Get Mystery Box with random crypto!

ነገረ - ጥበብ 📚📚

የቴሌግራም ቻናል አርማ zikiretibeb — ነገረ - ጥበብ 📚📚
የቴሌግራም ቻናል አርማ zikiretibeb — ነገረ - ጥበብ 📚📚
የሰርጥ አድራሻ: @zikiretibeb
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 440
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channal
ላይ የጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ ሁሉቹንም ለማስደሰት የተመረጡ እና ማራኪ የሆኑ ወግ፣ ግጥም ፣ ስዕሎች አጫጭር ድርሰቶች እና ከመፅሐፍት የተወሰዱ ጣዕም ያላቸው አጫጭር ፅሁፎች ይቀርባሉ።
ጀማሪ ገጣምያን እና ፀሀፊያ ይበረታታሉ። ለተጨማሪ
በ.
@Fano3

@ZikiretibebBot

ማናገር ትችላላቹ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-02 13:55:30
የዋህ ምን ይሆናል ?

ከራሚና : ሂያጅ
ወጪና : ወራጁ
ለጸሊም : ልባቸው
ከመለኮት : ደጁ
በዕዳሌ : ፈገግታ
ሞፈሩን ሲቆርጡ
በገዛ : ብልቱ
ተመን ሲያወጡ
ያረምማል : እንጂ
የዋህ : ምን : ይሆናል?
የቃሉን : መሀላ
እምነቱን : ይበላል

fanuel a.
@zikiretibeb
@zikiretibeb
73 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 10:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 08:07:47 ወንድም የሌለበት ጦርነት ደስ ማለቱ
እንቅልፍ ይወስዳቸዋል። ይስቃሉ። ከቻሉ እስክስታም ይወርዳሉ ። የላኩት ወይ የሚጠብቁት የላቸውም። ታድለው!
እዚህ... አልጋዬ ይወጋኛል ፣ ሰማዩ ሲያጓራ የምደበቅበት አንገት ከጎኔ ርቋል፣ ነጠላ የለበሰ ሰው ባየሁ ቁጥር ሽንቴ ይወጥረኛል፣ጀበና እና ስኒዬን ድር ሸፍኖታል። ይወደው የነበር ሽቶዬ ሳልነካው ቀን በቀን ነፍሶ አልቋል ። ጉንጉኔም አስታውሶ የሚያድሰው ጠፋ። ቆሞ ቀር ሀገሬ ባሌን ቀማችኝ። አባቴ መርጦ የሾመልኝን ጠባቂዬን ወሸመችብኝ።
እሷስ የለበጣም ቢሆን የሚያዝን የሚያስተዛዝናት አታጣም።(እንዳልጎደለባት ሆንኩ'ኔ)
ሀገራቸውን በባሌ ደረትና ጎድን አጥረው አንቀላፍተዋል። የሚጠብቁት ክብር፣ የሚዋደቁለት ድንበር፣የሚያስሞት ሀገር በልባቸው አላቸው። ታድለው። (በገባኝ እና ጋደም ባልኩ)
ባሌን አልወደውም ነበር። ከሰኞ ማክሰኞ'ዬ ፈልቅቆ ሲወስደኝ ቤት እንኳን አልገዛሁም ። ከ ሰርጌ ይልቅ ቅልልቦሽ ተጫውቼ ያበላኋት አይጥ በዓሌ ነበረች።ከዛ ሁሉ ያቆራረጠኝ ነው። አጠገቡ አድጌ ነው ሴት የሆንኩት። ክታቤን አውልቆ በ ድሪ ሲቀይርልኝ ማጌጥ የምትጠላ የለችምና ትንሽ ወደድኩት። ሎሚው ያልጠራ ዶሮዬን አመስግኖ ሲበላ ጨርሼ ይቅር አልኩት። መቀነቴ ወደ ዳሌ'ዬ እየተንሸራተተ መውደቁን ሲተው። አፍርሶ እንደሰራኝ ሆንኩ። ሴትነቴን ወስዳ ሀገሬ ድንበሯን ጠቀጠቀችበት። መሬታችን ጦሙን አደረ። እሱ እንኳን አራሙቻ ለብሶ ክረምቱን ተወጣ። እዚህም እዛም ለሚበርደኝ እኔ ዋ!
ከዛ እስከዛሬ እንደሄደብኝ ነው። ደህና ናችሁ?
ያቺን ቀን እኔና ክብሬ
እሱ፡ ዘመቻ መሄዴ ነው ። አንገቱን ቀና እንዳረገ
እኔ:ለማን ነው
እሱ ለሀገር ነዋ
እኔ ለእዚህ ለጦስ ማስገሪያ?
እሱ ሞኞ ኧረ ለ ትልቋ
እኔ እንደኔ ጠይም ናት? ሴት ናት? እኔን ታውቀኛለች? የደፈሯት ተመልሶ ይከብርላታል? ባሌን እስካካፍላት ሀገር ሆናኛለች?
እሱ እንደ ፈሪ አታስወሪኝ።
እኔ፡ ማን ወርሮን ነው? አዝማቹ ማን ነው?
እሱ፡ አንዴ ስብሰባ ቀርተን ማዳበርያውን ዘንድሮ አታገኙም ብሎን የለመንሽው ረጅሙ ሰውዬ አወቅሽው? እሱ ነው የመለመለን።

Zion lisanu
@zikiretibeb
@zikiretibeb
80 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 08:01:27 ምን አይነት ዘመን ነው
ዘመነ ተላላ
እውነት ስትሸፈን
በድኩም መኃላ
ቆመን የሰቀለነው
በስሜት ሁካታ
ተቀመጦ ያርደናል
ባለጊዜ ጌታ

fanuel a.
@zikiretibeb
@zikiretibeb
113 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 10:31:13 °ብርቱ ጥቁር°



እናት አባቱ ካፈሯቸው ስምንት ልጆች መሀል አንዱ ነዉ። አባቱን በነጮች የዘረኝነት በትር ያጣው ገና በልጅነቱ ነበር።•••

•••ከዚህ በኋላ የሱን ጨምሮ የስምንት ለስራ ያልደረሱ: ልጆቿን ሆድ የመሙላት እጣ: እናቱ ላይ ወደቀ፣ የሚያሳዝነው ልጆቿን ለመመገብ ስራ ፍለጋ ብትወጣ: የባሏን ስሞ እየጠሩ " የሱ ሚስት ናት ስራ እንዳታሰሯት" ብለው ተማማሉ!

•••የስምንት ልጆቿን ረሀብ እንዴት አስችሏት ትይ? እናት እኮ ናት!

•••ምርጫ ያጡት ልጆችም ጎዳና ወጡ: ይሄንን ያየች እናት: አባወራዋን በግፍ የተቀማች እናት፣ በነጮች የክፋት ሴራ: ልጆቿን መመገብ ያልቻለች እናት ጨርቋን ጥላ አበደች።ምስኪን እናት!•••

•••'ተፈጥሮ' ግን ይሄንን በመሰለ መመሰቃቀል ውስጥም ቢሆን: ለ ተአምር ይሆን ዘንዳ: ከስምንቱ አንዱን: በመከራ ካሳለፈው ሂወቱጋ አዋህዳ ጠንካራ ፍልስፍናን ሰጠችው። •••

•••ያላለፈበት የህይወት ፈተና የለም፣ በግፍ ተወልዶ በግፍ አድጓል። •••

•••ይህንን ብርቱ ሰው: ዛሬ ላይ አንዱ: "የጥቁር የነፃነት ታጋይ ይለዋል፣ ሌላው የኔ ሐይማኖት ተከታይ ነዉ ይለዋል።•••እሱ ግን የማንም አይደለሞ ፣ መከራን ኖሮት: ስለ እውነት ታግሎ ስለ እውነት የተሰዋ ብርቱ ሰው ነው። •••

•••የእናቱን በግፍ ብዛት ማበድ በልጅነት እድሜው ማስቀረት ያልቻለ ሰው ነው።

" ሁለተኛው ግፍ ጫንቃዬን ተገርፌ: ልብሴን መገፌ" የሚሉትን ብሂል እሱ ግን ኖሮታል!

••• ይህ በባዶ እግሩ በ እሾህ ላይ ተራምዶ: ታላቅ የሂወት ፍልስፍናን የወለደው: ጠንካራ ጥቁር ሰው 'ማልኮም ኤክስ' ይባላል።•••

•••የሂወት ፈተናን ኖረውት አልፈው: ለምድር ፋናቸውን የተዉ ህያው ግለሰቦችን: እዛ የሂወት ፍልስፍና ላይ ምን እንዳደረሳቸው ስንማር ምናልባትሞ: በስክነት እንድንራመድ ያደርገን ይሆናል።! •••

•••ማልኮም የማንም አይደለሞ። የጥቁር መብት ታጋይ አትበሉት! የኔ ሐይማኖት ተከታይ ነውም አትበሉት! እሱ የመከራን እሬት ለጠጡ፣ ፍልስፍናን ካጠገባቸው እንጀራ ውስጥ ሳይሆን: ከረሀባቸው ውስጥ ለወለዱት ነው ተምሳሌትነቱ። •••



•••"እስከ ክርን የሚደርስ ስለት በጀርባዬ ከተው: ስንዝር ያህል ስበው ስላወጡልኝ : መልካም የዋሉልኝ ይመስላቸዋል?? ሙሉውን እንኳን ቢያወጡልኝ: ጠባሳው እንደሚቀር አያውቁምን???" ይላል ማልኮም የነጮችን የክፋት ልክ ሲገልፅ።


•••ብርቱ ጥቁር! ብርቱ ሰው! ማልኮም ኤክስ።•••



ተፃፈ:- በጠሃ ጀማል( ሄብሮን)

16/10/ 14
@zikiretibeb
@zikiretibeb
146 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 10:31:02
110 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 16:41:24 ውድ የነገረ-ጥበብ channel ቤተሰቦች... በተለያየ ሁኔታ በመጨናነቄ በቻናሉ ለተፈጠረው ክፍተት ይቅርታ እየጠየኩ... ቻናሉ የናንተም ነውና ቀጣይነት እንዲኖረው ያዝናናል ያስተምራል የምትሉትን ፅሁፎች በመላክ ይበልጥ ቤተሰብነታችንን እናጠንክር።

@zikiretibeb
@zikiretibeb
123 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 11:31:48 (ለ ግንቦት ፳ (20))
#በድጋሚ
#በወረሀ_ግንቦት

የማሩ ባተሌ
ከጫካ የወጣች
ምን ብትሆን ነዳፊ
ላ'መል የማትመች
ግብሯ እውነት አለው
አበባ መቅሰሙ
ውሉ ለዝንብ ነው
ግንቦት መሠየሙ
እናም በእኛ እድሜ
በምኖረው ትውልድ
በሀያዎች ዘመን
በመጣነው መንገድ
በወርሀ ዘጠኝ
በጠባ መስከረም
የዝንብ መንጋ እንጂ
ንቡን አለየንም!።


fanuel a.
@zikiretibeb
@zikiretibeb
200 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 22:10:22 በመከፋት ውስጥ ያለው ምርጥ ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ?

ሁሉም ነገር መጮህ እና መፈንዳት ይጀምራል ይሄም በህይወት ውስጥ አንድ ነገር ልትማርበት እንደምትችል ያሳያሃል ያም በጭራች የማይወድቀው ብቸኛው ነገርህ ነው። በአጥንቶችህ ውስጥ ያለው መቅኔ አርጅቶ መንቀጥቀጥ ትጀምር ይሆናል፣ በእኩለ ለሊት ነቅተህ የደም ስሮችህን ህመም ልታዳምጥ ትችላለህ ፣ ብቸኛዋን ፍቅርህን ልታጣትም ትችላለህ፣ የገነባኸው አለምህ ለሴጣን ምሳ ሆነው ሲደመሰሱ ልታይ ትችላለህ ፣ ወይም በሰዎች በአዕምሮ ምልከታ ውስጥ ክብርህ እንደተረገጠ ልታውቅ ትችላለህ ፡፡

በእነዚህ ሁነቶች ውስጥ አንድ ነገር ብቻ ነው የምታገኘው ---ምን ካልከኝ ትምህርት:: ስትማር አለም እንዴት እየተሰቃየች እንደሆነ እና ስቃዩ ምን እንደሆነ ተማርበት:: ያ ብቸኛው ነገር አእምሮ በጭራሽ የማይዝልበት፣ የማይታወክበት ፣ የማይሰቃይበት፣ በጭራሽ በፍርሀት የማይታወክበት እና በጭራሽ የማይጸጸት ህልም ነው፡፡

መማርህ ላንተ ያለህ ብቸኛው ነገር ነው :: እስኪ ተመልከት ምን ያህል ብዙ ነገሮች እንድትማርበቸው እንደተዘጋጁልህ............

(T.H. White, The Once and Future King)


@zikiretibeb
@zikiretibeb
236 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:05:18 መጤ!


የመጣ ሰው የለም: ሁሉም ኢትዮጵያዊ እዚህ የነበረ ነው! የመጣው IDEOLOGY ነው። ኢትዮጵያ ከ ክርስትና በፊትም ነበረች: ክርስትናን እንደተቀበለች ሁሉ እስልምናን ተቀብላለች: በአንድ ሙስሊም፣ ፕሮቴስታንት ፣ ወይም ኦርቶዶክስ መሀል ያለው ልዩነት አሁንም የ IDEOLOGY እንጂ ሁሉም ደሙ አንድ ነው። መጤ ማለት ስሙ አቡበከር የሆነ ሰው አረብ ነው ማለት ነው??? IDEOLOGYን መቀበል መጤ ሚያስብል ከሆነ እዝች ሀገር ውስጥ ምንም አይነት የውጭ IDEOLOGY ያላስተናገዱት ብቻ ናቸው መጤ ማይባሉት!!!••• እንጂ ሁስታዝ ሆነ ዲያቆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው ደሙ: ኢትዮጵያዊ ደምን መሻር አይቻልም በሐይማኖት! ሐይማኖት ስላለን አይደለም ኢትዮጵያዊ የሆነው: ሐይማኖት ኖረም አልኖረ እኛ ፈለግንም አልፈለግን ሁላችንም ኢትዮጵያዊ ነን! ።


I am sorry for African Religious concept••• here is a powerful quote

Our task is to make ourselves the architects of the future.” “When the Missionaries arrived, the Africans had the land and the Missionaries had the Bible. They taught us how to pray with our eyes closed. When we opened them, they had the land and we had the Bible.”

Jomo Kenyatta


i am thinking about the negative impacts of comparative religion to become Ethiopia and Ethiopian! AND the concept of Mysticism.


by :Teha Jemal(Hebron)
@zikiretibeb
@zikiretibeb
226 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 11:37:55 አየር ልቀቅ!

(Samuel Geda)

በአንድ ትልቅ የመኪና ማምረቻ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ የሚሠራ መሐንዲስ፤ በዐይነቱ ልዩ የሆነ፣ በተወዳዳሪነቱም የላቀ- አዲስ የመኪና ሞዴል ይነድፋል።
*
የድርጅቱ ባለቤትም በውጤቱ እጅጉን በመደነቅ ምስጋናን ይቸረዋል።
*
ይሁንና መኪናውን ከማምረቻ ሥፍራ ወደ ማሳያ ክፍል (showroom) ለመውሰድ በሚሞክሩበት ጊዜ፤ አዲሱ መኪና ከመግቢያው በር በ10 ሳ.ሜ እንደሚረዝም ይረዳሉ።
*
መሐንዲሱም፤ ቀድሞውኑ የመኪናውን ንድፍ ሲሠራ ይህንን ግንዛቤ ውስጥ ባለማስገባቱ ይተክዝና ያዝን ጀመር።
*
የድርጅቱ ባለቤትም መኪናውን ከማምረቻ ሥፍራ እንዴት እንደሚያወጣው ግራ ይገባዋል።
*
ይህን ጊዜ ቀለም ቀቢው ተነሥቶ፤ "መኪናውን ሊያወጡት እንደሚችሉና በመኪናው ላይኛው ክፍል ብቻ ትንሽ ጭረት እንደሚኖር እሱም ቢሆን ከወጣ በኋላ በቀለም ሊስተካከል እንደሚችል" በመናገር ተስፋን ይሰጣል።
*
ለጥቆ መሐንዲሱ፤ "የመግቢያውን በር ሰብረው መኪናውን ማውጣት እንደሚችሉና መልሰውም በሩን እንደሚጠግኑት" ይናገራል።
*
ይሁንና የኩባንያው ባለቤት የተነሱት የመፍትሄ ሐሳቦች በመላ አልተዋጡለትም፤ መኪናው ላይ የሚደርሰው ጭረትም ሆነ የመግቢያውን በር መስበሩ መልካም መስሎ አልታየውም።
*
ታዲያ ይህ ሁሉ ሲሆን ዳር ቆሞ ሲታዘብ የነበረው የኩባንያው ጥበቃ ሠራተኛ በዝግታ ወደ ባለቤቱ ይጠጋና የሚቻል ከሆነ በነገሩ ላይ ሐሳብ ለመስጠት እንደሚፈልግ ይናገራል።
*
ኃላፊውም የጥበቃ ሠራተኛው የነገራቸው ኤክስፐርቶች ሊሰጡ ያልቻሉትን በመሆኑ እጅጉን ተደነቁ።
*
ጥበቃው የተናገረው፤ "መኪናው ከመግቢያው በር በትንሽ ሳ.ሜ ከፍታ ብቻ ነው የሚረዝመው፤ ስለዚህ በቀላሉ በጎማው ያለውን አየር ስትለቁ የመኪናው ቁመት ይወርዳል፤ በቀላሉም መውጣት ይችላል" የሚል ነበር።
*
ሁሉም በአንድ እጅ አጨበጨቡ!
* * *
ልብ በል፤
• አንድን ችግር ከባለሙያ/ኤክስፐርት እይታ ብቻ ተነስተህ ለመተንተን ወይም ለመፍታት አትሞክር።

• ሁልጊዜም ቢሆን "ተራ" ከሚባል ሰው ለወሳኝ ሁነት የሚሆን ጠቃሚ መልስ እንዳለ አትዘንጋ።

• ጥበብ በትህትና የምትሸመት ገንዘብ መሆኗን ልብ በል።

• አንድን ጥያቄ የሚያከብደውም የሚያቀለውም የነገሩ ውስብስብነት ሳይሆን ችግሩን የምትፈታበት መንገድ መሆኑን አስተውል።

የህይወት ነገርም እንዲሁ ነው.. ቀለል አድርገህ አስብ። ቀላል ነገር ሥራ፤ በቀላሉም ኑር! ምክንያቱም 'ተሞልተን' ነው እንጅ እኛ በተፈጥሮ መልካም ሰዎች ነን።

ይኸውልህ፤ አንተ በጠጣኸው መርዝ ሌላው እንዲሞት መቼም አትጠብቅም፤ ውስጥህን የሞላው 'አየር' ያንተን እጣ ፈንታ ይወስናል። ። ምናልባት ይህ አየር (ንዴት፣ ጸጸት፣ ግራ መጋባት፣ ቂም፣ ጥላቻና በቀል) ጉዞህን ገቶት፣ ነገህን አጨልሞት፣ እርምጃህን ገድቦት፣ ተስፋን አሳጥቶ፡ ሩቅ አልመህ ሩቅ እንዳታድር አድርጎህ... ይሆናል።

የተሞላኸውን አየር ልቀቅ። ስትለቅ የሚለቅና የሚለቀቅ ነገር አለ። ያን ጊዜ አላልፍም ካልክበት ሁኔታ ልታልፍ፣ አልወጣም ካልክበት ማጥ ልትወጣ ትችላለህ። አየህ በስተመጨረሻ ሁሉም ነገር "ቁመትን/አስተሳሰብን ማስተካከል" ይሆናል፤ በውጤቱም- የውስጥ ሰላምን፣ ጤናማ አስተሳሰብን፣ ስኬትንና ደስታን... ማጣጣም ትችላለህ!!
@zikiretibeb
@zikiretibeb
244 viewsፌዮዶር. ዶስቶዬቭስኪይ , 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ