Get Mystery Box with random crypto!

Ahlu Al Qur'an

የቴሌግራም ቻናል አርማ abdurahmansultan — Ahlu Al Qur'an A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abdurahmansultan — Ahlu Al Qur'an
የሰርጥ አድራሻ: @abdurahmansultan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 554
የሰርጥ መግለጫ

ኡማውን በዲኑ እውቀት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው የአቅማቸንን ያህል ለማገዝ ጥረት የምናደርግበት ቻናል ነው!!

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-10 00:14:07
በሀገራችን የመጀመሪያው ልዩ ዓለም አቀፍ የቁርአን ሒፍዝ ውድድር የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ስታዲየም

በሌሎች ሀገሮች አይተነው የተመኘነው እንደዚ አይነት ፕሮግራም በሀገራችን ለመጀመሪያ ግዜ ልዩ ዓለም አቀፍ የቁርአን ሒፍዝ ውድድር የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል። ከ56 ሀገራት በላይ ተወካዮች የሚሳተፋበት ታላቅ ዓለም አቀፍ የቁርአን ሒፍዝ ለመወዳደር ለመዳኘት ለመደገፍ ወደ ሀገራችን የተለያዩ እንግዶች እየገቡ ይገኛሉ።

ማንም መቅረት የሌለበት ድንቅ ፕሮግራም ነው ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን መግቢታ ትኬቶች በዳሽን ባንክ በሁሉም ቅርንጫፎች ያገኙታል።

የአንድ ሰው normal መግቢያ 500 ሲሆን vip 1000 ነው።

#እሁድን_በስቴድየም

share ይደረግ
82 views21:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 13:23:23
66 views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 07:26:49 https://vm.tiktok.com/ZMN1xWV1X/?k=1
103 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 20:54:40 ወገኖቻችን ምን እያደረጉ ነው ያሉት?

ወገኖቻችን የአልሞት ባይ ተጋዳይ መንፈራገጥ ላይ ናቸው። ቡጭሪያቸው ወዲያም ወዲህም ነው። ያገኙትን ይነከሳሉ፣ ያረፈደ ብልጠታቸው እስላሙን የጦስ ዶሮ አድርጎ በሴራ ለማስበላት ብዙ ሞክረው ቀላል በማይባል ደረጃ ተሳክቶላቸዋል።

ይዞ ሟችነት እንዲህ ነው! ያላቸው አማራጭ ሁለት ነው። የገርገራ (የጣዕረ ሞት) ጊዜን ማራዘም (Decreasing at a decreasing rate) ላይ መሰንበት! ከመሞት መሰንበት! አሊያም እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀልን መርህ አድርጎ ይዞ ሟችነት ላይ ምንችክ ማለት!!

ወዳጄ የክርስቲያን አክራሪነት እያስደነገጠህ ከሆነ አይግረምህ ነገሩ “ሀከዛ” ነው!

ግና መፍትሄው ምንድን ነው ካልከኝ አድምጠኝ።

የግሪቫንስ ፖለቲካ የሚባል አለ። የመጥፋት፣ የመረሳት ስጋት ያለባቸው አካሎች ወደ ተረትነት ከመቀየራቸው በፊት ማንኛውንም ነገር ያደርጋሉ። እሪሪሪታው እየየየው ይቀጥላል። ዓላማው መንፈሳዊ ሳይሆን ብሶተኛ፣ የተበዳይነት ስሜትን ያዳበረ በቀለኛ ኃይልን መሰብሰብ ብቻ ነው። ይህ ተወገርኩ ተቀጠቀጥኩ፣ ነደድኩ እየየው ለሚዲያ ማሳያ ይፈልጋል። በደሉ እውነተኛ ከሆነ እውነተኛ ታጋዮችን ያፈራል። ቤተ-ክርስቲያኗ ብትነጥፍ እንኳን እየተበደለች ከሆነ አላህ ከውስጧ በደልን የሚገፈትሩ ወንዶችን፣ ትውልዶችን ይፈጥራል። አላህ ሃይማኖትህን ሳይሆን መበደልህንና ጥረትህን ነው የሚመለከተው።

ግና እሪታውና ኡኡኡታው ማሳያ አልባ፣ ሀቅ የከዳው የሴራ ጩኸት ከሆነ ጊዜ ያከስመዋል። ግና በራሱ አቅም ማንሰራራት የተሳነው ያገኘው ጋር በመጋጨት፣ በመደቆስ፣ በመገፋት ውሥጥ እሮሮ የኳተረው አቅም ሆኖ ቀስ በቀስ ተመልሶ ለመምጣት “የጠላት ያለህ!” እያለ ይቦጭርሃል! ስለዚህ ወዳጄ እስከመጨረሻው ዝምብለህ ልታካትማቸው ከፈለግክ በፍጹም በፍጹም እትንካቸው፣ የመበደልን ጉልበት አትስጣቸው! ብቻ ይዘውህ እንዳይሞቱ ራስህን ከቻልክ ከጦስ ዶሮነት አግልል፣ ካልቻልክ ራስህን ተከላከል! ከዚያ ያለፈ ዝምምምምም በላቸው! ያኔ ልጆቻችን በተረት ተረት አሊያም ታሪክ መጽሀፍ ላይ ያውቋቸዋል። እነሱም የማይቀረውን ተፈጥሯዊ ሞታቸውን ከብዙ መንፈራፈር በኋላ ይሞታሉ። ያኔ የሮም ታሪክ ራሱን ይደግማል! ደወልና ደዋዩ ብቻ ይቀሩና ታርፋለህ!! እናም አትንካቸው! አጀንዳም አታድርጋቸው! ረስተሃቸው ዝምምም ብለህ በራስህ ላይ ሥራ!!
127 views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 20:54:40 የኛዎቹ ግን ሶሎሞናዊ ነን ብለው መንግሥትነትን ወረሱ፣ መንፈሳዊነት በነ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ በነላልይበላ ጊዜ ቀረና መንፈሳዊነትን እየሰበከ ዓለማዊነትን የሚኖረው፣ ገዳማትን እየተከለ ግና ገዳማትን የሚያረክሰው፣ ለፊውዳሊዝም ሥርዓቱ ፊውዳል ቤተ-ክህነትን የተከለው የአጼው ሥርዓት ነገሰ፣ ተጠናከረ። ሁሉም ነገር ወደ “መስቀል ጦርነት” ተባለና አያል መቶዎች አመታትን ያሳለፈ የጦርነት ታሪክን በአገራችንን ምድር ላይ ጻፈ! መንፈሳዊነትና ኦርቶዶክስነት ይጠጌ አይነኬ (asymptotic) ሊሆኑ ተዳረሱ። ይጠጋጋሉ ግና የማይነካኩ ሆኑ! ታላቋ ቤተ-ክህነት በአቡነ ተ/ሃይማኖት ፎርሙላ ፊውዳሊስት ሆነችና አረፈችው! ደጀሰላሞች መንፈሳዊነትን እየራቃቸው መጣና በጥላቻ ስብከት ተሞሉ!
ይህ መልሶ ግብን ሊያሳካ የሚችል ነፍጠኛ፣ አመጸኛ፣ አሸባሪ አደረጃጀትን እንጅ መንፈሳዊ ባለጽናትና ሩቅ አሳቢ ኤጀንቶችን አሳጣቸውና ዛሬ ነፍጠኛ ዲያቆናቱ እንደ አበደ ውሻ ተቅበዘበዙ!

ምን ተስፋ አስቆረጣቸው ?

ሁነኛ መንፈሳዊ የሆነ የአማኝ እጦት
ቤተ-ክህነቷና ቀሳውስቶቿ በታሪክ ውሥጥ በተለይም በአቢሲኒያ በአሃዝም በሚናም የበላይ ሆነው ኖረዋል። በተደጋጋሚ የአባላት ወይም የአማኝ መቀነስ ወይም የመጥፋት አደጋ አጋጥሟቸዋል። በድህረ ግራኝ በአቢሲኒያ ከአስሩ ዘጠኙ እስላም እንደሆኑባቸው ሁሉ አብዝተው ጽፈዋል። ግና እንዲህ ያለውን የአማኝ እጦት ስጋት በምን ፈቱት?

ዴሞግራፊ ሲሳሳብህ ዴሞግራፊህን (የህዝብ ብዛትህን) በሶስት መልኩ ታስተካክላለህ፣ ታሻሽላለህ። አንድም በመዋለድ፣ ሁለትም በአስተምህሮ ሶስትም በግድ ታጠምቃለህ። የኢትዮጵያ ኦ/ቤተክርስቲያን ሰዎች ምዕምኖቻቸው በብዛት እንዲወልዱ በማድረግ በማበረታታት ሥራ ላይ አይደሉም፣ ሙከራው ቢኖርም ምዕምኖቻቸውም ይህን በቀላሉ ሊፈጽሙላቸው አልቻሉም። ዲያቆናቱ ቀሳውስቱና መምህራኑ ቤተ-ክርስቲያኗንና አስተምህሮዋቿን በአገሪቱ ቋንቋዎች ሁሉ ለማስተማር ፈቃደኛ ሳይሆኑ ኖረዋል፣ ስብከቶቻቸው ትምህርቶቻቸው መንፈሳዊነትን ረስተው እሮሮ፣ የጥላቻ ቅስቀሳ፣ የአጼው ናፍቆት ትርክትና ትምክህት ከሆኑ ዘመናት አልፈዋል።

ስለዚህም እንደ ፕሮቴስታንቱና እንደ ሙስሊሙ ሃይማኖቱን ሰብከው በርካቶች የኢ/ኦ/ቤተክርስቲያንን እንዲቀላቀሉ ማድረግ አልተቻላቸውም። ሶስተኛው በግድ ማጥመቅ ዛሬ አይቻልም! ታቦት ይዞ ንጉስ ቀስቅሶ አንድን ህዝብ ወርሮ በግድ ማጥመቅና ማቁረብ ዛሬ አይቻልም፣ ነፍጠኛ ተከትሎ ደጃዝማችና ራስ አጅቦ ሄዶ አንድን ጎሳና ብሄር ከነመሬቱ መጸበልና ማጥመቅ ዛሬ በፍጹም አይታሰብም።

ስለዚህም በነፍጥና በአጼው ሥርዓት እያስፈራሩ በጉልበት ማጥመቀ ድሮ ቀርቷል ማለት ነው። ታዲያ በመዋለድ በስብከትና አስተምህሮ እንዲሁም በግድ በማጥመቅ አባላትን ወይም ምዕምንን ማብዛት ካልተቻላቸው በየቀኑ በፕሮቴስታንትና በሙስሊሙ አስተምህሮ ምክንያት የሚከዳቸውን አባላት እንዴት ማስቆም ባይችሉ መተካት እንዳለባቸው ግራ የገባቸው ወገኖቻችን ካገኙት ጋር መጋጨትን፣ የግሪቫንስ ፖለቲካ ታክቲክን፣ የጅምላ ጭፍጨፋና የሽብር ሂደትን መከተላቸው የሚጠበቅ አይሆንም?

ቤተ-ክርስቲያኗ በሲሶ መንግሥትነት ዘመኗም ሆነ ከዚያ ወዲህ የሰበሰበችው፣ ያካበተቸው ሀብት እጅጉን ብዙ ነው። ይህ ሀብት ትውልድ ቀረጻ ላይ አልዋለም! ሀብትና ሌጋሲን አስቀጣይ የበቃ የሰከነ መንፈሳዊ ትውልድ አልተዘጋጀም! በመጡባችሁ ስብከት የደነበረ እንጅ የሰከነ ትውልድን መፍጠር የማይችል መምህራን ተሰግስጎባታል።

ዛሬ በወረራም በቢሮክራሲ ላዕላይነት ሳቦታጅም ምክንያት እንዳሻት ኣከብታ የምትቆጣጠራቸው ቦታዎችና ውብ አብያተ ክርስቲያናት እንደ አውሮፓ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከመቶ አመታት በኋላ ለእስላሞች እየተከራዩ ረመዷን እንደማይሰገድባቸው እርግጠኛ መሆን አይቻልም!
እንደ ድሮው በኢትዮጵያ ስም እየማሉ የኢትዮጵያ ታሪኳና መልኳ ቤተ ክርስቲያኗ ትሆን ዘንድ ከመመኘት ያለፈ ማድረግ ዛሬ አልተቻለም።

በኢትዮጵያዊነት ካባ ሥር የተከለለው ምስጢር ሁሉ ዛሬ ተበትኖ አደባባይ ላይ ተበትኗል። አማራጭ ሲጠፋ ወደ አ*ማራ ክልል ስደቱ ተፋጥኗል። ከዚያም አሳደው አ-ማራ ሳይንት ሊያስገቧት የሚሯሯጡቱ ልጆቿ የቂል ጉዞ ላይ ናቸው።የበላይነትን ሲጠባ የኖረ እኩል ነህ ሲባል የተበደለ ይመስለዋልና እቡይ ምሁራኖቿ ከዘመን ጋር ሊያስታርቋት ከቶ አልተቻላቸውም! ስለዚህም ዛሬ ቤተ-ክርስቲያኗ ዓይኗ እያየ በሁለንተናዊ ተክለ ቁመናዋ ላይ አይደለችም! በስነ-ልቦና የተጠቂነት ልክፍትን እያወረሷት እንጅ ተተኪ ሃይልን እያዘጋጁላት አይደለምና!!

ምን ተስፋ አስቆረጣቸው?

አራት፡- የስልጣኔ ገደብ

በኢኮኖሚክስ ቲዮሪ ቶታል ፕሮዳክት ከርቭ የሚባል ከርቭ አለ። ይህ ከርቭ ምርታማነትና የምርት ግብአትን ምጣኔ ያሳያል። ሶስት ደረጃዎች አሉት መጀመሪያው increasing marginal returns ይባላል። በዚህ ስቴጅ በእያንዳንዷ ተጨማሪ ሀብት የተሻለ ተጨማሪ ጥቅም ወይም ምርት የምታገኝበት ነው። ግብአት በጨመርክ ቁጥር የበለጥ ምርት ወይም እድገት ታገኛለህ። ሁለተኛው እርከን Diminishing marginal returns ይባላል። በዚህ ግብአት በጨመርክ ቁጥር ምርትህ እድገትህ ያድጋል፣ ግን በግብአትህ ልክ ወይም ከዚያ በላይ አይደለም የምታመርተው። እድገትህ በዲክሪዚንግ ሬት ነው የሚያድገው።

ሶስተኛው ርከን ጠቅላላ ምርትህ የፈለግከውን ግብአት ብትጨምር ምንም ዓይነት እድገት የማያሳይበትና ከዚያም እንዲያውም ግብአት በጨመርክ ቁጥር እየከሰርክ የምትመጣበት ስቴጅ ነው። Negative marginal returns ይባላል። በዚህ ስቴጅ ውሥጥ ከገባህ አርጅተሃል፣ የሚጠብቅህ ሞት ነው። ከመጃጃት ከመሞት አትድናትም! ያለህ አማራጭ ሁለት ነው። ሞትህን ማዘግየት! ወድቀትህን ማንቀራፈፍ! Decreasing at a decreasing rate ላይ ለመቆየት መጣጣር፣ መፈራገጥ! ሞትህ ግን አይቀርም! ይህ የተፈጥሮ ህግ ነው። እንደ ቦረቅክ አትቀርም፣ ትጎለምሳለህ፣ ታረጃታለህ ትሞታታለህ!

ታዲያ ይህ ከወገኖቻችን ጋር ምን አገናኘው? ካላችሁኝ የሚያገናኘው ቤተ-ክርስቲያኗን ከትናንቷ ቤተ-ክርስቲያን አንጻር ስትታይ እዚህ አስከፊው Negative marginal returns እርከን ላይ መገኘቷ ነው። የሶሎሞናዊውን ሥርዓት ያመጣችው የአቡነ ተ/ሃይማኖቷ ቤተ-ክህነት ተራ ስርዓት ብቻ አይደለችም! ስልጣኔም እንጅ! የራሷ ባህል፣ ቋንቋ፣ ታሪክ፣ ከፍታና ዝቅታ፣ አስተዳደርና መንግሥት ያላት ስልጣኔ ነበረች!

የዓለምን ጥንታዊና አሁናዊ ስልጣኔዎች ላይ የሚያጠኑ ምሁራኖች እንዲህ ይላሉ። The average lifespan of those surveyed was 336 years ነው ይላሉ። እንደ Daron Acemoglu and James A. Robinson ትንታኔ ደግሞ የአንድ ስልጣኔ ቆይታ 800 ዓመታት ነው።

ይህን የዓለማችንን ተሞክሮ ይዘን የወገኖቻችንን የዘወትር ትዝታና (Golden age memory) እና ናፍቆት የሆነውን የሶሎሞናውያኑን (የደሴታውያኑን፣ የኤጼውን) ሥርዓት ስንገመግመው ከ1270 ጀምሮ ዛሬ ድረስ ወደ ሰባት መቶ አርባ አመት በላይ ሆኖታል። ይህ ሥልጣኔ ሰባት መቶ አመታት ከቆየ በኋላ በይፋ ተገርስሷል። አልሞት ባይ ተጋዳይ ሆኖ፣ የናፍቆት ሩጫ እያደረገ አርባ አመታትን አሳልፏል። ይሁን እንጅ እንደ ማንኛውም የዓለማችን ሲቪላይዜሽኖች ተፈጥሯዊ የሆነውን ሞት ከመሞት ግን በፍጹም አይቀርም! ደሴቷም ላትመለስ እየሰመጠች ናት!
71 views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 20:54:40 የዲያቆናቱ ቡጭሪያና ማለስለሻ መፍትሔው
★★★// //★★★

(እኔ ስፅፈው ያልፈራሁትን አንተ ምን አሰነፈህ?ጨክነህ አንበበውማ)

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት፣ መምህራን፣ ዲያቆናትና በሥሯ የተደራጁ ቡድኖች በተለየ መልኩ የጥላቻ ቅስቀሳ፣ ትንኮሳ፣ የሽብር ድርጊት፣ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ የፖለቲካ ውጥረት፣ ጠላት ማብዛት፣ ከመንግሥትም ከሁሉም ጋር መናከስን መጋጨትን ተያይዘውታል። የተቃጠልን ነደድን በሚል ራሳቸውንም ቤተክርስቲያኒቱንም፣ ሙስሊሙንም፣ ፕሮቴስታንቱንም፣ ኦሮሞውንም፣ ሱማሌውንም፣ ስልጤውንም ፣ መንግሥትንም ሰላም መንሳት የተለመደ ጠባያቸው ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ለምን ሆነ? ምንስ ይሻላል? ወንድሞቻችን እንዴት ሠላም ያግኙ የሚለው አሳሳቢ ነውና እንዲህ የሚያደርጋቸውን ሥረ-ነገር ማጥናቱ ተገቢ ነው።

ምክንያት አንድ ፡- ተስፋ መቁረጥ

በስነ-ልቦና ምሁራኖች ዘንድ frustration anger aggression theory የሚባል ሃይፓተሲስ አለ። በዚህ ቲዮሪ መሰረት ከአብዛኛው ወንጀል፣ አመጽ፣ ረብሻ፣ ቁጣ፣ ሁከት፣ ሽብርተኝነት እና ተናካሽነት ጀርባ ወይም የዚህ ሁሉ መነሻና ጅምር ተስፋ መቁረጥ ነው። ተስፋ የቆረጠ አካል ይዞ ሟች ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል እንዳበደ ውሻ ለካፊ ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል እረፍት የለውም ይቅበዘበዛል! ይንቀዠቀዣል! ካገኘው ጋር ይጋጫል! ይላተማል! ያገኘውን ይነክሳል! ይቧጨራል!

ተስፋ የቆረጠ አካል እሪሪሪታው ብዙ ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል መርሁ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ነው!”፣ ተስፋ የቆረጠ አካል ቡጭሪያው እንዲሁ አይደለም! ቡጭሪያው እንዳይሰምጥ ወይም ገደሉ ውሥጥ እንዳይገባ አንዲም መፈራገጡ፣ ሁለትም አንተን ይዞ ለመትረፍ የሚያደርገው ደመ-ነፍሳዊ መፈራገጡ፣ ሶስትም ጦሰኛ ሆኖ ይዞህ ሊሞት ገደል ሊገባ የሚያደርገው ደመ-አብራሪያዊ ባህሪው ነው። የቤተ-ክርስቲያኒቱ አንዳንድ ማህበራት፣ አንዳንድ ቀሳውስቶች፣ መምህራን፣ ዲያቆናቱና ህቡእ አደረጃጀቱን ወቅታዊ ተጨባጭ ይህ ነው።

ለመሆኑ ተስፋ ምን አስቆረጣቸው?

ከላይ የተጠቀሰው የጨለምተኝነት ቲዮሪ እንዲህ ይላል

Drive to Goal obstacle to a goal frustration Anger Aggression Catharsis

ግብ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ያለ አካል አንዳች ያልጠበቀው ዓይነት ወይም ሊያሸንፈው ያልቻለው እንቅፋት ሲያጋጥመው ተስፋ ይቆርጣል። ተስፋ የቆረጠ ሰው ደግሞ ይበሳጫል የተበሳጨ አካል ደግሞ ካገኘው ጋር ይጋጫል፣ ወንጀል ይሰራል፣ እብሪተኛ ይሆናል፡፡

ወገኖቻችን ግብ ነበራቸው፣ ለዚህ ግብ ሲሉ አርባ አመት ለፉ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ ብዙ ተደራጁ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ በ1960ዎቹ ወደ ኋላ የቀለበሷቸውን የያን ትውልድ አባል ጭምር ንሰሃ አስገብተው አተጉ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ ከፍተኛ ሪሶርስ በጅተው ተንቀሳቀሱ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ እጅግ አደገኛ አደረጃጀቶችንና ኤጀንቶችን በብዛት አመረቱ፣ ይህ ግብ በሴኪዩላሩ ፖለቲካዊ አመጽ መሳሪያነት ለስኬት ቀርቦ የተቀለበሰ ወይም ድንገት አቢዮቱ በሌላ የተቀማበት ግብ ነው። ይህ የወገኖቻችን ግብ ምንድን ነበር? ግባቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያንን ከተቻለ እንደ ቀድሞው በይፋ ሲሶ መንግሥት የማድረግ ግብ ነው።

የቤተ-ክርስቲያኒቱን የመንግሥት ህገ-መንግስት፣ የመንግሥት-ፍልስፍና፣ የአስተዳደር ሞራል፣ የአይዲዮሎጂ ምንጭ የማድረግ ምኞት ነው። የመንግሥትነትና የገዥነት ህጋዊነት (legtimacy) ምንጭ የማድረግ ግብ ምኞት ነው። ቤተ-ክርስቲያኒቱን የአገሪቱ ሲሶ ሀብት ባለቤት የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር ፍልስፍናና የበላይ የማድረግ ምኞት ነው። ይህ ካልሆነ ቤተ-ክርስቲያኒቱንና ኦርቶዶክሱን በተለየ መልኩ እውቅና የሚሰጥ፣ ተቀዳሚ ላዕላይ የሚያደርግ፣ ባለርስትና ቀዳማይ ሌላውን መጤና ባሪያ የሚያደርግ አሰራርና ህግ መልሶ እውን እንዲሆን የማድረግ ግብ ነው። ተምኔታዊው ግብ ሲጠቃለል ደሴቷንና የአጼውን ሥርዓት ዳግም የማንበር ምኞት ነው።

ይህን ግብ እውን ለማድረግ በሴኪዩላር ስም በተደራጁ አሃዳዊና ብሄርተኛ ድርጅቶች ጀርባ ሆነው የናፈቁትን ውሃ ሊጠጡ የኢህአዴግን መውደቅ አድፍጠው ሲጠብቁ የነበሩ ነበሩ። ለዚያም እጅጉን የተጉ ነበሩ።

ይህን ግብ ለምን መረጡት? ይህን በዚህ ዘመን ተግባራዊ ሊሆን የማይችል (infeasible system) ግብ የሙጥኝ ማለታቸው አንድም የኢ/ኦ/ቤተ ክርስቲያንና ምዕምኗን በተለየ መልኩ በባለርስትነት፣ በምርጥነት፣ በቀዳማዊነት፣ በላዕላይነት፣ በህጋዊ ወራሽነት ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ዴሞግራፊያዊና በተለይም ስነ-ልቦናዊ ጥቅምን በተለየ መልኩ ለቤተክርስቲያኗና ለምዕምኖቿ ሊያስከብር የሚችል ሌላ አንዳችም የአስተዳደር ሞዴል ሊኖር ባለመቻሉ ሲሆን ሁለትም ሩቅ ጠይቆ ብዙ ለማትረፍ በሚል ነው።
ይህ ግብ እጅግ ግዙፍ እክሎች (obstacle) አጋጥመውታል።

የመጀመሪያው እክል አጼ ሚናስን ያጋጠመው ግርታ (confusion) ነው። አጼ ሚናስና ተቀዳሚዎቹ ለዘመናት “እኛ ክርስቲያኖች ምርጦቹ የእግዚአብሔር ልጆች” ሆነው ሌሎቹ ያሏቸው ደግሞ “አህዛቦች፣ አዋሚዎች፣ ፈላሻዎች” ብለው ብዙ የአይዲዮሎጂ ስንቅና ትጥቅ ይዘው ሲታገሉ እንዳልኖሩ በሚናስ ዘመን ሃይማኖትን ሳይሆን ዘርን መሰረት ያደረገ የኦሮሞ ሃይል አጋጠመው። አፄ ሚናስን ጨነቀው፣ የታጠቀው የአይዲዮሎጂ ትጥቅ ለዚህ ዓይነቱ ተገዳዳሪ ሃይል በቅጡ የዳበረ ፎርሙላ አልነበረውም። እሱ በሃይማኖት እነሱ በዘር ሆነውበት ግራ ገባው።

ዛሬም ከላይ ያለውን ግብ ለማሳካት እየተፍጨረጨሩ የነበሩትና የህወሃት-ኢህአዴግን መውዴቅ ሲጠባበቁ የነበሩት ኃይሎች ያጋጠማቸው ከሚናስ የከፋ ነው። ወዲህ በብሄርተኝነት ፖለቲካ ጥርሱን ነቅሎ የደደረ የጎለመሰ የኦሮሞ ፖለቲካ፣ ወዲያ በካፒታሊስቶቹ የዘመናችን ባለ ሄጅሞኒዎች የሚዘወር የፕሮቴስታንት ሃይማኖት። ሶስትም የነቃ ሙስሊም ትውልድ! እነዚህ ዋነኞቹ እንቅፋቶች ቢሆኑም ወግ ላለማብዛት እናሳጥረው።

እነዚህ እክሎች ወይም እንቅፋቶች ወዳጆቻችንን ተስፋ መቁረጥ ውሥጥ ከተዋቸዋል። ተስፋ የቆረጠ አካል ደግሞ እንዳበደ ውሻ ያገኘውን ይለክፋል!

ምን ተስፋ አስቆረጣቸው ?

የመንፈሳዊነት ታሪክ እጦት

መንፈሳዊነት ጉልበት ነው። መንፈሳዊነት የትዕግስትና ጽናት እናት ነው። ወገኖቻችን ድህር አጼ ይኩኖ አምላክ ላይ ከመንፈሳዊነት ተናጥበዋል! ሮሃ ላይ በመንፈሳዊነትም በቁሳዊነትም ዓለምን ያስደመመውን የዛግዌውን መንግሥት “እኛ የንግሥቲቱ የሳባ ዘሮች የሰለሞን ትውልዶች ነን የጨዋይቱም የሳራ ዘሮች ነን” ብለው በሶሎሞናዊነት ስም የመጡት ኃይሎች እንደዚያ ዘመኑ የታላቋ የሮማን ካቶሊክ ብሎች እንደነ ቴምፕላራስ፣ እንደ ጥንተ ካባላ እርሾዎቹ፣ እንደ ተከታይ ፍሪሜሰንስ ሁሉ በኢትዮጵያችን የበቀሉ ህቡእ ኃይሎች ነበሩ። የአውሮፓዎቹ መንግሥትነትን ሊወርሱ ብዙ ዳከሩ ግና የቫቲካንን ኢንኪዩዚሽን ጽዋ እየጨለጡ እንደ አውሬም ታድነው አለቁ።
69 views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 07:38:49 https://vm.tiktok.com/ZML77px77/?k=1
94 views04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-10 19:26:51 «ሚዲያን መቆጣጠር ሀገርን መቆጣጠር ነው»
በአሕመዲን ጀበል
ክፍል አንድ


«በምድር ላይ እጅግ አደገኛው ነገር መገናኛ ብዙሃን(ሚዲያ) ነው።የብዙሃኑን አእምሮ ስለሚቆጣጠሩ ንፁሀንን ጥፋተኛ ፣ጥፋተኛውን ደግሞ ንፁህ የማድረግ አቅም አለው። ይህም ኃይል ነው።» (ማልኮም ኤክስ)


እንኳንስ በዚህ ዘመን ያኔ ጥንትም ቢሆን ኋላ ቀርና ልትወገድ ተገቢ በመሆኗ የሰጠመችውን ደሴት ከባህሩ ዉስጥ ፈልገው ዳግም ሊያቆሟት እየተጉ ያሉ «የሰመጠችው ደሴት ናፋቂዎች» እኔን «እንቅፋት ሆነብን» ብለው በማሰብ በማሳጣትና በማሸማቀቅ አፍ የሚያዘጉበት አንዳች ማስረጃ ብናገኝ ብለው ማስረጃ ፍለጋ ብዙ ለፍተዋል።እየለፉም ነው። እስካሁን አንዳች ለማጠልሸት የሚሆን ነገር በማጣታቸው ያለማስረጃ የማጠልሸቱ ጉዳይ በተለይ በሙስሊሙና ምክንያታዊ በሆኑት ክርስትያኖች ዘንድ ዳገት ሲሆንባቸው ዉንጀላቸውን በማስረጃ ማስደገፍ ከቻልን ብለው ብዙ ጥረዋል።እየጣሩም ይገኛሉ።

የግል ኢሜይሎቼን ከአዲስ አበባ አምስት ኪሎ፥ከካዛንቺስ፥ ከአሜሪካ፥ከጀርመንና ከዱባይ ሀገር በተደጋጋሚ ጊዜ ለመጥለፍ ሞክረዋል። ተንቀሳቃሽ ስልኬንም አሰርቀዋል (ዘመናዊውን አይፎን ስልኬን የሰረቀው አካል ስልኬ እጁ ላይ እንደገባ ወዲያው ከስልኩ ይልቅ በስልኩ ላይ ተከፍተው (Signin) ሆነው የነበሩ የማህበራዊ ሚዲያና የኢሜይል ፓስወርዶቼን ለመለወጥና የራሱ ለማድረግ ሲታገል እንዲያሳውቀኝ ለጥንቃቄ ያደረግኩት የሲስተሙ አላርም በሌላኘው ስልኬ ላይ «ፓስወርዶቹን ለመለወጥ የፈለግከው አንተ ነህን? » ሲል በጥያቄ እየተደረገ ያለውን ሙከራ አሳወቀኝ።እናም ጥረታቸውን ስንዝር ሳይጓዙ ተኮላሸ)። እስካሁን በዚህና በሌሎች መንገዶች የኢሜይልና የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶቼን ለመቆጣጠር ጥረዋል።

የፌስቡክ ገጼን ለማዘጋት ሞክረው ሳይሳካላቸው ሲቀር ጠልፈው ለመውሰድ ብዙ ጥረዋል።ለጊዜው እውነትነቱን ማረጋገጥ ባልችልም በሁለት ግለሰቦች አማካኝነት ሰዎቹ በመንግስት መዋቅር ዉስጥ ባሉ አባሎቻቸው በኩል የስልክ ግንኙነቶቼን ሲያደምጡ እንደነበር ተነግሮኛል። ይህ ሁሉ ልፋታቸው አንዳች የተጨበጠ ነገር አላስገኘላቸውም።

በኔ ላይ በሀሰት በሚያቀርቡት ዉንጀላ ላይ እንዲታመኑ ዘንድ ማሰረጃ ለማቅረብና ለማስረዳት እስከ ዛሬ በየትኛውም መድረክ ከተናገርኳቸው ንግግሮች መካከል አንዳች የድምጽ ወይም የቪዲዮ ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም። ስላልቻሉም ያለአንዳች ማስረጃ በስም ማጥፋት ዘመቻቸው ገፉበት።

የስም ማጥፋት ዘመቻን ከሚያካሂዱት አንዱ የሆነውን ግለሰብ በህግ አግባብ እንዲጠየቅልኝ ስል ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክስ ባቀርብም መርማሪው ፖሊስ ቃሌንና ማስረጃዎቼን ከተቀበለና ከመረመረ በኋላ «ጉዳዩ ያስከስሰዋል»ብሎ ተቀበለኝ። ቀጥሎም መዝገቡን «አጠናቅሬ ወደ ዐቃቢ ሕግ መርቼዋለሁ» ካለ ሁለት ዓመት ሊሞላው እየተቃረበ ቢሆንም ዛሬም ድረስ አንዳች የተደረገ ነገር የለም።ይህ ሁኔታ ፖሊሱ ቃል ሲቀበለኝ ስለግለሰቡ «እርሱ እኮ በማህበራዊ ሚዲያ በየእለቱ የሚናገረው አብዛኛው እኮ የሚከስ ካለ በወንጀል የሚያስከስስ ነው።» ያለኝ ነገር በአዕምሮዬ ላይ ደጋግሞ ያቃጭልብኛል።እውነትም «የሚከስ ካለ»።

በሰሞኑ በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ንጹሃን ሙስሊሞች ላይ ታቅዶበት የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት ሕዝበ ሙስሊሙን ሲያስቆጣና ጉዳዩ ወደ ተቃውሞ ሲያመራ የቆሙለትን አካል ወንጀል ለመደበቅ፥ሙስሊሞችን መልሰው በመወንጀልና በማጠልሸትና አጀንዳ ለማስቀየስ መንገድ ሲፈልጉ የነበሩት የሰጠመችው ደሴት ናፋቂዎች አህመዲን «የሚዲያ ስልጠና ሰጠበት» ያሉትን ሰነድ ተጠቅሞ ማወናበድ ጠቃሚ መስሎ ታያቸው።ወዲያው ከዚህ በፊት በሞጣው የሽብር ጥቃት «ተጠያቂው አሕመዲን ጀበል ነው።» ብለው ለማጠልሸት እንደሞኩሩት ሁሉ ጎንደር በሙስሊሞች ላይ የተፈጸመውንም የሽብር ጥቃትም «አሕመዲን ጀበል ለሽብር ዓላማ ሲያሰለጥናቸው ከነበሩት ሕቡዕ ቡድን አባላት በኩል ያስፈጸመው እርሱ ነው ።» በሚል ቅኝት «ይኀው ያሰለጠነበት ሚስጥራዊ ሰነድ» ብለው ወደ ሚዲያዎቻቸው ብቅ አሉ። አባላቶቻቸውም በማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው ተቀባበሉት።ባለፉት ሁለት ሳምንታት የነርሱ መደበኛና ማህበራዊ ሚዲያዎች መሪ ቃል «አሕመዲን ጀበል» ሆኖ ሰነበተ።

ለሰጠመችው ደሴት አንዴ በሃይማኖት፣ሌላ ጊዜ ደግሞ በብሄር፣ሲያሻቸው ደግሞ በኢትዮጵያዊነት ስም እንደየአስፈላጊነቱ በተለያዩ ማሊያዎች የሚጫወቱት ወገኖቻቸው አንዳንዶቹ ሰነዱን በማጋራት፥ ሌሎቹ ደግሞ «አሕመዲን ጀበል ያሰማራቸው አካለት ቤተክርስቲያን አቃጠሉ።» እያሉም ተቀባበሉ። በሚዲያዎቻቸው በኩል «አሕመዲን ለሕግ ይቅረብልንም» አሉ።እዚህ ላይ ግልጽ ለማድረግ የምፈልገው እኔ ለሕግ እንድቀርብ የሚፈልግና «አሕመዲን ጀበል ወንጀል ሰርቷል።ማሰረጃ አለኝ።» ብሎ የሚያምን የትኛውም አካል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያለማስረጃ ስሜን በማጠልሸት ሳይሆን «አለኝ» የሚለውን ማስረጃውን ይዞ ወደ ሕግ እንዲሄድ አበረታታዋለሁ።

እነርሱ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ የተቀባበሏቸው ሰነዶች በግልጽ እንደሚጠቅሱት ስልጠናው “የሚዲያና አክቲቪዝም” ነው። በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው ሰነድ አንድም ስፍራ «በአህመዲን ጀበል የተዘጋጀ» የሚል የለበትም። እንዲያውም ሰነዱ እንደሚያሳየን ጽሁፉን ያዘጋጁት ስዎች ጽሑፉ የጻፉት ለአህመዲን እንዲደርስ መሆኑን «ለአህመዲን ጀበል» ሲል ሰነዱ ይገልጻል።እነርሱ ሕዝቡን እንደናቁት ሕዝቡ ደብዳቤ ሲጻጻፍ «ከእገሌ… ለእገሌ» የሚለውን የላኪንና ተቀባይን ማንነት ገላጭ ቃላትን የማያውቅ ባለመሆኑ ብዙዎች ይህን ነጥብ ብቻ እያነሱ ሞግተዋቸዋል።

ሰነዱም አንድም ስፍራ ላይ እነርሱ ሊያሳዩ የፈለጉት ሚስጢራዊ ወይም የተንኮል ነገር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚገልጽ አንዳች ነገር የለበትም።ሰነዶቹን አያይዘው በማሳየት በሰነዶቹ ዉስጥ የሌለና የማይገናኝ ርዕስ ሰጥተው ሚዲያን ተጠቅሞ ተራ የዉንብድና ተግባር ፈጸሙ። ጀርባዬም፥ ተግባሬም ሆነ ሂደቶቹ ፍጹም ህጋዊና ሰላማዊ ስለሆነ እንኳንስ በዚህ ተራ የቀሽም ፕሮፓጋንዳ እኔን ልታሸማቅቁ ይቅርና እንደቁም ነገር ወስጄ ምላሽ ለመስጠት ጊዜ የማባክንበት አልነበረም።

አንዳንድ ሙስሊምና ክርስቲያን ወዳጆቼም «ንጹሕነትህ ላይ ፍጹም እርግጠኞች ብንሆንም በሚዲያቸው ስለተቀባበሉት የዋሆች ሰለባ እንዳይሆኑ ስትል የሆነ ነገር ብትልበት» ብለው ስለጠየቁኝ እንዲሁም ጊል ከርቲማንቺ«ፕሮፓጋንዳ እንደ ሄሮይን አደገኛ ነው። ሰዎች ሳያጤኑት ሙሉ የማሰብ አቅማቸውን ያሟሟል።›› እንዳለው የሰዎቹን ሴራና የፕሮፓጋንዳን ምንነት በቅጡ ያልተረዱ የዋሆችን ለመታደግ ስል በጉዳዩ ላይ ጥቂት ነገር ለማለት ወደድኩ።

እርግጥ ነው እንኳንስ «ሚስጥራዊ» የሚል ታፔላ(ርዕስ) የተለጠፈለት ሰነድ ተያይዞ አይደለም ያለምንም ማስረጃ የተጻፈውን ብቻ ለማመን ቅርብ የሆኑ ስለሚዲያ ቁማር የማያውቁ ወይም በስከዚህ ቀደሙ ሚዲያውን በተቆጣጠሩት አካላት አማካኝነት በተሠሩ ፕሮፓጋንዳዎች ምክንያት አሕመዲን ላይ ጥርጣሬ ቢጤ የገባቸው ጥቂት የዋሆች ሊታለሉ እንደሚችሉ እሙን ነው። ምክንያቱም ስቴፈን ሞሊኒዬክስ እንዳለው‹‹የፕሮፓጋንዳ አጠቃላይ ዓላማ ግልፅ የሆነውን ነገር ደብዛዛ አልያም አስፀያፊ አድርጎ ማቅረብ ነው።›› ነውና።
98 views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 06:00:26 https://vm.tiktok.com/ZMLWQLgSQ/
90 views03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 01:50:35
የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሸኽ ሰይድ ስለጎንደሩ ጭፍጨፋ ጉዳት፣ መንስዔና በክልሉ ስላለው የሙስሊም በደል ትናንት በዒድ ሰላት ባደረጉት ንግግር እውነታውን ተናግረዋል።

T.me/ahmedin99
113 views22:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ