Get Mystery Box with random crypto!

በዶ/ር ኤልያስ ገብሩ ''አርምሞ'  ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰዱ፦ - የእያንዳንዳችን | ህይወት ጥበብ ፍልስፍና

በዶ/ር ኤልያስ ገብሩ ''አርምሞ" 


ከመጽሐፉ የውስጥ ገጾች የተወሰዱ፦

- የእያንዳንዳችን የውስጥ ዓለም ሲያምር እንደ ህዝብ ውጫዊ  ህይወታችንም ይዋባል። ውስጣቸው የተረበሹ ሰዎች ግን ህዝብና ሀገርን ይረብሻሉ።

- ሰው በጥሞና ተቀምጦ አእምሮውን ሲያዋቅር፣ ነፍሱን ከሀልዮቱ ሲያስታርቅ ከራሱ አልፎ በዙሪያው ባሉ ሰዎች ላይ ተጽዕኖ ያደርጋል።

- ውስጣቸው የሰለጠነ፣ እግረ-ህሊናቸው የበረታ፣ በአርምሞ የመጠቁ ዜጎች ሲበዙ፣ ያኔ ሀገር ሰላምና አንድነቷ የእውነት ይፀናል።