የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሽንፈትን አስተናግዷል!
በ ካሜሮን አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የሰላሳ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አንድ ሁለተኛ ጨዋታ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በኬፕ ቨርዴ አቻው 1-0 ውጤት ተሸንፏል ።
የኬፕ ቨርዴን የማሸነፊያ ግብ ጁሊዮ ታቫሬዝ አስቆጥሯል ።
ያሬድ ባየህ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በኩል በ12ተኛው ደቂቃ ላይ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል ።
የዛሬውን ጨዋታ ውጤት ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ምድብ አንድ ላይ አራተኛ ደረጃን ላይ የተቀመጠ ሲሆን ኬፕ ቨርዴ ምድቡን በሶስት ነጥብ ከካሜሮን ጋር በተመሳሳይ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ቀጣይ ጨዋታውን ሀሙስ ከአዘጋጇ ካሜሮን ጋር ያደርጋል ።