#ፍትህ_ለእህታችን_ፀጋ_በላቸው ! በሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ የተጠለፈችው ፀጋ በላቸው ! የዳሽን ባንክ ሐዋሳ ዋርካ ቅርንጫፍ ሰራተኛ ነች ። ፀጋ በላቸው ትባላለች፤ ለማግባት ጥቂት ጊዜ ቀርቷት በዝግጅት ላይ ነበረች። ሆኖም ግን ፤ ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም. ከስራ ወደቤት ስታቀና ፤ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጠባቂ የሆነው ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ጠልፎ ተሰውሯል ። ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በማሳወቅና የፍርድ ቤት መጥሪያ በማውጣት ተጠርጣሪውን ለመያዝ ቤተሰቦች የቻሉትን ቢያደርጉም ፤የሲዳማ ክልል ፓሊስ ጉዳዩን በቸልተኝነት አለፍ ሲልም ተባባሪ በሚመስል መልኩ ጉዳዮን ይዞት፤ ለባለፉት 7 ቀናት ፀጋ በላቸው የት እንዳለች አናውቅም በማለት ፤ ቤተሰብ ጭንቅት ላይ ነው። ሼር #ፍትህ_ለእህታችን_ፀጋ_በላቸው @abisiniya_times @abisiniya_times 2.9K viewsedited 19:35