Get Mystery Box with random crypto!

ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) የሚባል በዓል በኢስላም አለን???? ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) በኢስላም | Sunnah Media Zone 」【SMZ】

ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) የሚባል በዓል በኢስላም አለን????

ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) በኢስላም
(በቁርአንና በሐዲስ) እይታ

فإن الله شرع للمسلمين عيدين عيد الفطر وعيد الأضحى.

《አላህ በኢስላም ውስጥ ሁለት አመታዊ በዓልንና አንድ ሳምንታዊ በዓልን ብቻ ነው የደነገገው። ለዚህም ማስረጃው…

ودليل ذلك ما رواه أبو داود في سننه عن أنس رضي الله عنه قال قدم رسول الله صلى الله عليه وسلم المدينة ولهم يومان يلعبون فيهما فقال: "ما هذان اليومان؟ قالوا: كنا نلعب فيهما في الجاهلية فقال يا رسول إن الله قد أبدلكم بهما خيراً منهما يوم الأضحى ويوم الفطر "
رواه أبوا داود.

《ነብዩ ﷺ ወደ መዲና በተሰደዱበት ወቅት የመዲና ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው በመጨፈር የሚያከብሯቸው ሁለት አመታዊ በዓላት(ዒዶች) ነበሯቸው።
ነብዩﷺ እነዚህ ሁለት የምታከብሯቸው ቀናት ምንድናቸው ብለው ሲጠይቋቸው የመዲና ነዋሪዎችም ከድንቁርና(ከጃሂሊያ) ዘመን ጀምሮ እናከብራቸው ነበር አሏቸው ነብዩም ﷺ አላህ እነዚህን ሁለት አመት_በዓሎችን በተሻለ ሌላ ሁለት አመት_በዓላት(ኢዶች) ቀይሮላቹሀል እነሱም ዒደል ፊጥርና ዒደል አድሐ ናቸው። ብለዋቸዋል።》
አቡዳውድ ዘግበውታል።

ከዚህ የምንረዳው በኢስላም ውስጥ የተደነገጉ አመታዊ በዓላት ሁለት ብቻ እንደሆኑና እነሱም ዒደልፊጥርና ዒደል አድሐ ብቻ እንደሆኑ ነው።

ሳምንታዊው ዓመት_በዓል ደግሞ አንድ ብቻ ሲሆን እሱም የጁምዓ እለት ነው።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ግን በቁርአንም ሆነ በትክክለኛ(በሰሒህ) ሐዲስ ያልተደነገጉ ኢ_ኢስላማዊ በዓላት ሲከበሩ ይስተዋላል።

ከእነዚህ በኢስላም ካልተደነገጉ በዓላት መካከል መውሊድ፣ሸዋል ፍችና ዐሹራ ናቸው።

እነዚህ ሶስቱ በዓላት መውሊድ፣ሸዋል ፍችና ዐሹራ በቁርአንና በትክክለኛ ሐዲስ(በሰሒህ) ያልተነገጉ ነገር ግን ሰዎች ስሜታቸውን በመከተል የፈበረኳቸው የአላህ ሳይሆኑ የሰዎች በዐላት ናቸው።

ይህ ማለት መውሊድ፣ዐሹራ እና ሸዋል ፍች ኢስላማዊ በዐላት ሳይሆኑ ኢ_ኢስላማዊ በዐላትና ኢስላም ውስጥ ከሚተገበሩ ከቢዳዓ ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

እስኪ ነብዩ ﷺ ኹጥባ ሲያነቡ ሁሌም ሳያነቡ ማያልፏትን ዐረፍተ ነገርን እናስታውስ…

وشر الامور محدثاتها وكل محدثة بدعة وكل بدعة ضلالة وكل ضلالة في النار》

《በዲን ውስጥ የነገራቶች ሁሉ መጥፎ(ሸር) ተግባር ማለት ከመሰረቱ በዲን ያልነበረና ወደ በወኋላ አዲስ የሚፈጠር መጤ ነገር ነው፣ አዲስ ነገር ሁሉ ደግሞ መጤ(ሰርጎ ገብ) ነው፣ በዲን ውስጥ ከጅምሩ ያልነበረ አዲስ መጤ ተግባር ደግሞ ጥመት ነው፣ እያንዳንዱ የጥመት ተግባር ደግሞ የእሳት ድርሻ ነው(ለእሳት የሚያበቃ ነው》ብለዋል።

መውሊድ፣ዓሹራና ሸዋል ፍች በቁርአንና በትክክለኛ ሐዲስ እስካልተደነገገ ድረስ ማንም አለ ብሎ ይናገር ማን ንግግሩ ውድቅ(ረድ) ሊደረግ ግድ ነው።

عن أم المؤمنين عائشة رضي الله عنها قالت : قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد ) رواه البخاري ومسلم ،

《ዓኢሻህ አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና ባስተላለፈችው ሐዲስ ነብዩ ﷺ《በዚህ ዲናችን ውስጥ ከጅምሩ ያልነበረን ነገር ያስገኘ ሰው ያ ያስገኘው ነገር ሊስተባበል(ረድ) ሊደረግ የሚገባ ነው።》ብለዋል።

ኢማሙ ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

وفي رواية لمسلم : ( من عمل عملاً ليس عليه أمرنا فهو رد ) .

《በሌላ የነብዩ ﷺ ንግግር《አንድ ሰው የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ነገር በዲን ውስጥ ከተገበረ ይህ ተግባሩ ሊስተባበል(ውድቅ) ሊደረግ የሚገባ ተግባር ነው።》 ብለዋል።

ሙስሊም ዘግበውታል።

ነገ በአብዛሀኛው ባህልን ዲን አድርገው በሚገነዘቡና ዲንን በባህላዊ መንገድ በዘልማድ በሚያራምዱ የህብረተሰባችን ክፍል ዘንድ የሚከበረው የሸዋል ፍች በዲን ስም ከሚከበሩ ሰው ሰራሽ አመት_ በዓሎች(ዒዶች) መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ይህንን የቢዳዓ በዓልን የሚያከብሩ ሰዎች ከዲን የሚፃረር ባህላዊ እምነት እያከበሩ መሆናቸውን በሚገባ ሊያውቁ ይገባል።

ማንኛውም ከዲን ተፃራሪ አስተምህሮትና ተግባር ደግሞ በኢስላም ውስጥ አፍራሽ አመለካከት ነው።

በመሆኑም በቁርአንና በትክክለኛ የነብዩ ﷺ ሐዲስ የተደነገገውን ብቻ በመከተልና በመተግበር እንዲሁም በቁርአንና በትክክለኛ(በሰሒህ) በነብዩ ﷺ ሐዲስ ያልተደነገገን ነገር በሙሉ በመፀየፍና በመራቅ የትክክለኛው የኢስላም አስተምህሮት የሱና(የሰለፊያህ) ተከታይና አራማጅ መሆን የእያንዳንዱ ሙስሊም የነፍስ ወከፍ ግዴታ ነወ።

አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 27/08/2014ዓ ል

ሸዋል 05/10/1443 ዓ ሂ

http://telegram.me/abuibrahim0102030405