2022-07-05 23:06:17
#ዝርፊያ
የኤሌክትሮኒክ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዜጎች በተለያየ ጊዜ ዘረፋን ጨምሮ እስከ ግድያ የሚደረስ ወንጀል ይፈፀምባቸዋል።
ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት ሲፈፀም ሰምተናል።
ከሰሞኑን አንድ በዚሁ በኤሌክቶኒክ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ሚሰራ ሰራተኛ ዝርፊያ እንደተፈፀመበት አመክቷል።
ስሙ ሚኪያስ ተፈሪ የተባለው ወንድማችን ራሱንና ቤተሰቡን ለማስተዳደር የሚሰራባትን መኪና ይዞ ቆሞ ሥራ ሲጠባበቅ ነበር (ባለፈው ረቡዕ ምሽት)።
ከአገግልሎት ሰጪ ድርጅቱ ተደውሎ ከሳሪስ ጀሞ ሥራ እንዲሄድ ይጠየቃል ፤ የድርጅቱን ትእዛዝ ተቀብሎ ሦስት ሰዎችን አሳፍሮ ወደታዘዘበት ጀሞ ይሄዳል።
ደንበኞቹ ያሉበት ጀሞ ደረሱ። " ሂሳብ ስንት ቆጠረ?" ብለው ጠየቁ። ሂሳቡን ነገራቸው። እነርሱ ግን በያዙት ስለት አስፈራርተው መኪናውን ነጥቀው ተሰውሩ።
ሚኪያስ ቤተሰቡን የሚያስተዳድርበትን መኪና በዚህ መንገድ ተነጥቋል። ሚኪያስ ለፖሊስ ጣቢያ ድርጊቱን አሳውቋል። እስከዛሬ ሰኞ ድረስ አንዳችም ፍንጭ አልተሰማ።
መኪናው ከላይ በፎቶው የተያያዘ ሲሆን ታፋልጉት ዘንድ ጥሪ አቅርቧል ፤ (0922875988)
በሌላ በኩል ፤ በመሰል ስራ ላይ እራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን የሚያስተዳድሩ ወገኖች በተደጋጋሚ የሚሰሙት ዝርፊ እና ወንጀል ለስራቸው ስጋትን እየፈጠረ መሆኑን በመግለፅ የደህንነት ጉዳይ ይታሰብበት ፤ ወንጀለኞችንም ተከታትሎ አድኖ መያዝ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
477 viewsedited 20:06