Get Mystery Box with random crypto!

❤️ የስነ–ልቦና ምክር (የተውበት እባዎች😭😭]

የቴሌግራም ቻናል አርማ abdulhakemohammed — ❤️ የስነ–ልቦና ምክር (የተውበት እባዎች😭😭]
የቴሌግራም ቻናል አርማ abdulhakemohammed — ❤️ የስነ–ልቦና ምክር (የተውበት እባዎች😭😭]
የሰርጥ አድራሻ: @abdulhakemohammed
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.99K
የሰርጥ መግለጫ

1, መስራት ባለብህ ሰዓት ካልሰራህ መሳቅ ባለብህ ሰዓት
ታለቅሳለህ
2, ወጀል፣ጭንቀት፣ሀዘን፣ተስፍመቁረጥ፣
3, የስነልቦና ምክር እሰጣለን ከወንጀል መላቀቅ ላቃታቹ የጨነቃቹ ምታማክሩት አታቹ ችግር ውስጥ ያላቹ ኑ እንመካከር አማክሩን
4, ደስታን ፍለጋ
5, @nesihatewba በውስጥ መስመር ያውሩን

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-27 20:31:57 ጥያቄ ሴት ልጅ ባሏን ግንኙነት እናድርግ

#ሴት ልጅ #ባሏን ግንኙነት እናድርግ ማለት ትችላለች ወይ

መልሱ አዎ ሴት ልጅ ባሏን ግንኙነት እናድርግ ማለት ትችላለች ዛሬ ዛሬ አንዱ የትዳር መፍታት ምልክቱ ይሄ ነው ቧል በስራ በምን ደክሞ ይመጣና የራሱን ስሜት እጂ የሚስቱን ስሜት አይረዳም እሱ ከፈለገ ነይ ይላታል ካልፈለገ ዝም ይላል በዚህ ምክንያት

ብዙ ወንዶች ከሚስቶቻቸው ግንኙነት ሳያደርጉ ሳምንት ፣ ወራት ያሳልፍሉ በዚህ ምክንያት ሚስት ከባሏ ምትፈልገውን ነገር ስታጣ ወደ ሌላ ወድ ወደ ሀራም ወደ ዝሙት የመሄድ ቻንሷ የሰፍ ነው

በዚህ ምክንያት ትዳራቸው ይፈርሳል ከሌላ ወንድ አየዋት እያለ ወደ ፍቺ ይቸኩላል

ሲጀመር አንተ መቼ ሀቋን ጠበክ በወር በሳምንት አንዴ እያደረክ እሷ ስትጠይቅህ እቢ ማለት ወጀል መሆኑ ታውቃለህ አስብበት

በዚህ ጉዳይ የተፈተናቹ ሴቶች መፍትሄ ለመፈለግ ጣሩ ሚስጥራቹን ለሚጠብቅ ሰው አማክሩ ዲኑ ሚለው 4 ወር ድረስ ካላደረገ ግንኙነት እዲያደርግ ተጠይቆ እቢ ካለ መጨረሻው ፍቺ ነው


by ኢብኑ ሙሀመድ (አ/ሀቅ)

የስነ–ልቦና ምክር ለሙስሊሙ ኡማ
@Abdulhakemohammed
@Abdulhakemohammed
817 viewsWell Com ( ነጃሺ ማርኬት), edited  17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 14:36:30 አግብቼው አሰልመዋለው

ብዙ ጊዜ አንዳንድ ሴቶች በስራ፣ በት/ቤት፣ በሰፈር በተለያየ አጋጣሚ ሙስሊም ያልሆነ ወንድ ይቀርቡና ጓደኛ ከመሆን አልፈው ይዋደዳሉ አቤት ፀባዩ ፣ መጠጥ አይጠጣ፣ ለስልምና ክብር አለው ሌላም ሌላም ይላሉ ልንጋባነውም ይላሉ ተይ ይቅርብሽ አይቻልም ስትባል

የተጋባን ለት ሸሀዳ ይይዛል ወይ ከተጋባን እሰልማለው እያሉ ያታልላኩ ብዙ ዎቹ የሰርጉ ቀን ሸሀዳ ይይዛሉ በነገው ለት ይከፍራሉ መጠጥ ቤት ጭፈራ ቤት፣ በቤቱ መዝሙር መክፈት ሌላም ሌላም ያደርጋሉ

እና እህቴ ማግባት ከፈለግሽ እሰልማለው ካለ
ቀድሞ ሰልሞ፣ እስልምናውን በደንብ አውቆ፣ ፆም ፁሞ፣ ዘካ ከወጀበበት አውጥቶ ፣ 5 ወቅት ሰላቱ ሰግዶ ሲጠነክር ታገቢዋለሽ

አለበለዚያ ወላሂ ካፊር ከምታገቢ ሳታገቢ ብትቀሪ ላቺ በላጭ ነው ወንጀልም ነው ካገባሽ እና አደራ አደራ አደራ
እኔ ብዙ ጊዜ የሚያናደኝ እና የሚያበሳጨኝ የጠላቶቼ ንግግር ሳይሆን የወዳጆቼ ዝምታ ነው።

የስነ–ልቦና ምክር ለሙስሊሙ ኡማ
@Abdulhakemohammed
@Abdulhakemohammed
1.1K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), edited  11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 04:36:28 ቢስሚላህ አዲስ ጉዞ ለ #1444 ረመዳን

እኔ በቀድር አምኛለው እምነቴም ነው በነዚ 10 የመጨረሻዎቹ ቀን ውስጥ 1 ቀን አለ እሱም ለይለትል ቀድር ነው

በዛ ቀን እስከሚመጣው አመት ድረስ በአንድ ሰው በአንድ ሀገር ላይ የሚደርሰውን ሁሉ ይወርዳል የተፃፈልን ሙሉ ነገር ይከሰታል

እስከሚመጣው የረመዳን 1444 ተኛው ድረስ በዚ አመት ምን ይፈጠራል?

ማን ያገባል ፣ ማን ይፍታል ፣ ማን ይሞታል ፣ ማን ይወለዳል ፣ ማን ሀብታም ይሆናል ማን ድሀ ይሆናል

ሀገር ሰላም ትሆናለች ወይስ ችግር ይኖራል ረሀብ ይፈጠራል ወይስ ኑሮ ይረክሳል

ማን ቤት ሀዘን ይፈጠራል ማን ቤት ደስታ ይኖራል ማን ይሞታል ማን ይወለዳል

ለነዚ ጥያቄ ሁሉ እኔም እናተም በዚ አመት ምን ይግጠመን ምን ይፃፍልን ምን ትሁን ማናችንም አናቅም

ብቻ በዱአ አላህ መልካሙን ሁሉ የተሻለውን ሁሉ ይግጠመን ረመዳናችን ይቀበለን የተፃፈውን ሲገጥመን ሲከሰትብን ከአላህ መሆኑ ቀደር መሆኑ አምነን ሰብር እናድርግ በአላህም እንመን

ወይ ደስታ ፣ ወይ ሀዘን አይቀርም እና ተዘጋጁ በለይለቱል ቀድር ቀን በየአመቱ ሚከሰቱት ሚፈጠሩት ሚከናወኑት ሁሉ ወደ ምድር ትዛዝ ይወርዳል

ኸይሩን ወፍቀን አሚን የተሻለው ከኛ በላይ አዋቂ ነህ እና

ቢስሚላህ ለሚቀጥለው የረመዳን 1444 ተኛ እዲያደርሰን በሰላም ተመኘው

አዲስ ጉዞ በአላህ ስም እጀምራለው

የናተው ወድም ኢብኑ ሙሀመድ ( አ/ሀቅ)

የስነ–ልቦና ምክር ለሙስሊሙ ኡማ
@Abdulhakemohammed
@Abdulhakemohammed
1.3K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), edited  01:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 04:25:40
1.4K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), 01:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 14:07:09 ሼር በማድረግ ለሁሉም ያዳርሱ

ሴቶችም ሆናቹ ወንዶች ለተራዊህ ስትወጡ በጀመዓ ሂዱ ዱርዬዎች ከተራዊ መልስ የሚመለሰውን ሙስሊም በተለያየ ዘዴ እየያዙ ገንዘብ እየዘረፉ መሆኑ በቤተል መስጂድ ተነግሯል

በተለይ በተለይ በመኪና ሆነው የመስረቁን ነገር ተያይዘውታል የትም ስትሄዱ ተጠንቀቁ በተለይ መኪና ይዘው ኑ እንሸኛቹ ፣ እናድርሳቹ እያሉ ጥቃት እያደረሱ ነው

ብትችሉ ሴቶች ለተራዊህ ከሰፈራቹ ውጪ ራቅ ያለ ቦታ ለመሄድ አታስቢ አደራ ብዙ ጠላት አለብሽ ማንም በማታ ቢያገኝሽ እደማይተውሽ እወቂ

ወድሜም አደራ ብቻህን አትንቀሳቀስ በጀመዓ ሁነህ ውጣ የአንድ ሙስሊም በህይወት መኖሩ የምድር መቆየቷ ምልክት ነው እና አደራ ስልክህን ፣ ወይ በኪስህ ያለውን ገንዘብ ለመውሰድ በጩቤ ወግተውህ ገድለውህ ነው ሚዘርፉህ እና ጥንቃቄ አደራ

እነሱም አላህ ሂዳያ ይስጣቸው አልያ የስራቸውን ይስጣቸው አሚን

የስነ–ልቦና ምክር ለሙስሊሙ ኡማ
@Abdulhakemohammed
@Abdulhakemohammed
1.8K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), edited  11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 23:05:19

ክፍል አንድ


ሙስሊሙ ዝሙት ላይ መውደቁን የሚጠቁሙ ነገሮች
በተለይ በረመዷን ምሽቶች የተስተዋሉ የሙስሊም ልጆች ልቅነት።

ምንም እንኳን በረመዷን ምሽቶች የፆመኞች ትኩረት ወደ መስጂድና ተራዊሕ ቢሆንም ግና የብዙ አዳጊ ልጆች (በተለይ ከ10 ዓመት ጀምሮ ያሉ ሴቶች እና ወንዶች ትኩረታቸው መስጂድ ላይ አልነበረም፤ ይልቁንም የረመዷን ሌሊቶች በተለይ ለአዳጊዎች ከተቃራኒ ፆታ ጓደኞቻቸው ጋር በነፃነት የሚገናኙበት ወር ሆኖላቸው አርፏል፡፡ የዚህ አብይ ምክንያትም ልጆቹ ለተራዊሕ በሚል ከቤተሰብ ፈቃድ ስለሚሰጣቸው፣ ብሎም ከወላጆቻቸው ጋር ይልቅ ከጓደኞቻቸው ጋር እንዲሄዱ ስለሚፈቀድ በዚህም አጋጣሚ ልጆቹ ልቅ በመሆን በርካታ ድብቅ ገመናዎቻቸውን ይፋ አውጥተዋል፡፡ ይህም አጋጣሚ የአዳጊዎችን እምቅ የመበላሸት ችሎታቸውን ገላልጦ ያሳየን የማንቂያ ደውል ነበር፡፡ ወሩ የተከበረ የመሆኑን ያህል የመጪው ትውልድ ገመናን ልንማርበት አልያም ችላ ካልነው መቀመቅ ልንወርድበት፣ ብሎም በቁም ልንቀበርበት ዘንድ ልቅነታችንን ቁልጭ አድርጎ አሳይቶናል፡፡ በዚህ አጋጣሚ አንድ የቁርኣን አንቀጽ ትዝ ይለኛል፡፡

አላህ (ሱብሃነ ወተዓላ) እንዲህ ይላል
Surah At-Taubah 115

وَمَا كَانَ ٱللَّهُ لِيُضِلَّ قَوْمًۢا بَعْدَ إِذْ هَدَىٰهُمْ حَتَّىٰ يُبَيِّنَ لَهُم مَّا يَتَّقُونَ إِنَّ ٱللَّهَ بِكُلِّ شَىْءٍ عَلِيمٌ

አላህም ሕዝቦችን ከአቀናቸው በኋላ የሚጠነቀቁትን (ሥራ)ለእነሱ እስከሚገልጸላቸው(እስከሚተውትም) ድረስ ጥፋተኛ የሚያደርግ አይደለም፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነውና፡፡

ይህ አንቀጽ ከባድ መልዕክት አለው፡፡
የአዳጊዎቻችን ድብቅ ገመና ጋር ትልቅ ትስስር አለው፡፡ በተለይ ወላጆች ያሉበትን ሁኔታ ያሳየ ነበር፡፡ ምናልባትም አላህ(ሱብሃነ ወተዓላ)በዚያ በተከበረው ወር ይህንን ዘግናኝ ድብቅ ገመናችንን ያሳየን ጥፋተኛ አድርጎ ከማያዙ በፊት ማስጠንቀቂያን ሊሰጠን ሽቶ ይሆናል፤ ምክንያቱም አላህ(ﷻ)ሕዝቦችን ቅናቻውን መንገድ ከመራቸው በኋላ ጥፋተኛ ሳያደርጋቸው በፊት ትምህርት የሚወስዱበትን ነገር(ማስጠንቀቂያን)አስቀድሞ በግልጽ ያሳያቸዋልና፡፡ በውነቱ የባለፈው ረመዷን የአዳጊዎቻችን ገመና ትምህርት ከወሰድንበት ትልቅ ማስጠንቀቂያና የማንቂያ ደውል ነበር፡፡ አዎን! አዳጊዎች ማታ ማታ በተራዊሕ ስም ከቤት ይወጡና ከዚያም በዚህ ዕድሜያቸው ወደ መስጊድ ከማቅናት ይልቅ በየጥጋጥጉ ተያይዘው ሲቀመጡ፣ ውስጥ ለውስጥ ተቃቅፈው ሲዞሩ፣ ሲገባበዙና አብረው ሲያመሹ ተስተውሏል፡፡ በርካታ ሙስሊሞችም ይህን አሳፋሪ ትዕይንት በዓይናቸው አይተዋል፡፡ የበርካታ መስጂድ ኮሚቴዎችም በተደጋጋሚ ሴት ልጆቻችሁን ብቻቸውን አትልቀቁ እያሉ ወላጆችን አስጠንቅቀዋል፡፡ የወላጆች እንዝላልነት ግን ሥር የሰደደ ስለሆነ ይህንን ማስጠንቀቂያ ከመጠየፍም የቆጠሩ አይመስሉም፡፡ በተለይም ለእናቶች ሴት ልጆቻችሁን እጃቸውን ይዛችሁ እንጂ ወደ መስጂድ አትምጡ ብሎ ኢማሙ በቁጣ ተናግሯል።
«እንደውም ብልግናው እንዲህ ከተንሰራፋ ሴቶች ከቤት ባይመጡ ይሻላል» ሲሉ አስተያየት ሰጥተው ነበር፡፡ የመስጂድ ኮሚቴዎች በበኩላቸው «ሴት ልጆች ከእናቶቻቸው ጋር ካልመጡ አናስገባቸውም» ሲሉ መመሪያ ሁሉ ለማውጣት ተገደው ነበር፡
እነዚህ ለናሙና የተጠቀሱ ናቸው እንጂ በርካታ መስጊዶችም ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያዎችን ሰጥተዋል፡፡ ወላጆችም ቢሰሙም ተግባራዊ አላደረጉትም፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አንድ በሙያው መምህር የሆነ ወንድማችን የዘመኑን ወላጆችና የልጆችን ግንኙነት አስመልክቶ የታዘበውን ነገር ሲናገር እንዲህ ይላል

«አሁን አሁን ወላጆች ከልጆቻቸው እየፈሩ ይገኛሉ፡፡ ልጆቻቸውን ከማዘዝ ይልቅ ለነርሱ መታዘዝ ይቀናቸዋል፡፡
በተለይም እነዚያ ውጭ ሄደው ገንዘብ የሚልኩ ልጆች የወላጆችን ሥልጣን ተቀናቅነዋል፡፡ እነርሱ ከዚያ እየደወሉ ስለሚያዙ ወላጆች በዚህ ዓይነት ሁኔታ ያዳበሩትን ባህሪ በሌሎች ልጆቻቸው ላይም ይደግሙታል፡፡
ሀገር ቤት ያለው ልጅም ቢሆን ትንሽ ገንዘብ አምጥቶ ዱዓ ካስደረገ በቃ ወላጆች በርሱ ትዕዛዝ ሥር ይሆኑና ሐቁም ይረሳል፡፡ በተለይ ሴቷ ለወላጆቿ ብር ካመጣች ቤተሰብ በሙሉ በርሷ ተጽዕኖ ሥር ይወድቃል፡፡ ለምን እንደዚህ እንዳልኩ ታውቃላችሁ? ሴቷ ከጓዳ ጀምሮ፣ ኩሺናውን እካሎ መላውን ግቢ ለመቆጣጠር ትፈልጋለች፡፡ ወንዱ ግን ምናልባትም ሳሎን ቤቱንና ግቢውን ለመቆጣጠር ቢፈልግ እንጂ ወደ ኩሺና አይዘልቅም፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ የወላጆች የማዘዝ ወኔያቸው ስለሚሟሽሽ ልጆቻቸውን ለማዘዝ ይሳናቸዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ልጆች ተምረዋል ብለው ስለሚያስቡ የተማረ ሁሉ ጨዋና የማይባልግ ይመስላቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሳ ወላጆች በልጆቻቸው ላይ የሚያሳድሩት አሻራ ተዳፍኖ ወደመቅረቱ እያቀና ነው፤ አላህ ይጠብቀን እንጂ፡፡»


የመጨረሻው ክፍል

ይ ቀ ጥ ላ ል

እራስ ወዳድ ካልሆኑ መልዕክቱን ሼር ያድርጉት በምታውቋቸው ግሩፖች ሼር ያድርጉ በውስጥ መስመርም ለሁሉም ጓደኞቻችን እንላክላቸው።
ሃላፊነት አለብን! ምን አልባትም የአንድ ሰው ወደ አላህ የመመለስ ሰበብ ልንሆን እንችላለን።
ለመልካም ነገር እንሽቀዳደም
ባረከላሁ ፊኩም


ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር
ሼር ሼር ሼር ሼር
ሼር ሼር ሼር


ይህ ባጭር ግዜ ውስጥ ተወዳጅነት ያተረፈውን የቴሌግራም ቻናላችን ነው። አልሃምዱሊላህ የአላህ ፍቃድ ሆኖ በምናቀርባቸው ፁሁፎች ብዙዎች ተጠቅመውባቸዋል እናንተም ትቀላቀሉን ትጠቀሙበታላችሁ በአላህ ፍቃድ።
1.3K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), edited  20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-01 23:18:08 በረመዳን በየሰፈራቹ የታዘባቹትን መስተካከል መታረም አለበት ምትሉት እዲሁ ሌሎችን ነገሮች ካሉ በውስጥ ይላኩልን አላህ ካለ በአዲስ መልክ ምክሩን እጀምራለን


@abdulihake
1.0K viewsAbdu ( ነጃሺ ማርኬት), edited  20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ