2022-05-19 20:54:40
የዲያቆናቱ ቡጭሪያና ማለስለሻ መፍትሔው
★★★// //★★★
(እኔ ስፅፈው ያልፈራሁትን አንተ ምን አሰነፈህ?ጨክነህ አንበበውማ)
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት፣ መምህራን፣ ዲያቆናትና በሥሯ የተደራጁ ቡድኖች በተለየ መልኩ የጥላቻ ቅስቀሳ፣ ትንኮሳ፣ የሽብር ድርጊት፣ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ የፖለቲካ ውጥረት፣ ጠላት ማብዛት፣ ከመንግሥትም ከሁሉም ጋር መናከስን መጋጨትን ተያይዘውታል። የተቃጠልን ነደድን በሚል ራሳቸውንም ቤተክርስቲያኒቱንም፣ ሙስሊሙንም፣ ፕሮቴስታንቱንም፣ ኦሮሞውንም፣ ሱማሌውንም፣ ስልጤውንም ፣ መንግሥትንም ሰላም መንሳት የተለመደ ጠባያቸው ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ለምን ሆነ? ምንስ ይሻላል? ወንድሞቻችን እንዴት ሠላም ያግኙ የሚለው አሳሳቢ ነውና እንዲህ የሚያደርጋቸውን ሥረ-ነገር ማጥናቱ ተገቢ ነው።
ምክንያት አንድ ፡- ተስፋ መቁረጥ
በስነ-ልቦና ምሁራኖች ዘንድ frustration anger aggression theory የሚባል ሃይፓተሲስ አለ። በዚህ ቲዮሪ መሰረት ከአብዛኛው ወንጀል፣ አመጽ፣ ረብሻ፣ ቁጣ፣ ሁከት፣ ሽብርተኝነት እና ተናካሽነት ጀርባ ወይም የዚህ ሁሉ መነሻና ጅምር ተስፋ መቁረጥ ነው። ተስፋ የቆረጠ አካል ይዞ ሟች ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል እንዳበደ ውሻ ለካፊ ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል እረፍት የለውም ይቅበዘበዛል! ይንቀዠቀዣል! ካገኘው ጋር ይጋጫል! ይላተማል! ያገኘውን ይነክሳል! ይቧጨራል!
ተስፋ የቆረጠ አካል እሪሪሪታው ብዙ ነው! ተስፋ የቆረጠ አካል መርሁ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ነው!”፣ ተስፋ የቆረጠ አካል ቡጭሪያው እንዲሁ አይደለም! ቡጭሪያው እንዳይሰምጥ ወይም ገደሉ ውሥጥ እንዳይገባ አንዲም መፈራገጡ፣ ሁለትም አንተን ይዞ ለመትረፍ የሚያደርገው ደመ-ነፍሳዊ መፈራገጡ፣ ሶስትም ጦሰኛ ሆኖ ይዞህ ሊሞት ገደል ሊገባ የሚያደርገው ደመ-አብራሪያዊ ባህሪው ነው። የቤተ-ክርስቲያኒቱ አንዳንድ ማህበራት፣ አንዳንድ ቀሳውስቶች፣ መምህራን፣ ዲያቆናቱና ህቡእ አደረጃጀቱን ወቅታዊ ተጨባጭ ይህ ነው።
ለመሆኑ ተስፋ ምን አስቆረጣቸው?
ከላይ የተጠቀሰው የጨለምተኝነት ቲዮሪ እንዲህ ይላል
Drive to Goal obstacle to a goal frustration Anger Aggression Catharsis
ግብ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ያለ አካል አንዳች ያልጠበቀው ዓይነት ወይም ሊያሸንፈው ያልቻለው እንቅፋት ሲያጋጥመው ተስፋ ይቆርጣል። ተስፋ የቆረጠ ሰው ደግሞ ይበሳጫል የተበሳጨ አካል ደግሞ ካገኘው ጋር ይጋጫል፣ ወንጀል ይሰራል፣ እብሪተኛ ይሆናል፡፡
ወገኖቻችን ግብ ነበራቸው፣ ለዚህ ግብ ሲሉ አርባ አመት ለፉ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ ብዙ ተደራጁ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ በ1960ዎቹ ወደ ኋላ የቀለበሷቸውን የያን ትውልድ አባል ጭምር ንሰሃ አስገብተው አተጉ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ ከፍተኛ ሪሶርስ በጅተው ተንቀሳቀሱ፣ ለዚህ ግብ ሲሉ እጅግ አደገኛ አደረጃጀቶችንና ኤጀንቶችን በብዛት አመረቱ፣ ይህ ግብ በሴኪዩላሩ ፖለቲካዊ አመጽ መሳሪያነት ለስኬት ቀርቦ የተቀለበሰ ወይም ድንገት አቢዮቱ በሌላ የተቀማበት ግብ ነው። ይህ የወገኖቻችን ግብ ምንድን ነበር? ግባቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያንን ከተቻለ እንደ ቀድሞው በይፋ ሲሶ መንግሥት የማድረግ ግብ ነው።
የቤተ-ክርስቲያኒቱን የመንግሥት ህገ-መንግስት፣ የመንግሥት-ፍልስፍና፣ የአስተዳደር ሞራል፣ የአይዲዮሎጂ ምንጭ የማድረግ ምኞት ነው። የመንግሥትነትና የገዥነት ህጋዊነት (legtimacy) ምንጭ የማድረግ ግብ ምኞት ነው። ቤተ-ክርስቲያኒቱን የአገሪቱ ሲሶ ሀብት ባለቤት የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር ፍልስፍናና የበላይ የማድረግ ምኞት ነው። ይህ ካልሆነ ቤተ-ክርስቲያኒቱንና ኦርቶዶክሱን በተለየ መልኩ እውቅና የሚሰጥ፣ ተቀዳሚ ላዕላይ የሚያደርግ፣ ባለርስትና ቀዳማይ ሌላውን መጤና ባሪያ የሚያደርግ አሰራርና ህግ መልሶ እውን እንዲሆን የማድረግ ግብ ነው። ተምኔታዊው ግብ ሲጠቃለል ደሴቷንና የአጼውን ሥርዓት ዳግም የማንበር ምኞት ነው።
ይህን ግብ እውን ለማድረግ በሴኪዩላር ስም በተደራጁ አሃዳዊና ብሄርተኛ ድርጅቶች ጀርባ ሆነው የናፈቁትን ውሃ ሊጠጡ የኢህአዴግን መውደቅ አድፍጠው ሲጠብቁ የነበሩ ነበሩ። ለዚያም እጅጉን የተጉ ነበሩ።
ይህን ግብ ለምን መረጡት? ይህን በዚህ ዘመን ተግባራዊ ሊሆን የማይችል (infeasible system) ግብ የሙጥኝ ማለታቸው አንድም የኢ/ኦ/ቤተ ክርስቲያንና ምዕምኗን በተለየ መልኩ በባለርስትነት፣ በምርጥነት፣ በቀዳማዊነት፣ በላዕላይነት፣ በህጋዊ ወራሽነት ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ዴሞግራፊያዊና በተለይም ስነ-ልቦናዊ ጥቅምን በተለየ መልኩ ለቤተክርስቲያኗና ለምዕምኖቿ ሊያስከብር የሚችል ሌላ አንዳችም የአስተዳደር ሞዴል ሊኖር ባለመቻሉ ሲሆን ሁለትም ሩቅ ጠይቆ ብዙ ለማትረፍ በሚል ነው።
ይህ ግብ እጅግ ግዙፍ እክሎች (obstacle) አጋጥመውታል።
የመጀመሪያው እክል አጼ ሚናስን ያጋጠመው ግርታ (confusion) ነው። አጼ ሚናስና ተቀዳሚዎቹ ለዘመናት “እኛ ክርስቲያኖች ምርጦቹ የእግዚአብሔር ልጆች” ሆነው ሌሎቹ ያሏቸው ደግሞ “አህዛቦች፣ አዋሚዎች፣ ፈላሻዎች” ብለው ብዙ የአይዲዮሎጂ ስንቅና ትጥቅ ይዘው ሲታገሉ እንዳልኖሩ በሚናስ ዘመን ሃይማኖትን ሳይሆን ዘርን መሰረት ያደረገ የኦሮሞ ሃይል አጋጠመው። አፄ ሚናስን ጨነቀው፣ የታጠቀው የአይዲዮሎጂ ትጥቅ ለዚህ ዓይነቱ ተገዳዳሪ ሃይል በቅጡ የዳበረ ፎርሙላ አልነበረውም። እሱ በሃይማኖት እነሱ በዘር ሆነውበት ግራ ገባው።
ዛሬም ከላይ ያለውን ግብ ለማሳካት እየተፍጨረጨሩ የነበሩትና የህወሃት-ኢህአዴግን መውዴቅ ሲጠባበቁ የነበሩት ኃይሎች ያጋጠማቸው ከሚናስ የከፋ ነው። ወዲህ በብሄርተኝነት ፖለቲካ ጥርሱን ነቅሎ የደደረ የጎለመሰ የኦሮሞ ፖለቲካ፣ ወዲያ በካፒታሊስቶቹ የዘመናችን ባለ ሄጅሞኒዎች የሚዘወር የፕሮቴስታንት ሃይማኖት። ሶስትም የነቃ ሙስሊም ትውልድ! እነዚህ ዋነኞቹ እንቅፋቶች ቢሆኑም ወግ ላለማብዛት እናሳጥረው።
እነዚህ እክሎች ወይም እንቅፋቶች ወዳጆቻችንን ተስፋ መቁረጥ ውሥጥ ከተዋቸዋል። ተስፋ የቆረጠ አካል ደግሞ እንዳበደ ውሻ ያገኘውን ይለክፋል!
ምን ተስፋ አስቆረጣቸው ?
የመንፈሳዊነት ታሪክ እጦት
መንፈሳዊነት ጉልበት ነው። መንፈሳዊነት የትዕግስትና ጽናት እናት ነው። ወገኖቻችን ድህር አጼ ይኩኖ አምላክ ላይ ከመንፈሳዊነት ተናጥበዋል! ሮሃ ላይ በመንፈሳዊነትም በቁሳዊነትም ዓለምን ያስደመመውን የዛግዌውን መንግሥት “እኛ የንግሥቲቱ የሳባ ዘሮች የሰለሞን ትውልዶች ነን የጨዋይቱም የሳራ ዘሮች ነን” ብለው በሶሎሞናዊነት ስም የመጡት ኃይሎች እንደዚያ ዘመኑ የታላቋ የሮማን ካቶሊክ ብሎች እንደነ ቴምፕላራስ፣ እንደ ጥንተ ካባላ እርሾዎቹ፣ እንደ ተከታይ ፍሪሜሰንስ ሁሉ በኢትዮጵያችን የበቀሉ ህቡእ ኃይሎች ነበሩ። የአውሮፓዎቹ መንግሥትነትን ሊወርሱ ብዙ ዳከሩ ግና የቫቲካንን ኢንኪዩዚሽን ጽዋ እየጨለጡ እንደ አውሬም ታድነው አለቁ።
69 views17:54