Get Mystery Box with random crypto!

Abune Gorgorios

የቴሌግራም ቻናል አርማ abugs — Abune Gorgorios A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abugs — Abune Gorgorios
የሰርጥ አድራሻ: @abugs
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.93K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-03-09 12:28:55
3.6K viewsEsdros ICT, 09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-09 12:28:55 መምህራኑ በእግር ኳስ ውድርር አሸነፉ
*****
የአቡነ ጎርጎርዮስ አዋሬ ቅርንጫፍ ትምህር ቤት መምህራን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ጋር ባደረጉት የእግር ኳስ ጨዋታ ውድድር ለፍጻሜ በመድረስ የዋንጫ አሸናፊ ሆኑ፡፡
በውድድሩ የቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ መምህራን ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ለፍጻሜ ውድድር በማለፍ ከብሔረ ፅጌ ትምህርት ቤት ጋር ባደረጉት የዋንጫ ጨዋታ 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል፡፡
ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ በትምህርቱ ዘርፍ እያሳየ ከሚገኘው አመርቂ ውጤት ጎን ለጎን በማህበረዊ ተሳትፎም ውጤታማ በመሆን በተሳተፈበት ውድድር አሸናፊ መሆን መቻሉ ለትምህርት ዘርፉ መነቃቃትን ፈጥሯል፡፡
በክፍለ ከተማው በየአመቱ በሚዘጋጁ ስፖርታዊ ውድድሮች ላይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ ሁልግዜ ተሳታፊ እንደሚሆን የገለጹት የመጀመሪያ ደረጃ ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ ደረጄ በቀለ ሲሆኑ መምህራኑ በውድድሩ አሸናፊ በመሆናቸው ከፍተኛ ተነሳሽነትን በትምህርት ቤቱ መፍጠር ችሏል ያሉ ሲሆን የአንድነት መንፈስን መፍጠሩ በቀጣይ አብሮ በመስራት የመማር ማስተማር ሂደቱን ለመደገፍ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
መምህራኑ በውድድር ሜዳው በአጠቃላይ እንቅስቃሴ እና በሰፊ ጎል ብልጫ አሸናፊ በመሆን ዋንጫውን ከወረዳው የስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ ተርክበዋል፡፡
3.4K viewsEsdros ICT, 09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-08 18:44:43
2.9K viewsEsdros ICT, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-08 18:44:43 የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ለወላጆች ሥልጠና ሰጠ
*************
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ባሕር ዳር ቅርንጫፍ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በሙሉዓለም የባሕል ማዕከል የወላጆች፣ ተማሪዎች እና መምህራን ትስስር በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ለወላጆች ሥልጠና ሰጠ፡፡
ሥልጠናው በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የፊት ለፊት ሥልጠና ዘርፍ ባለሙያ በሆኑት በመምህር ዘላለም ንጉሴ የተሰጠ ሲሆን የወላጆች፣ ተማሪዎች እና መምህራን ትስስር ከግብረገብ ምንነት እና አስፈላጊነት አንጻር እንዲሁም ኢትዮጵዊ እሴት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት አስተዳደር የሆኑት አቶ አድጎ አድምጥ የተማሪዎች ሥነ-ምግባር እና ግብረገብነት የትምህርት ቤቱ፣ የወላጆች እና የማህበረሰቡም ኃላፊነት ጭምር ነው ያሉ ሲሆን ሥልጠናው ወላጆች ለልጆቻቸው አርአያ ሆነው ልጆቻቸውን መቅረጽ እንዲችሉ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ አስተዳደሩ ጨምረውም ልጆችን በስነምግባር አንጾ ማሳደግ የሁላችንም ድርሻ በመሆኑ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
ማህበረሰባዊ እሴቶችን አክባሪነት፣ ለሰው እኩል ክብር መስጠት፣ ማህበረሰባዊ ተደጋጋፊነት፣ ቅንነት፣ታዛዥነት እና የአገልጋይነት ስሜት የመሳሰሉት ርዕሰ ጉዳዮች እና ሌሎች በርካታ የሥነ-ምግባር መገለጫዎች በስልጠናው ተዳሰዋል፡፡
የቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ ከሰባት - አስራሁለተኛ ክፍል ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ አዲሱ አጥናፉ አቡነ ጎርጎርዮስ ካለው አላማ አንጻር ብቻ ተሰርቶ ለውጥ ላይመጣ ይችላል እኛ የሰራነውን ሌሎች ሊያፈርሱት ይችላሉ፡፡ ስለዚህ እንዴት ልጆቻችንን እናሳድግ በሚል ወላጆች ያልሆኑትን ልጆቹ ላይ ለማየት መጠበቅ አስቸጋሪ ስለሚሆን ሥልጠናውን ለወላጆች መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል፡፡
በሥልጠናው ተሳታፊ የነበሩ ወላጆች በበኩላቸው ራሳችንን እንድናይ እና የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመቅረጽ የድርሻችንን እንድንወጣ መነቃቃትን ፈጥሮልናል ያሉ ሲሆን አክለውም ይህን መሰል ሥልጠና በቀጣይም ማግኘት ብንችል ሲሉ የሥልጠናውን አስፈላጊነት ጠቁመዋል፡፡

የአክሲዮን ማህበራችንን ድህረ ገፅ https://esdros.com/e/ በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ።
2.8K viewsEsdros ICT, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-08 18:44:43
2.4K viewsEsdros ICT, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ