የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
4.07K
የሰርጥ መግለጫ
ዜና Tube በኢትዮጵያ ወቅታዊ ፣ ጠቃሚና አንገብጋቢ መረጃወችን ከስር ከስር ለመከታተል የዜና Tube ቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ይሆኑ!
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉ
👇👇👇👇
@ZenaTube_bot
@ZenaTube_bot
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
1
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3
2022-07-05 23:06:16
#EHRC
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን በሃዋ ገላን ወረዳ (መንደር 20 እና መንደር 21) ላይ ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ ንፁሀን ዜጎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ መፈጸሙን ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል።
ኮሚሽኑ ሁኔታውን እየተከታተለ መሆኑና እና ከአካባቢው ተርፈው የሸሹ ሰዎችን ማረጋገሩን አመልክቷል።
ኮሚሽኑ ጥቃቱ ያደረሱት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ሸኔ) አባላት መሆናቸውንና ግድያውም ከጥዋት አንስቶ መጀመሩን ምንጮቼ አመልክተዋል ብሏል።
ኢሰመኮ የመንደር 20 እና መንደር 21 ነዋሪዎች በዋናነት የአማራ ብሄር ተወላጆች መሆናቸውን መረዳቱንም ገልጿል።
የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ወደ አካባቢው መድረሳቸው ተነግሯል ያለው ኢሰመኮ ነዋሪዎቹ ግን ወደ ሌላ ቦታ ሄደው መጠለላቸውን ቀጥለዋል ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።
የኢሰመጉ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ " በአካባቢው የቀጠለው የጸጥታ ችግር እና በነዋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ብሔር ተኮር ግድያ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።
ተጨማሪ የንፁሃንን ሞት ለመከላከል መንግስት የፀጥታ ኃይሉን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።
404 viewsedited 20:06
2022-07-05 23:06:16
" በትንሹ 150 ሰዎች ተገድለዋል "
ቢቢሲ አፍሪካ ዛሬ ማምሻውን ይዞት በወጣው ዘገባ በኦሮሚያ ክልል፣ ሀዋ ገለን ወረዳ በተፈፀመው ጥቃት በትንሹ 150 ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል።
ቢቢሲ አፍሪካ ፤ የአይን እማኞች ጥቃቱ በሀዋ ገላን ወረዳ መፈፀሙን እንደገለፁለትና በአካባቢው ላይ በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር አክሏል።
416 viewsedited 20:06