የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
3.25K
የሰርጥ መግለጫ
ገና እንዘምራለን እንደመላእክቱ ብርሃንን ለብሰን
የኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምሮ ና ስርዓት የጠበቁ
👉 መንፈሳዊ መዝሙሮች
👉 መንፈሳዊ ትምህርቶች
👉 መንፈሳዊ ግጥሞች
👉 መንፈሳዊ ታሪኮች
👉 ምንፈሳዊ ምክር ነክ ፁፎች
👉 ንግሶች ስኖሩ እናሳዊቃለን
👉ለመናፍቃለ የተለያዩ መልሶችን እንሰጣለን
ቻናሉን ለመቀላቀል @Abalibanos333
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2
2023-03-08 20:03:09
በአንድ መንደር ውስጥ በሰዳቢነታቸው የታወቁ እድሜያቸው ገፋ ያለ ሴትዮ ነበሩ። አንዴ መሳደብ ከጀመሩ ማቆሚያም የላቸው።
የአብይ ጾም ገብቶ ነበርና ከአሁን በኋላ አልሳደብም ብለው ምለው ተገዘቱ።
ከእለታት በአንዱ ቀን አንዲት ጎረቤታቸው አንቺን ብሎ ጿሚ አፍሽ አይጾም እያለች በነገር እና በስድብ ስትጠዘጥዛቸው "አይ ጾም ሆነ እንጂ ለዚህስ መልስ ነበረው ፣ ሲፈታ ያገናኘን" አሉ ይባላል
ስድብ በቀጠሮ ይሏል ይሄ ነው።
@Abalibanos333
እስቲ ብዙዎቻችን ራሳችንን ዞር ብለን እንፈትሽ። ለጾም ለጾም ከኃጢአት ራቁ፣ ከጾም መልስ ወደ ኃጢአታችሁ ተመለሱ የሚል የትኛው የቤ/ክን ሕግ ነው? ጾምን በኃጢአት ይዘን በኃጢአትስ መፍታት ተገቢ ነውን? ጾም እንዴት ድል ባለ ጭፈራና የመጠጥ ጋጋታ ይይዛል? በጾም መያዣ ወቅት የከተማችን መኝታ ቤቶች ስለምን ይጨናነቃሉ? በእውነት ስለምን እንደምንጾም እናውቀዋለን ግን?
እግዚአብሔር ልብንና ማስተዋልን ያድለን።
501 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 17:03
2023-03-08 06:45:38
#መንፈሳዊ_ጉዞ ወደ ምድረ ከብድ አቦ ገዳም
በመጀመሪያ ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን እያልን የአያት ጣፎ መካነ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት በደማቅ ሁኔታ የሚከበረውን የምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓለ ንግሥ ምክንያት በማድረግ መጋቢት 4-5/2015 ዓ.ም ወደ ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ አዘጋጅተናል።ስለዚህ እርስዎም የበረከቱ ተሣታፊ ይሆኑ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር እና በጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስም ተጠርተዋል።
መነሻ ቀን : 04|07|2015
መነሻ : 12:00 ሰዓት
መመለሻ 05|07|2015 ከንግሥ በኋላ
የጉዞ ዋጋ : 500 ብር መስተግዶን ሳይጨምር
መነሻ ቦታ : አያት ጣፎ ቅዱስ ገብርኤል ቅጥር ጊቢ ዉስጥ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር :
0953125078 ዳኜ
0919289762 ደሳለኝ
0941137351 ፀጋ
0922592670 ተካልኝ
የጉዞ ቦታ ሳይሞላ አሁኑኑ ይመዝገቡ
በረከቱ እንዳያልፈን በቶሎ እንመዝገብ
ለመመዝገብ ከላይ ባሉት ስልኮች ይደውሉ
አዘጋጅ : ተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት
በቴሌግራም @DA121922
552 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 03:45
2023-03-08 06:40:49
@Abalibanos333
471 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 03:40
2023-03-08 06:40:48
የምትወዱት ሰዎች አልቅሱለት ብክይዎ ወላሕውዎ
እለ ታፈቅርዎ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ ኤልማስ
ዘበ እደ አይሁድ ተአስረ
አመ ጸምአ ማይ ይሰቲ
ሀሞተ ወከርቤ መሪረ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ
ጌታዬ አምላኬ በደል ሳይኖርበት ተገፋ
የአዳምን መርገም ሊያጠፋ
በአይሁድ እጅ ታሰረ
እንደ ወንጀለኛ ተቆጠረ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ስለኔ
አልቅሱለት ስለ መከራው የምትወዱት
አዕንቃዕደ ወሰማየ
ኀበ አቡሁ ነጸረ
ሶበመንፈሱ ትወጽዕ
በላዕለ መስቀሉ ገአረ
ወይቤ ወይቤ ተፈጸመ ኲሉ
ውሃን የፈጠረ ተጠማ
ሀሞትን አጠጡት እየደማ
የሾህ አክሊል ደፍቶ ቀና አለ
መራራውን ጽዋ ተቀበለ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ስለኔ
አልቅሱለት ስለ መከራው የምትወዱት
በእናቱ ፊት ሰቀሉት
በጥፊ እየመቱ ዘበቱበት
ሐዘኑንስ እንዴት ትቻለው
መተኪያ የሌለው ልጇ እኮ ነው
እውነት ወደ ምድር ቢመጣ
በሀሰት ዳኝነት ተመታ
በጀርባው ላይ ጅራፍ አረፈ
ደሙ እንደ ውሃ ጎረፈ
ጌታዬ አምላኬ ሞተልኝ ሰለኔ
ወይቤ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ
ወይቤ ኤሎሄ ተፈጸመ ኲሉ
https://t.me/Abalibanos333
466 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 03:40
2023-03-08 06:39:01
✞ከካራን ስወጣ✞
ከካራን ስወጣ ወደ አዲሱ መንገድ
አላውቅም ነበረ ወዴት እንደምሄድ
ያንተን ቃል ነውና በማመን ወጣሁኝ
በረከት አግኝቼ ዘሬን አበዛሁኝ
ሲሰማኝ ምሬቱ የቀድሞው ኑሮዬ
ከቅርቡ ታሪኬ ጨለመ ኋላዬ
ካራን ያስተማረኝ ተስፋ ቢስ ሕይወት ነው
ስጠራኝ ያየሁት የነገን ክብሬን ነው
አዝ= = = = =
ከቶ ማን ሆኜ ነው እንዲህ ያከበርከኝ
ከአህዛብ ለይተህ ከፍ ከፍ ያረከኝ
አብርሐም ሆይ አልከኝ የወደድከኝ አምላክ
ልገዛ ላምልክህ ለክብርህ ልንበርከክ
አዝ= = = = =
ሕዝብህን ታደገው በረከት አይጥፋ
መሆንክን ይወቀው የዘለዓለም ተስፋ
አለማመን ይራቅ ጥርጥር ይወገድ
ልጆችህ ይጓዙ በአንዲቱ መንገድ
መዝሙር
ቀሲስ ዳዊት ፈንታዬ
"ግዚአብሔርም አብራምን አለው። ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"
@Abalibanos333
@Abalibanos333
@Abalibanos333
532 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 03:39
2023-03-05 11:52:35
#ታላቅ_መንፈሳዊ_ጉዞ ወደ ምድረ ከብድ አቦ ገዳም
በመጀመሪያ ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን እያልን የአያት ጣፎ መካነ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት በደማቅ ሁኔታ የሚከበረውን የታላቁን ገዳም ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓለ ንግሥ ምክንያት በማድረግ መጋቢት 4-5/2015 ዓ.ም ወደ ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ አዘጋጅተናል።ስለዚህ እርስዎም የበረከቱ ተሣታፊ ይሆኑ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር እና በጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስም ተጠርተዋል።
መነሻ ቀን : 04|07|2015
መነሻ : 12:00 ሰዓት
መመለሻ 05|07|2015 ከንግሥ በኋላ
የጉዞ ዋጋ : 600 ብር ምሳን ጨምሮ
መነሻ ቦታ : አያት ጣፎ ቅዱስ ገብርኤል ቅጥር ጊቢ ዉስጥ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር :
0953125078 ዳኜ
0919289762 ደሳለኝ
0941137351 ፀጋ
0922592670 ተካልኝ
የጉዞ ቦታ ሳይሞላ አሁኑኑ ይመዝገቡ
በረከቱ እንዳያልፈን በቶሎ እንመዝገብ
ለመመዝገብ ከላይ ባሉት ስልኮች ይደውሉ
አዘጋጅ : ተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት
በቴሌግራም @DA121922
807 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 08:52
2023-03-05 11:29:53
3. #ምኩራብ
ምኩራብ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ናት፡፡ በብሉይ ኪዳን የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በሚገኘው ቤተ መቅደስ ላይ ብቻ የሚፈጸም ነበር፡፡ በኋላ ንጉሥ ናቡከደነፆር ቤተ መቅደሳቸውን አፍርሶ ሕዝቡንም ማርኮ ወደ ባቢሎን አፈለሳቸው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበርተኝነት ልዩ ቤት በመሥራት ስሙን ምኩራብ አሉት፤ (ሕዝ 11፥16)፡፡ በዚህ ምኩራብ ይጸልያሉ፣ ይማራሉ፣ ያስተምራሉም፤ በአጠቃላይ ከመሥዋዕተ ኦሪት ውጭ የቀረውን ሥርዓተ አምልኮ ሁሉ ይፈጽሙበት ነበር፤ መሥዋዕት ለማቅረብ ደግሞ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ይሄዱ ነበር፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ምኩራብ ለማስተማር በገባ ጊዜ ከግብሯ በተቃራኒ መሸጫና መለወጫ ሆና ርግብና በሬ ሲነግዱባት አገኛት፡፡ ጌታም ይህን በተመለከተ ጊዜ ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት›› (ማቴ 21፥13 ፣ ኢሳ 56፥7 ፣ ኤር 7፥11) በማለት ለጸሎት ሳይሆን ለንግድ የገቡትን ከምኩራብ እንዲወጡ በጅራፍ እየገረፈ አባሯቸዋል፡፡ ጌታ ይህን ያደረገበት ሳምንት መታሰቢያ በመሆኑ ሳምንቱ ምኩራብ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት የሚሰበከው ምስባክ ‹‹የቤትህ ቅናት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቋልና፤ ነፍሴን በጾም አስመረርኳት ለስድብም ሆነብኝ›› (መዝ 68፥9) የሚለው ሲሆን የዕለቱ ወንጌል ደግሞ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ መቅደስ ርግቦችን፣ በሬዎችን፣ በጎችን ወዘተ ይሸጡና ይለውጡ የነበሩትን ከቤተ መቅደሱ ማባረሩንና ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ‹‹የቤትህ ቅናት ይበላኛል›› የሚለው ትንቢት መፈጸሙን እንዳስታወሱ ይነገራል፤ (ዮሐ 2፥12-25)፡፡ ጌታ በዕለቱ በሬ፣ በግ፣ ርግብ ወዘተ ይሸጡ የነበሩትን ከምኩራብ አስወጥቶ በእነዚህ እንስሳት ይፈጸም የነበረውን መሥዋዕተ ኦሪት አልፎ የክርስቶስ ሥጋና ደም ብቻ የሚሠዋበት ጊዜ መድረሱን አስተምሯል፡፡
ቤት የተባለው በምሥጢሩ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነው የሰው ሰውነት ነው፡፡ ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን በዚህ ሳምንት ሸቀጥ ከተባለው ኃጢአት በንስሐ ታጥበን ለመቅደሱ ሥርዓት የምንመች ሆነን እንድንኖር ትሰብካለች፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ›› (ሮሜ 12፥2) ብሎ እንዳስተማረን በንሥሐ እየታደስን ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነት ሰውነታችንን ማዘጋጀት ይገባናል፡፡
@Abalibanos333
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
ምንጭ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ፣ ሰባቱ አጽዋማት
738 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 08:29
2023-03-03 16:29:14
ድንግል የዛን ጊዜድንግል
የዛን ጊዜ (፪) ሀዘንሽ በረታ (፪)
በመስቀል ላይ ሆኖ ልጅሽ ሲንገላታ(2)
የግፍ ግፍ ደርሶበት የዛን ጊዜ ተጠማሁ ሲልሽ
ለውሻ ያጠጣሽ በወርቅ ጫማሽ(2)
ሴቶች ሲያባርሩት የዛን ጊዜ ራርቶ ሆድሽ
ለፍጡር በማዘን ውኃ ያጠጣሽ(2)
ተጠማሁ እያለ የዛን ጊዜ ሲናገር ልጅሽ
ታዲያ እንደምን ቻለ የእናት አንጀትሽ (2)
እንደዚያ ስታለቅሽ የዛን ጊዜ ሐዘን ሲከብሽ
እነማን ነበሩ ያስተዛዘኑሽ(2)
ስታለቅሽ በማየት የዛን ጊዜ ራርቶ ልጅሽ
ዮሐንስን አፅናኝ እንደ ልጅ ሰጠሽ(2)
@Abalibanos333
Tik tok
https://www.tiktok.com/@da121922
805 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 13:29
2023-03-03 16:29:12
እመቤቴ ማርያምእመቤቴ ማርያም ወየው እያለች (፪)
አምርራ አለቀሰች እየተደፋች
ወየው አንዱ ልጄ
አንዱ ልጄ እኮ ነው የሌለው እኅት
አንዱ ልጄ እኮ ነው የሌለው ወንድም
ኧረ እንዴት ልቻለው መድኃኔዓለም
ወየው አንዱ ልጄ
እናቴ ኤልሳቤጥ ወዴት ነው ያለሽው
እኅቴ ሶሎሜ ወዴት ነው ያለሽው
እንድታላቅሽኝ ወየው እያልሽ ወየው
ወየው አንዱ ልጄ
ምንም ባላጠፋ ምንም ባልበደለ (፪)
በቀራንዮ ላይ በእንጨት ተሰቀለ
ወየው አንዱ ልጄ
@Abalibanos333
721 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 13:29
2023-03-03 16:26:24
ሞ
ተሃልና ስለኔ ሞተሃልና ስለኔ ምንም ስይኖርብህ ጥፋት
በሐሰት ተከሰህ በጲላጦስ ፊት
ኢየሱስ አምላከ ምሕረት ስብሐት ለከ
ያንተ መንገላታት ሁል ጊዜ ያሳዝነኛል ሲወራ
በመስቀል ላይ ስለ እኛ ያየኸው መከራ
ኢየሱስ የሕይወት እንጀራ ስብሐት ለከ
ከልዑል ቦታ ዝቅ ብለህ ፈጣሬ ፍጡራን አምላክ
በመስቀል ተሰቅለህ ስለ ሰው የሞትክ
በመስቀል ላይ ተጠማሁ እያልክ ስብሐት ለከ
ክፉ አድራጊዎች ተነሥተው በምቀኝነት መንፈስ
ብዙ ሲጣጣሩ ለደምህ መፍሰስ
ሞትክላቸው ደስ እዲላቸው ስብሐት ለከ
መሐሪ ጌታ አሁንም እንደቸርነትህ ብዛት
የእኛን በደል ሁሉ ሳትመለከት
አድነን ከዳግም ሞት ስብሐት ለከ
@Abalibanos333
Tik tok
https://www.tiktok.com/@da121922
621 viewsĎ`Ą የእናቱ ልጅ , 13:26