━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ አንደገሃነም ቁልቁለት ፥ የፍም ድጥ የእሳት ኮረብታ መጣሏን ባየሁበት ልክ ፥ ቃሌ ነፍስሽን አንሸራታ በሲኦል ምሶሶ ቁመት ፥ በሀዘኔ ቁመት ከፍታ ይቅርታ! ክፋቴ ያላየችሁን ፥ ስላንቺ ከራስሽ በልጣ ሳትገባ የያዘችዉን ፥ እሆድሽ ይዛ ብትወጣ ባብተሸ ባነባሽዉ ልክ ፥ በዕንባሽ ቁልቁለት ስሞታ ይቅርታ! ለልመናሽ ጌታ ሆኜ ፥ አፈር ልሰሽ አንደምንጣፍ አንደታቦት ተደግጌ ረግጬ ፥ ጠቅጥቄሽ ሳልፍ ፊቴ ወድቀሽ አንደገና ፥ አፍረሻልና በኔ ፈንታ እድሜ ባስቆጠረኝ ልክ ፥ የሐፍረት ሰጋር ትርታ ይቅርታ! ┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ መዘክር ግርማ ╰══•••┈ ወደመንገድ ሰዎች ┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ አንድ ልጅ አዝማሪ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• መዘክር ግርማ በ አዲስ መጽሃፍ መጥቶልናል ይነበብ! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• 422 views17:01