Get Mystery Box with random crypto!

ዑመር እብን ኸጣብ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋ | አቡኪ||የነቢ||OFFICIAL

ዑመር እብን ኸጣብ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم
እንዲህ ብለዋል፦ ‹አደም ሀጢአት በፈጸሙ ጊዜ
የሚከተለዉን ዱዐ አደረጉ፦
يَا سألك بحق دمحم لما غفرت لي
َ
َر ِّ ب أ
‹አምላኬ ሆይ፣ ምህረት ትለግሰኝ ዘንድ በሙሀመድ መብት
/ልቅና/ እለምንሀለሁ፤› አላህም፦ «ሙሀመድን ገና
ሳልፈጥረዉ እንዴት አወቅከው?» በማለት ጠየቃቸዉ ።
እርሳቸዉም፦ «በፈጠርከኝና ነፍስ በዘራህብኝ ጊዜ ቀና
ባልኩበት ቅጽበት ከአርሽ መቋሚያዎች ላይ ላኢላሀ ኢለላህ
ሙሀመዱን ረሱሉላህ የሚል ጽሁፍ አየሁ። ካንተ ዘንድ
ከየትኛውም ፍጡር የበለጠ ተወዳጅ የሆነን ሰው ሥም
ካልሆነ በስተቀር ከሥምህ እንደማታቆራኝም ተገነዘብኩ፣»
አሉ።
አላህም፦ «አደም ሆይ! እውነት ተናገርክ፤ በእርግጥም እርሱ
ከየትኛውም ፍጡር በላይ ከኔ ዘንድ ተወዳጅ ነው። በርሱ
መብት (ክበር ልቅና) ተማጸነኝ፤ ምህረት አድርጌልሀለሁ።
ሙሀመድ ባይኖር ኖሮ አልፈጥርህም ነበር፣» አለ። (አልሀኪም፣
አልበይሀቂ፣ አልሱዩጢ ጦበራኒ)
እብን ዓባስ ዋቢ ተደርገው በተላለፈ ሌላ ዘገባ፦ «ሙሀመድ
ባይኖር ኖር አደምንም፣ ጀነትንም፣ እሳትንም
አልፈጥራቸውም ነበር» ማለቱ ተወስቷል።



አልሀኪም፣ በሱዩጢና በሌሎችም ዑለማዎች ሶሂህ የተሰኘው
ይህ ሀዲስ የሚከተሉትን ቁሞ ነገሮች ያስተምረናል፦
1. የነብያችን صلى الله عليه وسلم ልቅና፤
2. ነብዩ አደም በርሳቸው በረከት ሐጢአታቸው መማሩ፣
3. በነብዩ صلى الله عليه وسلم ክብርና ልዕልና ተወሱል ማድረግ እንደሚበረታታ፤
4. በዚህ ዓለም በህይወት በሌሉበት ዘመንና ሁኔታ ተወሱል
በርሳቸው ማድረግ እንደሚወደድ፤
5. ነብያችን صلى الله عليه وسلم ክብር ተወሱል ማድረግ የነብያት ሱና መሆኑ፤
6. ነብያችን صلى الله عليه وسلم ለዓለም መፈጠር ሰበብ መሆናቸው፤
7. ነብያችን صلى الله عليه وسلم ሳይፈጠሩ በፊት በላይኛው ዓለም ዝናቸው
የገነነ እንደነበረ፤
8. በርሳቸው ክብር አላህን መማጸን ያለው ትርፋት፤

T.me/yenebiywedaj
T.me/yenebiywedaj
T.me/yenebiywedaj