Get Mystery Box with random crypto!

Abbay TV

የቴሌግራም ቻናል አርማ abbay_tv — Abbay TV A
የቴሌግራም ቻናል አርማ abbay_tv — Abbay TV
የሰርጥ አድራሻ: @abbay_tv
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.76K
የሰርጥ መግለጫ

Abbay TV 'News & Entertainment"

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-01-17 11:18:39
የአዲስ- አዳማ የፍጥነት መንገድ በደረሰ የእሳት አደጋ መዘጋቱ ተገለጸ::

የአዲስ- አዳማ የክፍያ መንገድ በደረሰ የእሳት አደጋ ዋና መውጫው ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ መሆኑን የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ አስታውቋል፡፡

በትናትናው ዕለት ምሽት 4 ሰዓት ከ 45 ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ ወደ አዳማ የሐበሻ አረቄ ጭኖ እየተጓዘ እያለ አዳማ መዉጫ የመጨረሻ ክፍያ ጣቢያ ሲደርስ በደረሰ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አራት ሰዎች ላይ ከባድ የቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸዋ።

በአደጋው በተሽከርካሪዎች ውስጥ የነበሩ ሶስት ሰዎች እና አንድ የክፍያ ጣቢያ ትኬት ቆራጭ ሰራተኛ ወዲያው በቃጠሎው ህይወታቸው ማለፉም ነው የተሰማው፡፡

በተጨማሪም አራት ሰዎችም ከባድ የቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸው በአዳማ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አረቄ ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ተሽከርካሪና ሌሎች ሦስት ተሽከርካሪዎች የተቃጠሉ ሲሆን 10 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ገልጸዋል።

የአደጋዉ መንስኤ የሆነዉ የአበሻ አረቄ በበርሜል የጫነ ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ አስቀድሞ በክፍያ መንገዱ ላይ ቃጠሎው ያጋጠመው ሲሆን፤ አሽከርካሪው መኪናውን ማቆም ባለመቻሉ እሳቱ ሊዛመት መቻሉ ተገልጿል፡፡

ህንንም ተከትሎ አዳማ የክፍያ መንገድ የአዳማ ዋና መውጫ ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ መደረጉ የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ያስታወቀ ሲሆን ደንበኞች በሞጆ 52 ኪሎ ሜትር፣ 56 ኪሎ ሜትር እንዲሁም በ60 ኪሎ ሜትር አማራጭ የጉዞ መስመሮችን እንዲጠቀሙም አሳስቧል፡፡

@Abbay_Tv
1.1K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 11:16:37
በታንዛኒያ በእስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ለመመለስ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ::

በታንዛንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሽብሩ ማሞ በሕገ ወጥ ደላሎች ተታልለው በታንዛኒያ በእስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ለመመለስ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አምባሳደሩ እንደገለጹት በተለያዩ ጊዜያት በታንዛኒያ በኩል አድርገው በማላዊ ድንበር ወደ ደቡብ አፍሪካ በሕገ-ወጥ መንገድ ለመሻገር ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 5 ሺሕ ኢትዮጵያዊያን በታንዛንያ መንግስት በቁጥጥር ሥር ውለው ለእስር መዳረጋቸውን አስታውሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት ጋር በመተባበር በተያዘው ዓመት 1 ሺሕ 99 የሚሆኑትን ከታንዛኒያ እስር ቤቶች ወደ አገር ቤት መመለሱን ገልጸዋል።

በቀጣይም መንግስት በታንዛኒያ በእርስ ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ለመመለስ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በዘላቂነት ለመግታት በኬንያና ኢትዮጵያ እንዲሁም በኬንያና በታንዛንያ ድንበር አካባቢ ጠካራ የቁጥጥር ሥራ ለመስራት አገራቱ መስማማታቸውን ገልጸዋል።

@Abbay_Tv
1.0K viewsedited  08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 11:15:36
በመዲናዋ ከመሬት ምዝበራ ጋር በተያያዘ ስምንት አመራሮችና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ከመሬት ምዝበራ ጋር በተያያዘ ሁለት አመራሮችና ስድስት ባለሙያዎች በጥቅሉ ስምንት በሙስና የተጠረጠሩ አመራሮችና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት አመራሮቹ ፦ አቶ መለሰ ጋሻው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሃላፊ እና አቶ ፍቃዱ መለሰ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ የመሬት ማኔጅመንት ፅ/ቤት ሃላፊ መሆናቸው ተገልጿል።

በቁጥጥር ስር የዋሉ ፈፃሚዎች ደግሞ አቶ ሄኖክ ፍቃዱ (የመሬት አገልግሎት መሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪ) ፣ ሜሮን ማህረይ (የቤዝ ማፕ ባለሙያ)፣ አቶ በላይህ ተፈሪ (የቤዝ ማፕ ባለሙያ)፣ አቶ ፍቅሬ ብርሃኑ (ፋይል አደራጅ)፣ ወ/ሮ ዘላለም በዛብህ (የሲአይ ኤስ ባለሙያ) እና አቶ ሃጎስ በርሄ (የሰነድ አጣሪ ባለሙያ) መሆናቸው ተጠቁሟል።

የተጀመረው ህግን የማስከበር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ የፀረ ሙስና ኮሚቴ ማስታወቁን ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

@Abbay_Tv
1.1K views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 11:07:48
የቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ ፓርቲ አንድ አባሉ መገደሉን ገለፀ::

የቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ ( ቤህኔን ) የፖለቲካ ፓርቲ ትናንት በአሶሳ ዞን አብራሞ በተባለ ወረዳ የንዑስ ቅንጫፍ ጽህፈት ቤት መክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ በደረሰ ጥቃት አንድ አባሉ መገደሉን ፓርቲው አስታውቋል፡፡

የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መሐመድ ኢስማኤል አብራሞ በተባለ ወረዳ በሚሊሻ አባላት በተተኮሰ ጥይት ሌሎች ሰባት ሰዎች ቆስለው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውንም ተናግረዋል።

ሃላፊው አክለውም በፓርቲው አባላት ላይ ጉዳት ያደረሱት የጸጥታ አካላት በህግ እንዲጠየቁም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ጨምረውም በፓርቲው አባላት ላይ ከፍተኛ ጫና እየደረሰ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መሀመድ ኢስማኤል በተለያዩ ጊዜያት በድርጅቱ አባላቱና ደጋፊዎቹ ላይ እስር እና ወከባ ሲደርስባቸው መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡

ፓርቲው በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ያለው የፖለቲካ ድርጅት ሲሆን በህጋዊ መንገድ የሚያደርጋቸውን የድርጅቱን ስራዎች የክልሉ መንግስት ሊያከብር ይገባል ብለዋል፡፡

የቤኒሻንል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሐሩን ዑመር በበኩላቸው ጉዳዩ ያልተረጋገጠ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ሲጣራ ማብራሪያ እንደሚሰጡ ለዶቼቨለ ተናግረዋል፡፡

@Abbay_Tv
1.2K viewsedited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 20:17:34

1.4K views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 19:38:07

1.4K views16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 13:16:32

1.5K views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ