2022-12-19 11:51:51
*ነፍስህን ይፈልጓታል*
*መልካም ንባብ!*
*ምስጢሩን ይግለጥልን*
(ሉቃ 12 )
------------
16 *ምሳሌም ነገራቸው እንዲህ ሲል፦ አንድ ባለ ጠጋ ሰው እርሻ እጅግ ፍሬያም ሆነችለት።*
17 *እርሱም፦ ፍሬዬን የማከማችበት ስፍራ አጥቻለሁና ምን ላድርግ? ብሎ በልቡ አሰበ።*
18 **እንዲህ አደርጋለሁ፤ ጐተራዬን አፍርሼ ሌላ የሚበልጥ እሠራለሁ፥ በዚያም ፍሬዬንና በረከቴን ሁሉ አከማቻለሁ፤*
19 *ነፍሴንም፦ አንቺ ነፍሴ፥ ለብዙ ዘመን የሚቀር ብዙ በረከት አለሽ፤ ዕረፊ፥ ብዪ፥ ጠጪ፥ ደስ ይበልሽ እላታለሁ አለ።**
20 *እግዚአብሔር ግን፦ አንተ ሰነፍ፥ በዚች ሌሊት ነፍስህን ከአንተ ሊወስዱአት ይፈልጓታል፤ ይህስ የሰበሰብኸው ለማን ይሆናል? አለው።*
21 *ለራሱ ገንዘብ የሚያከማች፥ በእግዚአብሔር ዘንድም ባለ ጠጋ ያልሆነ እንዲህ ነው።*
ይገርማል! ይህን ታሪኩ የተነገረለት ሰው ሁሉ ነገር የተ ሳካለት ትርፋማ ሰው፣ እርሻው እጅግ ፍሬያማ የሆነችለት ሰው: ብሎ ነው ጌታችን የገለጠው።
እናም ይህ ሰው እጅግ እጅግ እጅግ በጣም ትርፋማ ነበር።
አሁን ወደ ሜዳ ወጥቶ ከትርፋማነቱ የተነሳ ደስታውን መ ቆጣጠር አቅቶት ብቻውን ያወራ ጀመር፦
*ጐተራዬን አፍርሼ ሌላ የሚበልጥ እሠራለሁ፥ በዚያም ፍሬዬንና በረከቴን ሁሉ አከማቻለሁ*
*ነፍሴንም፦ አንቺ ነፍሴ፥ ለብዙ ዘመን የሚቀር ብዙ በረከት አለሽ፤ ዕረፊ፥ ብዪ፥ ጠጪ፥ ደስ ይበልሽ እላታለሁ አለ* ።
*ይገርማል! ሰውየው ሥራ መስራቱ መልካም፣ ትርፋማ መሆኑ መልካም ነበር: ምን ያደርጋል! መመጻደቁ እና ነፍሱን መርሳቱ አከሰረው እንጂ።*
*በሀሳቡ እንኳን እግዚአብሔር ከሰጠው ፍሬ ላይ አስራት ሊያወጣ አላሰበም፣ መንገድ ላይ ለወደቁት ችግረኞችም አላሰበም፣ለድሆች ዘመዶቹም አካፍላለሁ አላለም...በቃ ሀሳቡ ሌላ መጨመር ...እና ነፍሴ ብይ፣ ጠጭ እያለ ስለ ምግብ እና መጠጥ ሆኖ ነበር!*
*ይህን ሰው የመሰሉ ብዙዎች ዛሬም ድረስ በየሰፈሩ አሉ። አንዱን ይዘው በተሰጣቸው ሳያመሰግኑ፣ የእግዚአብሔርን አስራት ሳያወጡ ሌላው የሚያምራቸው...ሀሳብ ንግግራቸው ስለ ራሳቸው ብቻ ለዚያውም ስለ ሥጋ ብቻ የሆነ....ከዚህ ይሰውረን።*
*እናም ስለሚሰራው ጎተራ፣ ስለሚበላው ምግብ፣ ስለሚጠጣው መጠጥ እያሰበ ሲደሰት: በዚያችው ደቂቃ እግዚአብሔር መጣ፣ ነፍስህ በዚህች ሌሊት ትወሰዳለች አለው። ጨምሮም ይህ ያጥራቀምከው ሁሉ ለማን ይሆናል???? አለው። ተናግሮም አልቀረ ነፍሱን በዚያችው ቅጽበት ወሰዳት!*
*የዘራውን ሳያጭ ድ: ያከማቸውን ሳይበላ: የቀዳውን ሳይጠጣ በሞት ተነጠቀ። የምድሩንም የሰማዩንም አጣ። እኔ ጀግናው! እኔ ትርፋማው! ...ሲል የነበረው ሰው ከሰረ! እግዚአብሔር አምላካችን ከዚህ ይሰውረን!*
*ወገኖቼ ሁሉ ያልፋል። በተሰጠን ፍሬ እግዚአብሔርን እናክብርበት። እርሱ እግዚአብሔር ከሰጠን ላይ ለእርሱ ለእግዚአብሔር አስራት እናውጣ።ቤተ ክርስቲያንን እናስባት! በየስፍራው በግፍ ተፈናቅለው፣ ጎዳና የወደቁትን ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን፣ ልጆቻችንንም እናስባቸው። በተሰጠን ደግሞ እናመስግን ለሌሎች ማካፈልን፣ ድሆችን ማሰብን ህይወታችን እናድርግ። ለብዙ ዘመን የሚበቃኝ አለኝ ልብላ ልጠጣ እያልን እንደዚህ ሰው እንዳንከስር በማስተዋል እንኑር። በዚህች ሌሊት ነፍስህን እወስዳታለሁ ተብለን ድንገት ወደ መሬት ከመሄዳችን በፊት እናስብበት: አደራ! መንፈሳዊነት ይህ ነውና።*
*የመስቀለ ኢየሱስ በረከት በየቤታችን ይግባ።*
*ብሩህ ቀን*
110 viewsנְתַנְאֵל, 08:51