Get Mystery Box with random crypto!

📚ፈዋኢድ እና ፈራኢድ📚

የቴሌግራም ቻናል አርማ abdurezaq27 — 📚ፈዋኢድ እና ፈራኢድ📚 ፈ
የቴሌግራም ቻናል አርማ abdurezaq27 — 📚ፈዋኢድ እና ፈራኢድ📚
የሰርጥ አድራሻ: @abdurezaq27
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.15K
የሰርጥ መግለጫ

والسلام على من اتبع الهدى!

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 23:09:31 አንዘርቱኩሙ’ ናር!

☞ እሳትን አስጠንቅቄያችኃለው!
ከ12 አመት በፊት በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ እጅግ ገሳጭ ትምህርት


Share share share

በኡስታዝ አሕመድ አደም

@nesihastudio
103 viewsedited  20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:00:24 ለአርባ ሺህ ሰዎች መስለም ሰበብ የሆነው አስደናቂ ውሻ ገድል!


☞የክርስትና እምነት ተከታዮች ሞንጎላዊያን ክርስትናን እንዲቀበሉ በመቋመጥ በሞንጎላዊያን ጎሳዎች መካከል ሰባኪዎቻቸውን ይልካሉ። ይህን መስመር ያመቻቸላቸው አረመኔው ሆላኮው አንዲት ዘፈር ኻቱን ከምትባል ክርስቲያን ሴት ጋር በትዳር በመቆራኘቱ ሰበብ ነበር።

ከእለታት አንድ ቀን ታላላቅ የሚባሉ የክርስቲያን ቀሳውስት ከሞንጎላዊያን መሪዎች መካከል አንዱ ክርስትናን በመቀበሉ ሰበብ የተደገሰውን ታላቅ ድግስ ለመታደም ወደ ቦታው ተመሙ። በዚህም መሀል ከቀሳውስቱ መካከል አንዱ ተነስቶ የአላህ መልእክተኛን ሙሐመድን (صلى الله عليه وسلم) መሳደብ ጀመረ። እዛው ቦታ ላይ የአደን ስልጠናን በሚገባ የተማረ አደገኛ ውሻ ታስሮ ነበር። ይህ ክፉ መስቀለኛ ቄስ ረሱልን መሳደብ ሲጀምር ውሻው ማጉረምረም ጀመረ። ከዛም በእልህ እየጮኸ ቄሱ ላይ ዘሎ በሀይል ቧጨረው። ቦታው ላይ የታደሙ ሰዎች ቄሱን ከዚህ አደገኛ ውሻ በመከራ ገላገሉት።

ይህን ክስተት እዛው ተጥደው የነበሩ ሰዎች "የሙሐመድን ክብር ስለነካህ ይሆናል ውሻው እንዲህ የቧጨረህ" አሉት።
ቄሱም "በፍፁም! ውሻው አደገኛ ስለሆነ በእጄ ወደ እሱ ሳመላክት ልመታው ያሰብኩ መስሎት ነው የዘለለብኝ" አለ።

ከዚያም የአላህ መልእክተኛን በድጋሚ መወረፍና መሳደቡን ተያያዘው። የዚህ ግዜ ነበር ጉዱ ........
ውሻው የታሰረበትን ገመድ በጥሶ የቄሱ አንገት ላይ ዘሎ ደም ስሩን በጣጥሶ ወዲያውኑ ገደለው። እስትንፋሱን አሳጣው።

ይህን አስደናቂ ትእይንት ሲመለከቱ የነበሩ ወደ አርባ ሺህ ሞንጎላዊያን ኢስላምን ተቀበሉ።

አላሁ አክበር!


☞ይህን አስደናቃ ክስተት ታላቁ የኢስላም ሊቅ ኢብኑ ረጀብ (አላህ ይዘንለት) በዚህ ድርሳናቸው አፅድቀው ከትበውታል ▼▼▼▼▼▼

[الدرر الكامنة (202)]

እስኪ እኔን አንዴ አንብቡኝ!

☞የዚህን ውሻ አንድ አስረኛ እንኳን ለኢስላምና ለሱና መቆርቆር በቻልን አትሉም!

☞በህይወት ዘመንህ ቢያንስ አንድ ሰው በሰበብህ ወደ ኢስላም እንዲገባ ጥረት አርግ። ይህ ካቃተህ ከኢስላም እንዳይወጣ ታገል። ይህ ካቃተህ በአንተ ሰበብ ሰዎች ከኢስላም እንዳይወጡ ሞክር። ይህ ካቃተህ ውሻው ከአንተ ይሻላል ማለት ነው!

☞ውሻው ሰንሰለቱን ፈቶ ጠላት ላይ እንደዘለለው እኛም በስሜት ማነቆ የታሰርንበትን ዘለበት ፈተን ለኢስላም ዘብ እንቁም!

☞እንደ ውሻው መናከስ ባንችልም ሱናን ነክሰን እንያዝ!

☞እንደ ውሻው መጮህ ባንችልም ሱናን ለማስተማር በየቦታው ለሚጮኹ እውነተኛ ዳዒዎች ጆሮአችንና ልባችንን ለባጢልና ቢድዓ ደሞ ጀርባችንን እንስጥ!

☞አመት ጠብቀህ መልእክተኛውን እወዳለሁ እያልክ ከሴት ጋር ተቀላቅለህ እየጨፈር ከምትረብሽ ሱናቸው ሲረሳ ቢድዓ ሲነግስ ጀግና ሁን።

"إنا كفيناك المستهزئين"


(ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሀል)

[ሱረቱ'ል ሒጅር :(95)]


ዐብዱረዛቅ አል-ሐበሺይ

https://t.me/abdurezaq27
246 views14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 06:47:10
የማለዳ ፈዋኢዶች¹²

"ታላላቅ ስብእናዎችን መገንባትና ማነፅ ከፈለግን በዲን የታነፁ እናቶችን ልናፈራ ይገባናል። ይህን ታላቅ ትውልድ ማግኘት የምንችለው ሴቶችን ዲናቸውን በማስተማርና በኢስላማዊ ተርቢያ ማሳደግ ከቻልን ብቻ ነው። ነገር ግን ሴቶቻችንን ዲናቸውን የማያውቁ ሆነው በመሀይምነትና ፅልመት ላይ ከተውናቸው በፍፁም ታላላቅ የኢስላም ስብእናዎችን እናፈራለን ብለን መጠበቅ የለብንም።"

~ #آثَار ابن باديس رحمه الله (٢٠١/٤)
https://t.me/abdurezaq27
193 views03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 06:26:27 ልቅ የሆኑ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎችን በመመልከት ለተለከፉ ሁሉ!

እነዚህ ፊልሞችና ምስሎች የጀሀነም በሮች ናቸው!

እነዚህን የበከቱና የተግማሙ ዝሙተኞችን በማየት እስረኛ የሆንክ/ሽ ሁሉ በዚህ ሰበብ ምን እንደሚከተልህ/ሽ ተከታዩን እስተውለህ/ሽ አንብብ/ቢ!

☞ለላጤዎችና ለባለትዳሮች መጨረሻ ላይ የተቀመጠውን መፍትሄ በጥሞና አንብቡት!

☞የተራቆቱ ዝሞተኞችን ማየት እጅግ ከባባድ ወንጀሎች ውስጥ እንደሚካተቱ ታውቃለህ?

☞እነዚህን ዝሙተኞች መመልከት ውርደትና ደካማነት እንደሚያወርስ ታውቃለህ?

☞እነዚህን ዝሙተኞች መመልከት በሰዎች አይን ያነስክና ወራዳ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?

☞እነዚህን አፀያፊ ምስሎችና ቪድዮዎች በማየት የተለከፈ ወጣት በቀላሉ ካገኘው ተቃራኒ ፆታ ጋር ሁሉ ዝሙት ላይ የሚወድቅ ይሆናል። እንዲሁም ራስን ወደ ማርካት (masturbation) ሱስና የስንፈተ ወሲብ አደጋ ተጋላጭ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው።

☞እነዚህን የዝሙት ዌብሳይቶችና የቪድዮ ምስሎች መመልከት በአእምሮህና በአይንህ ላይ ድክመትን እንደሚከስት ታውቃለህ? ይህን በመመልከት ሱሰኛ የሆነ ሰው ቀለል ያሉ ጉዳዮችን በቀላሉ ይረሳል። ይህ አደጋ እያደገ ሲሄድ የአእምሮ ድክመት አስከትሎበት እንዴት መናገር እንዳለበት ሁሉ ላያውቅ ይችላል! ሌሎችም ብዙ የጤና እክሎች ያጋጥሙታል!

☞ይህ ወንጀል አላህ ዘንድ ወራዳ ሰው እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?

☞የእነዚህ ዝሙተኞች ምስል አእምሮህ ላይ ተቀርፇል? (ይህ የአላህ ቁጣ ምልክት ነው!)

☞እነዚህን ነገሮች መመልከት ትንንሽ ነገሮችን ሁሉ የምትሰጋ ፈሪና ልፍስፍስ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?

☞ይህን እርቃን ብልግና የምትመለከት ሆይ! የሸሪዓ እውቀትን ብርሃን በፍፁም ማግኘት እንደማትችል ታውቃለህ?

☞በዚህ ወንጀልህ ከምትወዳትና ከምትወድህ የህይወት አጋርህ ባለቤትህ ጋር የተረጋጋ ህይወት መኖር እንደምትነፈግ ታውቃለህ?

☞ይህን አስቀያሚ ተግባር የምትመለከት ከሆነ ደጋግ የአላህ ባሪያዎች ይህን ቀፋፊ ተግባርህን ባትነግራቸውም እንኳን ሊጠሉህ እንደሚችሉ ታውቃለህ?

☞እነዚህን ዝሙተኞችን ማየት ግዴታ የሚሆንብህ በዝሙት ወንጀላቸው በድንጋይ ተወግረው ሲገደሉ ብቻ እንደሆነ ታውቃለህ?

☞ ከዚህ ከምትመለከተው ቀፋፊ ምልከታ እውነተኛ ተውበት አድርገህ ወደ አላህ ካልተመለስክ እጅግ ከባድ ዋጋ ለወደፊት እንደሚያስከፍልህ ታውቃለህ?

☞እጅግ የምትወደውና የምትቀርበው ሰው ሞት ዜና ይህን ነገር እየተመለከትክ ብትሰማ ትወዳለህ?

☞ ከዚህ ወንጀል አፀያፊነት የተነሳ አላህ መሬትን ደርምሶ ሊያስውጥህ እንደሚችል ታውቃለህ?

☞በዚህ ቀፋፊ ምልከታ ላይ ሆነህ ሞት ሊመጣህ እንደሚችል ታውቃለህ? አስከፊ ኻቲማ ሊያስደነግጥህ እንደማይችል እርግጠኛ ነህ?

☞ጌታህ ቻይ ነው! ለግዜው ይተውኃል፤ ነገር ግን በምትሰራው ወንጀል ደስተኛ ሆኖ እንዳይመስልህ! ከዚህ ወንጀልህ ተውበት ካላደረክ ለወደፊትም ቢሆን ከባድ መከራ ትጋረጣለህ!

☞ የዒባዳህን ጥፍጥና እንደሚያሳጣህ አምልኮ ላይ ደካማ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?

ለዒባዳ በቆምክ ቁጥር የምታያቸው ምስሎች አዕምሮህን ተቆጣጥረው እንደሚፈታተኑህ ታውቃለህ? በዚህም ከአምልኮ መሸሽና ተስፋ ቢስነት ሊሰማህ ይችላል። ይህ ደግሞ ወደ አደገኛው አዘቅት ክህደት የሚጎትት ጠንቅ ነው።

☞ ራስህን የምትጠላ የወንጀል ምርኮኛ እንደሚያደርግህ ታውቃለህ?

☞ለአላህ ብሎ አንዳች ነገርን
የተወ ሰው አላህ የተሻለ መልካም ነገር እንደሚተካለት ታውቃለህ?

☞አላህ በባሪያው መመለስ የሚደሰት የተብቃቃና ምስጉን ጌታ መሆኑን ታውቃለህ?

☞ከወንጀል ጥብቅ ከሆንክ አላህ ከችሮታው እንደሚያብቃቃህ ታውቃለህ?

☞ለደቂቃዎች (ሻህዋ) ስሜት ተብለው የሚሰሩ ወንጀሎች የአመታት ቅጣት እንደሚያመጡ ታውቃለህ?

☞ዛሬ በዱንያ ላይ የምትሰራቸው ወንጀሎች፦ የተከለከለን ማየት፣ መስራትና ሌሎችንም በዱንያ ላይ ቅጣቱን በድህነት፣ በአደጋ፣ ሪዝቅህን በመከልከል በቤተሰብህ፣ በልጆችህና በቅርብ ሰዎች ላይ አደጋ ሊከስት እንደሚችል ታውቃለህ?

☞ይህ ወንጀል አእምሮህን ተቆጣጥሮ ከምትመለከታት ሴት ሁሉ ቀፋፊው ዝሙት ላይ ለመወደቅ እንደሚገፋፋህ ታውቃለህ?





☞ለላጤዎች ምክር!

ያላገባህ እንደሆነ በተቻለህ መጠን ለማግባት ሞክር!

ስለ ትዳር በቂ እውቀት ይዘህ ወደ ትዳር ግባ!

ማግባት ካልቻልክ ትርፍ የምትለውን ግዜህን በመልካም ነገር አሳልፍ፦ በፆም፣ በንባብ፣ ስፖርት በመስራት፣ መልካም ኢስላማዊ ትምህርቶችን በመማር፣ በመስማትና በማየት.......

በብዛት ብቻህን ከመሆን ተቆጠብ

አላህን ከዚህ ቀፋፊ ወንጀል ነፃ እንዲያደርግህ ተማፀን!

መልካም ሰዎች ጋር ለመቀማመጥ ሞክር!

ሸይጣን ይህን ወንጀል ባስታወሰህ ቁጥር ቆራጥ ሆነህ ላለመመለስ ሞክር! መጀመሪያው ቢከብድብም በሂደት አላህ ይረዳሃል!

☞ለባለ ትዳሮች ምክር

አግብተህ ከሆነ ከትዳር አጋርህ ጋር ስለ ህይወታቹህ ያለ እፍረት በግልፅ በመነጋገር የምትፈልጉትን እርካታ ሁሉ ማግኘት እንደምትችል እውቅ!

በኢስላም ጥላ ስር ያሉ ታማኝ ከትዳር ህይወት ጋር የተያያዙ አስፈላጊ ትምህርቶችንና ጥናታዊ ፅሁፎችን አንብብ!

በዚህ ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸውን አላህን የሚፈሩ ብለህ የምታስባቸውን ወንድሞችህን አማክር!

ሚስትም የዘመኑን ክፋት ልትረዳና ነቃ ብላ ከትዳር አጓሯ ጎን ልትቆም ይገባል። በግልፅ ማውራትና ፍላጎቱን ማሟላት ብልግና ሳይሆን ብልጠት መሆኑን አውቃ በተቻለ መጠን ውበቷን በመጠበቅ የባሏ ልብ እንዳይሸፍትና እንዳይሰላች የበኩሏን ጥረት ሁሉ በማድረግ ባለቤቷን ማስደሰት አለባት!

እነዚህ የተግማሙና የበከቱ ዝሙተኞች ይህችን አጭር ህይወትን እንዲያበላሹ አትፍቀድ! ጀግና ሁን/ሁኚ!

በመጨረሻም የመልካም ሰዎችን ታሪክ አንብብ! እንዴት አላህን እንደሚጠነቀቁ አስተውል። አስተንትን! በዚህ ወንጀልህ የሰማያትና የምድር ጌታን እያመፅክ መሆኑ ይሰማህ!
ኮምፒዩተሮችህና ስማርት ስልኮችን የመዋረጃህ ሰበብ አታድርጋቸው!

ኢብኑ'ል ወርዲይ በግጥማቸው እንዲህ ብለዋል ፦
إنَّ أحلى عيشةٍ قضيتُها
ذهبتْ لذاتُها والإثمُ حلْ

ስሜቴን ያራገፍኩባቸው ጣፋጭ ግዜያቶች
ጥፍጥናቸው ሄዷል ወንጀሉ ቅን ቀርቷል/ተመዝግቧል


ሁላችንንም አላህ ለሚወደው ይምራን!

ዐብዱረዛቅ አል-ሐበሺይ


https://t.me/abdurezaq27
432 viewsedited  03:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 15:08:09 ከነዚም መካከል ኢማሙል ገዛሊይ ለነበረበት ስህተት በፀፀት እንባን በማንባት ወደ ሰለፎች መንድ ተመልሷል። ለዚህም እማኝ ይሆን ዘንድ "ኢልጃሙል ዐዋም ሚን ዒልሚል ከላም" የሚልን ድርሰት አኑሯል

። እንዲሁም ኢማሙ'ል ሐረመይንና የእሱ ወላጅ አባት፣ ኢማሙ አ

ር'ራዚ፣ ሺህርስታኒን የመሳሰሉ ታላላቅ የአሻዒራ ስብእናዎች ከዚህ ከነበሩበት ጥመት በመፀፀት በጥቅል ወደ ሰለፎች ጎዳና ተመልሰዋል "ዒልመል ከላምን" ማለትም ወደ የእምነት መሰረታዊ ጭብጦችን ለማወቅ በሚል ፈሊጥ የተዘረጋን የተምታታ ፍልስፍናን ኮንነዋል።
በተለይ የኢማሙ'ል ሐረመይን ወላጅ አባት እንዴት እንደተመለሰ በዝርዝር አስቀምጧል። ይህን መልእክት "አልሙቱኑል ሙኒሪያ"በሚል የተለያዩ የድርሰቶች ስብስብ ውስጥ ያገኙታል። ስለዚህ አሽዐሪያ ማለት አቡል ሐሰን የነበረበት ዐቂዳ ነው። ቡኋላ ስህተቱን ተገንዝቦና ይህን ምልከታውን ውድቅ አርጎ ወደ ሰለፎች መንሀጅ ተመልሷል።

በተለያዩ ኢስላማዊ ዩንቨርስቲዎች በተለይ ግብፅ በሚገኘው አል-አዝሀር ዩኒቨርስቲ ይህ የአሽዐሪያ ዐቂዳ በዳዕዋ እና በኡሱሉ ዲን ዲፓርትመንት ይሰጣል። የአል-አዝሀር ተከታይ የሆኑ ዩኒቨርስቲዎችም ይህን አቡል ሐሰን ስህተቱን አጋልጦ ጥሎት የሸሸውን ብልሹ ዐቂዳ ያስተምራሉ።

በአጭሩ አሽዐሪያ ማለት ይህ ነው።

መነሻ ሀሳብ
المصدر : www.eljame.com/217

موقع العلامه محمد امان الجامي

ዐብዱረዛቅ አል-ሐበሺይ


ጥቅምት 2010 ከአራት አመት በፊት የተፃፈ
https://t.me/abdurezaq27
472 viewsedited  12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 15:08:09 عبد الرزاق الحبشي:
ዝክረ-ተውሒድ

☞"አል-አሽዐሪያዎችን" በአጭሩ እንተዋወቅ!

☞አል-አሻዒራ ማለት ወደ አቡ'ል-ሐሰን ኢብኑ ዐሊይ ኢብኑ ኢስማዒል አል-አሽዐሪይ የሚዛመዱ የፍልስፍና አንጃዎች ናቸው። ይህ ሰው ወደ ታላቁ ሰሐቢይ አቡ ሙሳ አል-አሽዓሪይ የሚዘዝ የዝምድና ትስስር አለው። አቡል ሐሰን አል-አሽዓሪይ ከእድገቱ መባቻ አንስቶ "ሙዕተዚላህ" ተብላ በምትጠራ አንጃ አስትምህሮት ስር ተኮትኩቷል። ይህም የሆነበት ምክንያት የዚህ አንጃ ፊት አውራሪ መምህር የሆነው አቡ ዐሊይ አል-ጁባኢይ የእናቱ ባል በመሆኑ ለእሱም የእንጀራ አባቱ ስለሆነ ነው። በጁባኢይ ስር በመሆን የሙዕተዚላን አስተምህሮት እየቀሰመ እድሜውን አሳልፏል። ይህን ስንል "ሙዕተዚላዎች ማን ናቸው?" ማለታችሁ አይቀርም አንዱ አንዱን ይመዛልና፤ በመሆኑም ሙዕተዚላህ የተባለው ቡድን ከጥመት ቡድኖች መካከል ፊት አውራሪ ሲሆኑ የአሏህን ባህሪያትና መገለጫዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግና ባለመቀበል ይታወቃሉ።
ይህንም ጠፍ ተግባራቸውን "አሏህን ከጉደለት ለማጥራት ነው!" በሚል ማምታቻ ይሸፋፍኑታል።
የአሏህን ባህሪያቶች ውድቅ ማረግ ማለት አሏህ ሀይል የለውም፣ መስሚያ የለውም፣ መሻት የለውም፣ አይናገርም .....ሌሎችንም ባህሪያቶች እንዲህ ባለ ሰላማዊ አእምሮንም ሆነ ትክክለኛ አስረጂዎችን በሚቃወም መልኩ በሰቀጠጠ ገለፃ ይገልፃሉ። ይህ አካሄድ የሙዕተዚላዎች አካሄድ አልያም ምልከታ በመባል ይታወቃል። በግልፅ እንደሚታወቀው የአሏህ እጅግ የተዋቡ ስሞቹ እና የላቁ ባህሪያቶቹን አስመልክቶ የቀደምት የኢስላም አበው ማለትም የሰለፎች መንገድ እነዚህን ስሞችና ባህሪያት ከፍጡራን ጋር ሳያመሳስሉ፣ ትርጉማቸውን ሳያራቁቱ (ትርጉም አልባ) ሳያደርጉ፣ ትርጉማቸውን ከትክክለኛው እሳቤያቸው ሳያዛቡ እንዲሁም ያሉበት ሁኔታን ሳይገልፁ መሰረታዊ ትርጉማቸውን በመረዳት የይዘታቸውን ምንነት እውቀት ወደ አሏህ አስጠግተው ያፀድቃሉ። ይህም ትክክለኛው የነብያቶች መንገድ ነው። ከዚህ ትክክለኛ ዐቂዳ በተቃራኒ የሰፈሩት የጥመት አንጃዎቹ ሙዕተዚላዎች የቆጠቆጡበት ዋነኛ ሰበብና ታሪካዊ ዳራ እንደሚጠቁመው የሙዕተዚላህ መነሻ ስብእና የሆነው ዋሲል ኢብን ዐጣእ እና አጃግሬዎቹ የታላቁን ሊቀ ኢስላም ሐሰነል በስሪን ትክክለኛ ምልከታ ገሸሽ በማረግ የራሳቸውን ውግዝ አመለካከት በመያዝ ከሳቸው የትምህርት መአድ እራሳቸው በማሸሻቸው እንዲሁም ሰዎችን በመገንጠላቸው ምክንያት ነው። በዚህ ምክንያት ተገንጣይ ጠርዘኞች የሚል ስም ተሰጣቸው በዐረብኛ "ሙዕተዚላህ" ለሚለው ቃል ተቀራራቢ ፍቺ ይመስላል። ነገር ግን ከሐሰን የእውቀት መቀማመጥ ብቻ ሳይሆን አያሌ ከሆኑ የሙስሊሞች ትክክለኛ እምነት ፅንሰ ሀሳብ በመገንጠላቸውም ምክንያት ነው ይህን ስም የተጎናፀፉት።
"ታዲያ በዚህ ዘመን ሙዕተዚላዎች አሉ!?" ብለህ ከጠየክ መልሱ "በሚገባ!" ይሆናል ። የሺዓ አመለካከት ያለው በአጠቃላይ የሙዕተዚላህ ዐቂዳ አራማጅ ነው። ይህን እንደ መርሆ ያዙ።
ሁሉም ሺዓዎች ትንሽ ወደ ሱና የቀረቡ ናቸው ከሚባሉት ዘይዲያዎች አንስቶ ከሱና እጅግ ከራቁት ጃዕፈሪያዎችና ኢማምያዎች ጭምር እምነታዊ ምልከታቸው (ዐቂዳቸው) ከሙዕተዚላዎች ጋር የገጠመ ነው።
አቡል ሐሰን አል ዐሽዓሪይም በዚህ በሙዕተዚላህ ዐቂዳ ላይ አርባ አመታትን አሳለፈ። ከአጎቶ ቀጥሎም የዚህ አንጃን ታላቅ ስብዕናን ለመላበስ በቃ። ነገር ግን የአሏህ ፍላጎት ሆነና ከአጎቱ ጋር በአንዳንድ መሰረታዊ ነጥቦች ዙሪያ መስማማት ላይ መድረስ ሳይችሉ ቀሩ። ይህም አሏህ ለባሮቹ ይበልጥ የሚበጃቸውን መተግበር ግዴታ አለበት የሚለው አደገኛ ጠንቅ ያለው አመለካከት ነው። እንደሚታወቀው አሏህ በግዴታ ሳይሆን በመፃደቅና፣ በችሮታው እንዲሁም በእሱ መሻት ለባሮቹ መልካም ይመነዳል እንጂ እሱን በተግባሩ ላይ የሚያስገድደው የለም። የአሏህ ችሮታ እና እዝነት ካላገኘው በስተቀር ማንም በስራው ጀነት እንደማይገባ የሚያስረዱ ነብያዊ ፈለጎች እንዳሉ ማንኛውም ሙስሊም የማይክደው እውነታ ነው።
አቡል ሐሰን ይህን "አሏህ ለባሮቹ መልካምን ማረግና ለሰሩት ደግ የመመንዳት ግዴታ አለበትቀ" የሚለውን የሙዕተዚላዎች ምልከታ ንፁህ በሆነ አእምሮው ሊቀበለው አልቻለም።
በዚህም የተነሳ ከሙዕተዚላህ መንገድ በመሸሽ ሀቅን መፈለግ ጀመረ። የአቡ'ል ሐሰን ሀቅን የመፈለግ ውጣ ውረድ ከታላቁ ሰሐቢይ ሰልማን አል-ፋሪሲይ ውጣ ውረድ ጋር ይመሳሰላል ይህ ሰሐቢይ በመጀመሪያ እሳት አምላኪ(መጁስ) እንደነበር ቡኋላም ሀቅን ለመድረስ አንድ ባህታዊ ጋር እንደዘወተረ በመጨረሻም የአሏህ መልእክተኛን በመዲና በማግኘት አላማው መሳካቱን እናውቃለን።
አቡል ሐሰንም ሀቅን ለመፈለግ ባረግው ጥረት የሰለፎች መንሀጅ የመሰለውን የኩላቢያን መንገድ መከተልን መረጠ። በሂደትም ይህ የኩላቢያ አስተሳሰብ ወደ አቡል ሀሰን እንዲጠጋ ሆነ። ሰበቡም አቡል ሀሰን በእውቀቱ እጅግ የገነነ በመሆኑና በዘር ሀረጉም የተሻለ እውቅናና ክብር ስላለው የዚህ ምልከታ አስተሳሰብ ከባለቤቱ ይልቅ ወደ አቡል ሐሰን ተጠጋ። ይህ ዐቂዳም የአቡል ሐሰን ዐቂዳ ተብሎ ተቆጠረ፤ አስተሳሰቡና ምልከታውም የአሽዐሪያ ምልከታ በሚል መጠነ ሰፊ እውቅናን አገኘ።

ይህ የአሽዐሪያ አስተምህሮም ልክ እንደ ሙዕተዚላዎች ሙሉ በሙሉ የአሏህን ባህሪያቶች ውድቅ ከማረግ ይልቅ ባህሪያቶቹን በአእምሮ የምናፀድቃቸው ባህሪያትና በወሬ ብቻ የምንቀበላቸው ባህሪያት ብሎ ይከፋፍላል።
በዚህም ምክንያት አእምሮ ያፀደቃቸውን ባህሪያቶች እንቀበላለን አእምሮ ያላፀደቃቸውን ባህሪያቶች ግን ለአሏህ አናፀድቅም የሚል እርስ በእርሱ የተምታታ ፈሊጥ ነው።
በዚህ ምልከታ ላይ የተወሰኑ ዘመናትን ካሳለፈ ቡኋላ ልክ ሰሐብዩ ሰለማን የአሏህ መልእክተኛን በመጨረሻ እንዳገኘና ሀቀን እንደተቀበለ ብጤ አቡል ሐሰንም ወደ ትክክለኛው የሰለፎች ጎዳና ለመመለስ በቅቷል። መመለሱን የሚያረጋግጡ ድርሰቶችን ፅፏል። ከዚህም መካከል "አል-ኢባናህ" የተሰኘው ድርሰት በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ይህ ድርሰት ታትሞ በየቦታው የሚገኝ ሲሆን በዚህ መፅሀፍ ውስጥ እሱ በታላቁ የአህለ ሱና ሊቅ በሆኑት በአል ኢማም አሕመድ ኢብን ሐንበል መንገድ ላይ እንዳለ ጠቅሷል። የሚገባቸውንም ሙገሳ በመፅሀፉ ውስጥ አስፍሯል። ወደ ሰለፎች ጎዳና መመለሱንም ይፋ አድርጓል።

ይህ የአሽዐሪያ አስተምህሮ ከሳውዲ ዐረቢያ ውጪ ባሉ የተለያዩ ኢስላማዊ ዩኒቨሪስቲዮች
ይሰጣል። ይህች ዐቂዳ የኩላቢዮች ስትሆን አቡል ሐሰን ከነበረበት የሙዕተዚላህ ዐቂዳ የተሻለ መስሎት ለተወሰኑ አመታት ያራመደው ነው። ቡኋላ ይህን ምልከታ ወደ እሱ በጠቀስነው ምክንያት እንዳስጠጉት ተመልክተናል። እነዚህ የአሽዐሪያን ዐቂዳን እንከተላለን የሚሉ ጭፍራዎች በአቡ'ል ሐሰን ላይ መቅጠፋቸውን አላቆሙም። እሱ ከነበረበት ምልከታ እንደተመለሰ የፃፋቸውን አያሌ ድርሰታት የሰለፎችን መንገድ እንከተላለን የሚሉ ሰዎች በሱ ላይ ቀጥፈው የፃፉት እንደሆነ ደጋግመው ይሞገታሉ። ነገር ግን የአሏህ ፍቃድ ሆኖ እሱ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ከእሱ ቡኋላ የመጡ የዚህ የአሽዐሪያ ዐቂዳ ታላላቅ ስብእናዎች የነበሩ የአቡል ሐሰን ተከታዮች የነበሩበትን ዐቂዳ ስህተት በማጋለጥ ወደ ሰለፎች መንገድ ለመመለስ እንደሞከሩና እንደተመለሱ በተለያዩ ድርሰቶቻቸው ላይ አስፍረዋል።
372 views12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 23:32:13 ሁለቱ ገጣሚ ሚስቶች

# الزوجتان الشاعرتان #

يُحكى أنه كان لأعرابي زوجتان فولدت إحداهما ولداً والأخرى بنتاً،

☞ሰዎች ዘንድ የሚተረክ ታሪክ ነበረ እሱም ፦

አንድ አዕራቢይ ሁለት ሚስቶች ነበሩት። አንደኛዋ ወንድ ልጅ ስትወልድ ሌላኛው ሴት ልጅ ወለደችለት።

فكانت أم الولد تحمله وترقص به أمام ضرتها لتغيضها وتقول:

ወንድ የወለደችው ሚስቱ ወንድ ልጇን ተሸክማ ጣውንቷ ፊት ለፊት ሆኖ ልጇን እያጫወተችና እየተወዛወዘች ትቦርቃለች። ሴት ወላዷን ለማናደድም እንዲህ እያለች ትገጥም ነበር

الحمد لله الحميد العالي
أكرمني ربي وأعلى حالي
ولم ألد بنتاً كجلدٍبالي
لا تدفغ الضيم عن العيال.

ከፍ ላለው አላህ ምስጋና ይገባው
ክብሬን ደረጃዬን እጅግ ከፍ አረገው
ሴትን አልወለድኩ እንደ ብስብስ ቆዳ
ከቤተሰቦቿ በደል መከራን ማታፀዳ

فاغتاضت أم البنت وراحت تشكوا ضرتها إلى زوجها ،فقال لها كلمة بكلمة، قولي لها: مثل ماتقول،

ሴት የወለደችው ሚስቱ ይህን የሰማች ግዜ በጣም ተናደደች። ለባሏም ስሞታ ልታቀርብ ሄደች። ይህን ግዜ ባሏ "እሷ እንዳለችሽ አንቺም በያት!" አላት።

فنظمت أم البنت أبياتاً وأصبحت ترقص بإبنتها وتقول:

የሴቷ እናትም እንዲህ የሚል ግጥም እየገጣጠመች ልጇን ይዛ መወዛወዝ ጀመረች።

وما علي أن تكون جارية
تغسل رأسي وتراعي حالية
وترفع ماسقط من خمارية
حتى إذا ما أصبحت كالغانية
زوجتها مروان أو معاوية
أصهار صدقٍ ومهورغالية.

ሴት ብትሆን እኔ ምን ገዶኝ
ፀጉሬን ምታጥብ ምታሰናዳኝ
የወደቀ ሻርፔን አንስታ ምትሰጠኝ
ውበቷ ደምቆ እጅግ ስታማልል
መርዋን ወይም ሙዓውያ ያገቧታል
የእውነት አማቾች መህሯ ይወደዳል

فشاعت أبياتها في الناس،
ولما كبرت البنت قال الأمير مروان بن الحكم : أكرم بالبنت ولاتُخيب ظن الأم ،
فخطب البنت وقدم لها مئة ألف درهم مهرا.

ይህ የሴቷ እናት ግጥም በሰዎች መሀል በጣም ተሰራጨ። ልጅቷ ያደገች ግዜ አሚር የነበረው መርዋን ኢብኑል ሐከም "የእናቷን ምኞት ከንቱ አላረግም!" ብሎ ልጅቷን አጭቶ አገባት። አንድ መቶ ሺህ ዲርሀም መህርም ሰጣት።

فلما علم _ معاوية ابن أبي سفيان- بالأمر قال: لولا أن مروان سبقنا إل
يها لضاعفنا لها المهر،ثم بعث للأم بمئتي ألف درهم هبة من عنده.

ሙዓውያም ይህን ታሪክ ሲሰማ "መርዋን ባይቀድመኝ ኖሮ ከሰጣት መህር በላይ እጥፍ አርጌ አገባት ነበር!" አለ። ከዛም ለእናትየው ሁለት መቶ ሺህ ዲርሀም ስጦታ ብሎ ላከላት።

≅ምንጭ


# فوائد ..... من كتاب،
"# لطائفـ المعارف#"
لإبن رجب الحنبلي رحمه الله


ዐብዱረዛቅ አል-ሐበሺይ

https://t.me/abdurezaq27
871 views20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 08:37:24 «دع السفهاء وليقولوا ماشاءوا !»

‏ قال الشيخ العلامة محمود شاكر رحمه الله:

«وليعلم كل من لا يعلم أن السفهاء في الدنيا كثير، فإذا كان يغضب لكل سفاهة من سفيه، فإن شقاءه سيطول بغضبه، فدع السفهاء وليقولوا ما شاءوا، وكن أنت ضنينًا بكرامتك، فإنها أعزّ وأغلى من أن تُبذل على الألسنة»

[جمهرة المقالات ١ / ٥٩٧]
381 views05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-08 13:35:08 قال ابن الجوزي -رحمه الله- :

‏"ﻭﻳْﺤَﻚ ﺃﻧﺖَ ﻓﻲ اﻟﻘﺒﺮِ ﻣﺤْﺼُﻮﺭ إلى ﺃﻥ ﻳﻨﻔﺦَ ﻓﻲ الصُّور، ﺛﻢ ﺭاﻛﺐ ﺃو ﻣﺠْﺮﻭﺭ، ﺣﺰﻳﻦٌ ﺃﻭ مسْرُور، ﻣﻄﻠﻖٌ ﺃﻭ مأْسور، ﻓﻤَﺎ ﻫﺬا اﻟﻠَّﻬﻮ ﻭاﻟﻐﺮﻭﺭ".
ወየውልህ! አንተ ቀብርህ ውስጥ በቀንዱ እስኪነፋ ድረስ ትታገታለህ። ከዚያም ወደ ጀነት ተሳፋሪ አልያም ወደ እሳት ተጎታች፣ ተዳሳችና ነፃ የሚወጣ አልያም እስረኛና የምትጠፈርህ ነህ! ታዲያ ይህ ሁሉ ዛዛታና ፌሽታ ስላቅና ደስታ ከየት ነው?

التبصرة (٢٣/٢)
598 viewsedited  10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ