በያዙ ዲያቆናት ከብረው፣
ከአብያተ ክርስቲያናት ወደ አብሕርተ ምጥማቃት ለመሄድ
ሲነሡ መላው አብያተ ክርስቲያናት የደወል ድምፅ
ያሰማሉ፡፡ ምእመናን ከልጅ እስከ ዐዋቂ በነቂስ ወጥተው
በአጸደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች
ይሰባሰባሉ፡፡

*_መንፈሳዊ ምሥጢሩ_*

ቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ አክብሮ ወደ ወንዝ መውረድ
በብሉይ ኪዳን የነበረ ሥርዓት ነው፡፡ ይኸውም ኢያሱ
በሙሴ ተተክቶ ሕዝበ እስኤልን ሲመራ ታቦቱን አሸክሞ
ሲሔድና ከዮርዳስ ወንዝ ሲደርስ ወራጁም ይቆም
እንደነበረ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል፡፡ እስራኤል ወደ
ምድረ ርስት ሲገቡ ታላቁን የዮርዳስ ወንዝ ሲሻገሩ
ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳን ታቦት ድንኳን ውስጥ
አድርገው ሌዋውያኑ ዙሪያውን ካህናቱ በውስጥ ሆነው
እግዚአብሔን እያመሰገኑ እንደተሻገሩ ዛሬም እንደ
ዮርዳኖስ ከጉስቁልና ወደ ብልጽግና ከደዌ ወደ ጤና
አላሻግር ያለን ባሕረ ኀጢአት በቃል ኪዳኑ አማካኝነት
በጥምቀቱ በረከት ያደርቅልናል ስንል ነው፡፡ ኢያሱ ፩፥፲፫ ፣ ኢያሱ ፫፥፰
አንድም ሐዋርያው ፊሊጶስ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባውን
ሊያጠምቀው ወደ ወንዝ የመውረዱ ምሳሌ ነው፡፡ (ሐዋሥራ ፰፥፴፬)

ዋናው ምስጢሩ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስን
አስከትሎ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ
ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፤ ታቦቱን ተሸክሞ የሚሄደው ካህን
የቅዱስ ዮሐንስ፣ ባሕረ ጥምቀቱ የዮርዳኖስ፣ ታቦታቱን
አጅበው የሚሄዱት ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ
የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች ምሳሌዎች
ናቸው፡፡
ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው በዚያው ማደራቸው
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ
ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ከማታው ጀምሮ
መውረዱንና ተሰልፎ ተራውን ሲጠብቅ ማደሩን
ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጥምቀት የሞቱ የመቃብሩ አምሳል ነው፡፡
ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያ ዘንድ
የዝናም፣ የበረዶ ወራት ነው፤ እንኳንስ ከወንዝ ዳር
ከማናቸውም ቦታ ቢሆን ያለ መጠለያ መዋልና ማደር
አይቻልም፤ በመሆኑም ከዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ
ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ድንኳናቸውን ተክለው ያርፉ
ነበር፡፡ በዚህ አንጻር ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙሪያ
በድንኳኖች የተከለሉ ዳሶች ይጣላሉ፡፡
ስለዚህ ከጥንት ጀምሮ የቃል ኪኑን ታቦት ይዘን ወደ ወንዝ
ወርደን በዓለ ጥምቀትን የምናከብረው ከዚህ ታሪክ
በመነሣት ነው፡፡

በዚህ ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ
ክርስቲያን በየዓመቱ ጥር ፲ ቀን ተቀራራቢ የሆኑትን
ታቦታትን በየአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ወንዝ በአንድነት
እያወረደች ከከተራ ዕለት ጀምሮ የጥምቀትን በዓል በታላቅ
መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታከብራለች፡፡ ሌሉቱን ከሚያነጋው
ሕዝበ ክርስቲያን ጋር በመሆን የማኅሌትና የወንጌል ጉባኤ
ተዘርግቶ በመምህራን ወቅታዊ ትምህርት ሲሰጥ ይታደራል
ይዋላል፡፡

*መልካም የጥምቀት በዓል ለመላው ህዝበ ክርስቲያን ይሁን!*

@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
48 viewsB Belete , 06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-14 21:51:47
45 viewsB Belete , 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-24 08:48:27 ​​​​ጾመገሀድ
በየኔታ ዘለዓለም ሐዲስ

ከዘጠኙ ዓበይት የጌታ በዓላት ሁለቱ የልደትና የጥምቀት በዓላት ተጠቃሾች ናቸው በሁለቱ በዓላት ቀን ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በኀዘን ማሳለፍ እንደሌለበት ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ ምክንያቱም የክርስቶስ ልደትና ጥምቀት የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደባቸው የድኅነታችን መሠረት የተጣለባቸው ዐበይት በዓላት ስለሆኑ ነው።

እነዚህ በዓላት በረቡዕና በዓርብ ቀን ከዋሉ አስቀድመን በዋዜማው ለውጥ አድርገን እንጾማቸዋለን ልደት ረቡዕ ከሆነ ማግሰኞ በዋዜማው፣ ዓርብ ከሆነ ሐሙስ በዋዜማው እስከምሽቱ አንድ ሰዓት (13 ሰዓት) እንጾማቸዋለን በሌሎችም ቀናት በዋዜማቸው በየዓመቱ ይጾማሉ ቀናቱ ሁለት ቢሆኑም ቁጥራቸው ግን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተብለው ነው የሚቆጠሩት፡፡

ገሀድ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት ገሀድና ጋድ፡፡ #ገሀድ ማለት መገለጥ መታየት መታወቅ ማለት ነው ተገለጠ ታየ ታወቀ የተባለውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ምንም ከዚያ በፊት አምላክነቱ የተገለጠባቸው ብዙ መንገዶችና ተአምራት ቢኖሩም አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው በማለት፣ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በመቀመጥ የክርስቶስ አምላክነት የተገለጠበት ዕለት ስለሆነ ገሀድ መገለጥ ተብሎ ተሰይሟል።

በሌላም በኩል #ጋድ ማለት ለውጥ ማለት ነው ልደትና ጥምቀት ረቡዕና ዓርብ ሲሆኑ ለውጥ ሁኖ የሚጾምበት ማለት ነው ስለዚህ ገሀድ ስንል የክርስቶስን አምላክነት በዕለተ ጥምቀት መገለጥ፣ ጋድ ስንል ደግሞ ለዓርብና ለረቡዕ ጾም ለውጥ ሁኖ የተጾመውን ጾም ማለታችን ነው፡፡ ይህንን ጾም ጥር 10 ቀን የሚነበበው ስንክሳር እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡፡

ወበእንተዝ አዘዙነ አበዊነ ከመ ይደሉ ንጹም እሎንተ ክልኤተ ዕለታተ ዘእምቅድመ በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት እስመ እላ ዕለታት ህየንቴሆሙ ለረቡዕ ወዓርብ ሶበ ይከውን ላዕሌሆሙ በዓለ ልደት ወጥምቀት ወበዝንቱ ይትፌጸም ለነ ክልኤቱ ግብር ግብረ ጾም ወግብረ በዓል ወከመዝ ሥሩዕ ውስተ አብያተ ክርስቲያኖሙ ለግብፃውያን ወለእመ ኮነ ዕለተ በይረሙን ዘውእቱ አስተርእዮ በዕለተ እሑድ አው በዕለተ ሰንበተ አይሑድ ይጹሙ በዕለተ ዐርብ እምቅድሜሁ እስከ ምሴት በከመ ተናገርነ ቅድመ ወለእመ ኮነ በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት በዕለተ ሰኑይ ኢይትከሀል ከመ ይጹሙ በዕለተ ሰንበት ዳዕሙ ይትዐቀቡ እምነ በሊዕ ጥሉላተ፡፡

ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው በይረሙን (መገለጥ፣ ገሀድ) በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥር ቀን ነው በዋዜማው ዓርብ እስከምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ በማለት ይገልጸዋል፡፡

ከላይ እንዳየነው ጥምቀት ወይም ልደት እሑድና ቅዳሜ ከዋሉ ጾሙ መጀመር ያለበት ዓርብ መሆኑን ተመልክተናል ይህንም መነሻ በማድረግ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት ሰኞ ሲሆን ዓርብ እስከ አንድ ሰዓት፣ ቅዳሜ እስከ ስድስት፣ እሑድ እስከ ቅዳሴ መውጫ እስከ ሦስት በመቁጠር የጾሙን ሰዓት 13 ሰዓት ያደርጉታል ይህም ከላይ የተገለጠውን ስንክሳር መነሻ በማድረግ የመሚናገሩት ስለሆነ አክብረን እንቀበለዋለን ቅዳሜ እስከ ስድስት ለመጾሙም ሃይ ምዕ 20 ተጠቃሽ ነው።

በሌላ በኩልም ጋድ አንድ ቀን ነው ሰኞ ሲሆን እሑድን ብቻ ከጥሉላት እንከለከላለን እንጅ ቅዳሜን አይጨምርም በማለት ይህን የሚቃወሙ አሉ ስንክሳር የተናገረውን ምን እናድርገው ተብለው ሲጠየቁም ስንክሳር የታሪክ እንጅ የሥርዓት መጽሐፍ አይደለም የሚል መልስ ነው የሚሰጡት፡፡

ይህ ጥያቄ ወደሌሎች ሊቃውንት ሲቀርብ የሚሰጡት መልስ ደግሞ ስንክሳር ታሪክ ብቻ ሳይሆን ሥርዓትም የተካተተበት መጽሐፍ መሆኑን ይናገራሉ በእርግጥ ስንክሳር ማለት እስትጉቡእ ስብስብ ማለት ስለሆነ ሥርዓተ ቤተ ክርስተቲያንን ከሠሩ አበው ታሪክ የተሰበሰበ መሆኑን መዘንጋት የለብንም ከላይም እንዳየነው ወበእንተዝ አዘዙነ አበዊነ ስለዚህ አባቶቻችን አዘዙን በማለት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጻፉ አበው አዘዙን አለ እንጅ ስንክሳርን የጻፉ ሰዎች የራሳቸውን ሐሳብ ያንጸባረቁበት አይደለም ስንክሳርም ቢሆን ምንም ቁጥሩ ከአዋልድ መጻሕፍት ቢሆን የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ነውና ጥምቀትና ልደት ሰኞ ከሆኑ ቅዳሜና እሑድን ከጥሉላት ተከልክለን ቅዳሜንም እስከ ስድስት ሰዓት ጹመን የአበውን ትዕዛዝ ማክበር አለብን፡፡

በሌላም በኩል ጋድ አንድ ነው እሱም የጥምቀት ዋዜማ ብቻ ነው የልደት ዋዜማ የለውም የሚሉም አሉ እንዲህ ለሚሉት መልሱ አጭር ነው ጾመ ነቢያት ስንት ነው የሚል ጥያቄ ማንሣት ነው እንደሚታወቀው ጾመ ነቢያትን ስንጾም ቀናቱ አርባ አራት ናቸው 40 ጾመ ነቢያት፣ 3ቱ የፊልጶስ ደቀ መዛሙርት የጾሙትና አብርሐም ሦርያዊ ተራራ ያፈለሰበት ጾም፣ አንዱ ጾመ ገሀድ ነው ስለዚህ በበዓለ ልደት ዋዜማ የምንጾመው ገሀድ መሆኑን ሁሉም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡

ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በተግሳፁ አንዳስቀመጠው "ስለ ፆም ክርክር በተነሳ ጊዜ ሁሌም ቢሆን ለፆም አድሉ "

"" መልሱ እንዲህ ከምስክር መምህራን ሲሆን ይሻላል፡፡ እኛ ከምንናገረው፡፡

የኔታ ዘለዓለም ሐዲስ ማለት የክቡር ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ምክትልና የ፬ቱ መጻሕፍተ ትርጓሜ መምህር ናቸው፡፡ (እንዲያው የኔ ብጤ የፌስቡክ አርበኛ እንዳይመስሉህ ብዬ ነው!)

DN YORDANOS ABEBE

ዝክረ ቅዱሳን ጉባኤ

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

#ሼር
@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
@ABUNE_ABIB
63 viewsB Belete , 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-13 08:35:41
ለገጠር ቤተክርስቲያን መርጃ ይሆን ዘንድ የተለገሰው ቲሸርት በመግዛት አገልግሎቱን ይደግፉ!

ቅዱስ ቂርቆስ ሰንበት ትምህርት ቤት ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ያገኛሉ ዋጋው 200 ብር ብቻ ነው (ጨርቆስ)።

ለበለጠ +251927707000 ይደውሉልኝ በቴሌግራም አድራሻ @BeGood16 ላይ ማናገር ይችላሉ።

በተጨማሪም ቲሸርቱን ለማግኝት
አዲስ አበባ +251927707000
ወላይታ +251910005860
አዳማ +251964356337

እግዚአብሔር ይስጥልን ሼር በማድረግ ይተባበሩ! እዚህ ላይ ይቀላቀሉ

https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet
54 viewsB Belete , 05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ