Get Mystery Box with random crypto!

TECH TALK

የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_yegna — TECH TALK T
የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_yegna — TECH TALK
የሰርጥ አድራሻ: @yegna_yegna
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 53
የሰርጥ መግለጫ

እንኳን ወደ TECH TALK ደና መጡ
😗😗በዚህ ቻናል ድንቅ ድንቅ ስራዎች ይቀርባሉ
👉አስደናቂ ታሪኮች
👉ግጥሞች
👉የተመረጡ መጽሐፍቶች እና ሌሎች የሚቀርብበት ቻናል ነው
💗አላማው የሰው ልጅ ከሁሉም ፍጡር የሚበልጥጠት
ኣእምሮ እና ልብ የሚያጠነክሩ እና የሰው ልጅ ልዩ ስጦታው እየተጠቀመበት እንዲኖር
የሚያደርጉ ሀሳቦች ማጋራት ነው።💜
👉ለማንኛውም አስተያየት @Abitiim

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-28 14:31:57 ዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
ሚካኤሌ ለትንሽ ደቂቃ በሩ ላይ ቆመና ሲያያቸው ቆየና ሚጣ በመነሳት ሄዳ
እጁን ይዛ ወንበሩ ላይ አስቀመጠችው ለደቂቃ በዝምታ ቆየና ።
" መሽቷል ማክዳና ሚጢ ለምን በኮንትራት ታክሲ አትሄዱም " አላቸው ሚካኤሌ
ግን ሁለቱም ለመሄድ ፍቃደኛ አልነበሩም
" ምን እንደተባለች ለምን አትነግረንም " አለች ማክዳ
" እሺ ምንም በሽታ የለባትም " አለቸው ሚካኤሌ
" እና ምን ሆና ነው " አለችው ማክዳ
" አይምሮዋ ከአቅሟ በላይ ጫና መቋቋም ተስኖት ነው እራሷን የሳተችው ግን
በወደቀችበት የጭንቅላት አጥንቷ እና የጀርባ ተሰብሯል ሌላም የተሰበሩ
አጥንቶች እግር እጇ ላይ የተሰበሩ አሉ " አለ እና አንገቱን ወደ መሬት ደፋ።
" ሚኪ ይሄ እኮ ውድ ሆስፒታል ነው ለሜን የመንግስት አንወስዳትም አሁን እኮ
ለዚህ ህክምና በትንሹ 10 15 ሺህ ይጠይቃሉ ....."
" የመንግስት ሆስፒታል መሄዱ ምን ትሩጉም አለው እነሱ ወደ የሚያክሙበት
የግል ሆስፒታል ይልኳታል ስለዚህ እዛ መሄዷ ትርጉም የለውም " አለ ኬብሮን
ድንገት በመሀል በመግባት ።
" ሚኪ ለአልጋና ለህክምናውን ስንት ጠየቁህ በእናትህ ንገረኝ ለምን
ትደብቀኛለህ " አለች ማክዳ በልመና ።
" እነግርሻለው ማኪ ለምን እደብቅሻለው እዚህ ከ15 እስከ 20ሺህ ለጀርባ
አጥንቷ የቻይና ሆስፒታል አለ እዛ ሄዳ መታከብ አለበት " አላት ሚኪ ማክዳ እንባ
አይኗን ሞላው
" ህክምናውን ባታገኝስ ሚኪ " አለች በሚያሳዝን ቃል።
" ለምን ማኪ ? " አለ ሚኪ
" ከየት እናመጣለን ፈጣሪ በእኛ ላይ ጨክኖብናል የምንበላው ሳይኖረን በሽታ
በበሽታ አድርጎን የምንጠየቀው ብር ደግሞ ከእኛ አቅም በላይ ሆነብን ምን
አይነት ሀጢያት እንደሰራን አላወቅም ግን ጨክኖብናል " አለች እያለቀሰች
" ተይ ማኪ ፈጣሪን ማማረር ጥሩ አይደለም ለሁሉም ነገር ምክንያት አለው እሺ
" አላት ሚካኤል
" ምን ምክንያት አለው ሚጣንም እግዚአብሔር ይስጠውና ዶክተሩ ከፈለልን
አሁን ማን ይከፍለዋል ?" አለች ማክዳ
" እረ ማኪ ዶክተሩ እኮ አይደለም የከፈለልኝ ሚኪ ነው የከፈለው እኮ " አለች
ሚጣ ሁሉም ደንግጠው ተመለከቷት የሚኪ ድንጋጤ እንዴት አወቀች የሚለውና
ማንም እንዲያውቅ ባለመፈለጉ ነው ማክዳ አንዴ ሚጣን ሌላ ጊዜ ሚኪን
አየችና።
" አንቺ እንዴት አወቅሽ ግን " አለቻት ማክዳ ግራ ተጋብታ
" እራሴን ስቼ በነበረ ጊዜ እሰማ ነበር ዶክተር ማን ይከፍላል ሲሉ ሚኪ ደግሞ
እኔ እከፍላለው ግን ማንም እንዳያውቅ ሲል ሰምቼያለው " አለች ሚጣ ማክዳ
በድንጋጤ ሚካኤሌን ስታየው እሱ አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬት እያየ ነበር።
ቃልኪዳን የሆቴሉን መኝታ ክፍል በር ላይ ቆማ ተመለከተቻቸው ሁለቱም
ከወገባቸው በላይ እራቁታቸውን ነበሩ የሰላምን ፈገግታ አየችና እሷም ፈገግ
ብላ።
" በጣም የምወድህ እና የማምንህ ባሌ መጣሁልህ " አለችው እሱም ፈገግ
ብሎ ሰላምን ለቆ ወደ ሚስቱ በመሄድ ተቃቅፈው ከንፈሯን ሲስም ሰላም ደንግጣ
ስታይ።
" አንቺ አንድ ሺህ ዲያቢሎስ አንቺን ሴራ ቀድሞ ታማኙ ባለቤቴ ነግሮኛል አንቺ
የእኛን ትዳር ለማፍረስ ያሴርሽ መስሎሻል ግን እኛ ነን በአንቺ ያሴርነው ... ነይ
ውጪ ዛሬ ውርደትሽን ትቀምሺያለሽ ... " አለችና ከባሏ ጋር በመሄድ እራቁቷን
እንዳለች ከአልጋ ጎትተው አውረደዋት መሬት ለመሬት እያፏቀቁ ወደ ዋናው
መዝናኛ በርካታ ህዝብ ወደ ተሰበሰበበት ወስደዋት በሁሉም ሰው ፊት እራቁቷን
እንዳለች አቁመዋት ሴራዋን ያደረገችውን ሁሉ ህዝቡ ግማሹ የሚጠጣውን
ሲደፍባት ሌላው በጠርሙስና በጫማ ሊመቷት ሲሉ ከለከሉና ድራፍቱ ሲደፍባት
መሬት ላይ እጥፍጥፍ ብላ በመቀመጥ እንዴት መበቀል እንደምትችል ታሴር
ነበር።
ኬብሮን ከፍራሹ ላይ ተቀምጦ ጫቱን ሲቅም ማክዳ አጠገቡ ቁጭ ብላ
እያየቺው ።
" መቃም እኔም እፈልጋለው" አለች ማክዳ
" እኔን ለማናደድ ነው ወይስ ..." አለና ዝም ብሎ ሲያያት እሷም ሆስፒታል
እንደምታድር ተናግራ ብዙ ቢከራከሩም እንቢ አላት መጨረሻ ላይ የቤቱ በር
ተንኳኳ ማክዳ ሄዳ ከፈተች አታውቃትም ግን መአዛ ነበረች ገፈተረቻትና
በመግባት ከኬብሮን ፊት ስትቆም እሱ ደንግጦ ተነሳ እሷ በንዴት ስታየው
ቆይታ።
" አንተ ብስብስ ወረዳ እቺ ደግሞ ማን ነች ... እኔን አስረግዘህ ከሌላ ሴት ጋር
አሸሼ ገዳሜ....." ስትለው ኬብሮን ብድንጋጤ ከተቀመጠበት ተነስቶ እያያት
" ምን?.... አስረግዘህ ነው ያልሺው " አለ ሰውነቱ እየተቀጠቀጠ.........

ይቀጥላል



╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
50 viewsĴozzz , 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-28 14:31:56 ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 16

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
አንዲት ቆንጅዬ ባትባልም የማታስጠላው የቶማስ ባለቤት በቤቷ ውስጥ
ከልጆቿ ጋር ትጫወታለች ። በዚህ ወቅት የሞባይሏ ስልክ ጮሀ ልጆቹን መጣው
ብላ በመሄድ የደዋዩን ስልክ ቁጥር አየቺው አታውቅም ለደቂቃ በዝምታ
አየቺውና አንስታው ወደ ጆሮዋ ወሰደችው።
" ሀይ ቃልኪዳን " በስልኩ ውስጥ እንደ እሳት ጆሮን ከሚያቃጥለው ሀይለኛ ሳቅ
በኋላ የመጣ ነበልባል ቃል ነበር
" እግዚአብሔር ይመስገን ..... አላወኩሽም ግን " አለች ቃል በተረጋጋ ስሜት ያን
እሳት የሚያጠፋ ንግግር።
" ጨዋ ነኝ እያልሽ ነው ነገሩ ጨዋ ነሽ .... እእእ ለማንኛውም ሰላም እባላለው
የባልሽ ሚስት ነኝ " አለች ሰላም እንደገና ወላፈን የነበረውን ቃል እረጭታ እሳት
የሆነውን ሳቋን አስከተለች ቃል የእሳቱ ወላፈን ጆሮዋን ለበለባት ሞባይሏን
ከጆሮዋ ላይ አነሳቺውና ለደቂቃ ዝም ስትል ሰላም ንግግሯን በመቀጠል "
ምነው ደነገጥሽ እንዴ ሞኛ አፍቃሪ "
" አልገባኝ ምን ለማለት እንደፈለግሽ " አለች በድንጋጤ ቃል
" ምን አልገባሽም ገብቶሻል ባክሽ .... ግን በደንብ እንዲገባሽ ማታ
እደውልልሽና ነይ እምልሽ ቦታ ትመጪያለሽ " አለች ሰላም ዘና በማለት
" አልመጣም ምን ስለሆንሽ ነው የምመጣው " አለች በንዴት እና በቁጣ ቃል
ኪዳን ።
" ተረጋጊ አትናደጂ ቶሎ ታረጂያለሽ .... እእእ ሽበት በሽበት ትሆኚያለሽ እንደዛ
ከሆንሽ ደግሞ በራስሽ ፍቃድ አሁንም አስጠሊታ ነሽ በጣም ታስጠዪና ቶሚን
አሳልፈሽ ትሰጪኛለሽ ስለዚህ አትናደጂ " አላቻት ሰላም
" የሰው ባል ማማገጥ ወግና ቁም ነገር አርገሺው ደውለሽ የምትለፈልፊው
ክብረ ቢስ ለማንኛውም ባሌን እወደዋለው አምነዋለው የእኛ ቤት እና ምሰሶ
በእንደአንቺ አይነት ወሬኛ አይፈርስም አይናጋም እሺ ልክስክሷ ደግሞ
አላምንሽም "
" እኔ ጨዋ ስለሆንኩ ስለ ባልሽ ብልግና በጨዋ ደንብ ደውዬ ሳናግርሽ አንቺ
ትሳደቢያለሽ እሺ ይሁን ለማንኛውም እኔን አትመኚኝ ለማመን ከፈልግሽ ማታ
ሆቴሉን ካወኩ በኋላ ደውዬ እነግረሺና ከፈለግሽ መጥተሽ ማየት ትችያለሽ እሺ"
" እንቢ አልሰማሽም የኔ ባል ጨዋ ነው እሺ እንደአንቺ ወሬ እያወሩ ቤትን
የሚያፈርሱ በf.b የሌለ ወሬ እያወሩ ሀገር የሚበጠብጡ እቺ ሀገር አላጣችም
ስራ ሰርቶ እንስራ ፍቅር ሰብኮ አንድነትን ተናግሮ ሀገር የሚያሳድግ ነው
ያጣችው እሺ እንዳትደዊ ሂጂና ተልከስከሺ ልክስክስ " አለችና ቃል ኪዳን
ስልኩን ዘጋቺው። ሰላም የቃልን ስልክ መዝጋት እንዳወቀች ከት ብላ ሳቀቺና ።
" እስቲ እኔ ምን ላርግ ምን አድርግ ትሉኛላቹሁ በፍቅር የተሞላ ትዳር በእምነት
የጎለበተ እና የጠነከረ የትዳር ምሰሶ ሳይ ያመኛል ያቅለሸልሸኛል እራስሽን
አጥፊ አጥፊ ይለኛል በቃ ይሄ ትዳር መፍረስ አለበት ።" አለችና ሳቀች።
በሆስፒታል ውስጥ ሰርካለም አይሲ ክፍል ውስጥ እራሷን እንደሳተች ነች ሚጣ
ኮሪደሩ ላይ ባለ አንግዳሚ ወንበር ላይ ጋደም ብላ ጭንቅላቷን ከማክዳ ጭን
ላይ አድርጋለች ። ማክዳ አንገቷን ዘወር አድርጋ ከእነሱ ትንሽ እራቅ ብሎ ስልክ
የሚያናግረውን ኬብሮንን በቅናት ታየዋለች ። ኬብሮን በንዴት ስልክ ከመአዛ ጋር
ስልክ ያወራል ።
" ቆይ አንቺ አፍቅረኝ እንጂ ያልሺኝ ብር ስለላክሺልኝ እኔነቴን ልግዛህ ነው እንዴ
ያልሺኝ በጣም አማረርሺኝ ተዬኝ እባክሽ" አላት ኬብሮን በንዴትና በምሬት ።
"ቆይ ምን አልኩሁ ማን ነች ጎሮቤትህ ብዬ መጠየቄ ያናዳል"
" መጠየቅሽ አያናድድም ግን ነገርኩሽ ከደረጃ ላይ ወድቃ ሀኪም ቤት ወስደናት
ነው ስሟም ሰርኬ ትባላለች አልኩሽ በቃ ሌላ ጥያቄ መጠየቅ ባላስፈለገሽ "
አላት በኬብሮን
" ሰርኬ ማለት ምን አስፈለገ ለምን ሰርካለም አትልም " አለች በቁጣ መዓዛ ።
" አንቺ መቼም አይገባሽም ሲገባሽ ደውይ እንዳልል ስለማይገባሽ ትቼዋለው
ቻው " ብሏት ስልኩን ዘግቶ ማክዳን ተመለከተ በንዴት እያየቺው ነበር
እንደማፈር ብሎ አንገቱን ደፍቶ ወደ እነሱ ሲሄድ የዶክተር ቢሮ ተከፈተና ሚካኤሌ
ሲወጣ ሁሉም ወደ እሱ እየሮጡ " ሚኪ ዶክተሩ ስለ ሰርኬ ምን አሉህ?" አሉት።
ምሽት በአንድ ሆቴል ሰላምና ቶማስ ተቀምጠው እየጠጡ አብረን እናድራለን
እያለች እሷ እሱ አላድርም የማይሆን ምክንያት ለሚስቴ ሰጥቼያት ነው
የማመሸው እያላት ቢከራከሩም በመጨረሻ በእሷ አሸናፊነት ንግግራቸው
ተቋጨ እና አልጋ ለመያዝ ብላ ወደ ውስጥ ገባች ከአንድ አስተናጋጅ ጋር
ስታወራ ቆይታ ቁልፍ ተቀብላ ብር ሰጠቺውና ከእሱ ዘወር ብላ ለቃል ስትደውል
ስልኩ እንደተያዘ ምልክት በተደጋጋሚ ሲሰጣት በሆነ ቦታ ተደብቃ ቶማስን
ስታየው እሱ ደውሎላት እንደሆነ ገባት ካለችበት ሆና ፎቶ አነሳቺው እና ሆቴሉን
የመኝታ ክፍሉን ቁጥር ፅፋ እንድታይም ጋብዛት በሜሴጅ ላከችላት።
ከደቂቃዎች በኋላ መኝታ ክፍል ገብተው ልብስ እያወላለቁ እሷ አንገቱ ስር
እየሳመቺው አልጋ ላይ ወደቁ።
በዚህ ወቅት ቃል ኪዳን መኪናዋን ከሆቴሉ በር አቆመቺው በፍጥነት ወርዳ ወደ
ውስጥ በመግባት ቀጥታ ወደ ላከቺላት መኝታ ክፍል በመሄድ ከፍታ ስትገባ
እራቁታቸውን ሆነው አልጋ ላይ አገኘቻቸው ሰላም ፈገግ አለች።......

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥


ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 17
41 viewsĴozzz , 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-27 21:58:14 ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 15

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
ሰርካለም በእንባ እረጥባ አንገቷን ደፍታ ከቢሮው ስትወጣ ባለቤቱ በር ላይ ቆሞ
በሀዘን ተመለከታትና አንገቱን በእፍረት ደፋ ዝም ብላው ልትሄድ ስትል እጇን
ያዘና ስሟን ጠራት ዘወር ብላ አየቺውና።
" ይቅርታ አላቀዬ .... እኔ ቆሻሻ ሽንት ቤት ጠራጊ ነኝ ... እሸታለው እገማለው
በሽተኛ....... "እያለች እያለቀሰች ስታወራ
" ሰርካለም ..." አለ በጩሀት ንግግሯን ስታቆም እሱ ቀጠለ " ...አየሽ እቺ አለም
ገብቶቸው ከሚኖሩ ሳይገባቸው የሚኖሩ እጅግ የበዙ ናቸው እሷ መስሏት ነው
አንቺን የሰደበች ግን የፈጣሪን ምርጡን የሰው ልጅ ነው የሰደበችው ... ሌላው
ልዩነታቹሁ ገንዘብ ነው እሱ ቀኑን ጠብቆ ይመጣል በተረፈ በየወሩ ደመወዝሽን
በባንክ እየሄድሽ ውሰጂ ግድ የለም .." አላትና ንግግሩን አቁሞ እጇን ለቀቃት
ስቅስቅ እያለች እያለቀሰች ወጥታ ስትሄድ እሱ ወደ ቢሮው በመግባት ሰላምን
ዝም ብሎ ሲያያት ቆይቶ።
" ምን ያህል ደስታ ይሰጥሻል የሰው ስቃይ የድሀ ለቅሶ " አላት ቶማሰ ወደ
ወንበሩ በመሄድ እየተቀመጠ።
" ደስታ ሳይሆን እርካታ ነው የሚሰጠኝ እጅግ እረካለው አንተም ባትፈልግም
ያልኩሁን ስላደረክ ዋጋህን እከፍለሀለው ማታ እንገናኛለን " አለችው ወደ እሱ
ተጠግታ ከተቀመጠበት በሁለት እጆቿ ትከሻ እና ትከሸዋን ይዛ በማንሳት
ከንፈሯን ወደ ከንፈሩ እያስጠጋች
" ከእኔ ከአናቴ ላይ ውረጂ.... እኔ በጣም የምወዳት የማፈቅራት ሚስት አለችኝ
ልጆችም በየደቂቃው የሚናፈቁ አሉኝ ተይኝ ተይኝ እባክሽ " አላት ቶማስ በጠቋሚ
ጣቱ በጡቶቿ መሀል ባለው አካፋይ ደረቷን እየነካ ወደ ኋላ እየገፈተራት ።
" እኔ ቆሻሻ ድሀ አይደለሁም አትገፍትረኝ ...... ሚስትህ ከእኔ የበከለጠች ቆንጆ
ነች እዛ ላይስ?...." አለች ወደ ጆሮው ተጠግታ በማሾካሾክ ቃላቶቿን ዘርግፋ
ሰጨርስ ጆሮውን በስሜት በመምሰል እየነከሰች።
" ቁንጅና መለኪያዬ አይደለም ይሄ ለሰው የሚታይ ለሴጣን መግቢያ በር የሆነን
ቁንጅና እኔ አልፈልግም ..... ቢሆንም አንቺን እሷንጨዠ ከማግባቴ በፊት
አውቅሻለው ግን ምርጫዬ አንቺ ሳትሆኚ እሷ በመሆኗ አገባኋት ያ ማለት
በሁሉም ትበልጥሻለች " አላት በኩራት
" ቀልድህ ባያስቀኝም እዝናናበታለው .... ለማንኛውም ተርቤያለው ማታ እንገናኝ
" ብላው በሩን ከፍታ ስትወጣ
" አንዱን ጥፋት በሌላ ጥፋት በፍፁም ማረም አልፈልግም" አለና መልሶ
ከወንበሩ ላይ ተቀመጠ ።
ፀሀይ በሰማይ መሀል በሰው ልጅ አናት ትክክል ወጥታ ከላይ እንደ እሳት
እያቃጠለች ከስር አስፓልቱ የጋለ ብረት ምጣድ መስሎ ሰዎችን አዋጅ የታወጀ
ይመስል መንገዱ ሰው አልባ ሆኖ በየቤቱ የከተመበት ሚስጥር እንደ እሳት
እያነደደችና እያቃጠለች ያለችው የምሳ ሰአት ፀሀይ ናት ። ሰርካለም ይሄ ንዳድ
አልተሰማትም ጭራሽ በረዶ የተደፋባት ይመስል ቀዝቅዛለች አይኗ በርበሬ
መስሏል በህፍረት ተሸማቃ በድህነቷ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍራና አንገቷን ደፍታ
በፍጥነት ወደ ቤት ትሄዳለች ። እቤቷ ደርሳ ሽጉጥ ቢኖራትና ሚካኤሌን
ብትገለው በወደደች ደስም ባላት ነበር ግን የላትም ይሄ ሁሉ ነገር የመጣው
በእሱ ነው ።
ሰርካለም እንኳን ሰላምን ለመሳሰሉ ከምላስ ሌላ አቅም ለሌላቸው ቀርቶ
ለወንድ እንኳ የማትደፈር ማንንም ለማቀጥቀጥ ወደ ኋላ የማትል ልጅ ነበረች ።
አሁን ግን ህይወቷ ልትሰጣት የምትችል ሚጣ አለች ለእሷ ክብሯን አይደለም
ነፍሷን ካለ ስስት ትሰጣለች አዎ ዛሬ ሰላም ያዋረደቻት ስለ ልጇ በምትኖርበት
ጊዜ ስላገኘቻት ነው ።
ሰውነቷ ወባ እንደያዘው አሊያም ብርድ እንደመታት እየተቀጠቀጠ ነው መንገዱ
እንደ ዛሬ እረዝሞባት አያውቅም በጣም ትራመዳለች ግን ተጎዛውም እዛ የሆነች
ይመስላታል ።
ሚካኤሌ ከቤቱ ኮሪደር ዳር ላይ ተቀምጦ ንፋስ እየተቀበለ ሳለ ማክዳ
በመምጣት ሰላም ካለቺው በኋላ ኬብሮን እንደናፈቃትና እንዳለ ጠየቀቺው
እሱም መኖሩን ሲነግራት ወደ እነሱ ቤት ገብታ ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ሁለቱም
እየተከራከሩ ወጡ እና ሚካኤሌን እንዲያስማማቸው እየጠየቁት ሳለ ሚጣ
ከቤት በመውጣት።
" አክስቴ እርቦኛል ምሳዬን ስሪልኛ....." አለችና ሚካኤሌን እንዳየቺው ".......
ጋሼ ምነው እቤት መጥተህ አትጠይቀኝም እንዴ? " ብላ ደረቷ ላይ የተለጠፈውን
ፕላስተሩን በእጇ ይዛ እየሮጠች ወደ እነሱ ስትመጣ ቀስ እንድትል ነገሯትና
ማክዳ ይቅርታ ጠይቃ ምሳ ለመስራት ገባች ።
ሚካኤሌ ኬብሮንና ሚጣ ሆነው እየተሳሳቁ እያወሩ ለደቂቃዎች እንደቆዩ
ሰርካለም ከመንገድ በመምጣት ደረጃውን ወጣችና ልክ እንዳየቻቸው በንዴት
ፊቷ ተለዋወጠ ሚጣ ዘወር ብላ አየቻት ስትጠራት ሚካኤሌ ከመቀመጫው
ብድግ ብሎ ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል ሰርካለም በቆመችበት አዙሯት ወደቀች
ከደረጃው ላይ እየተከባለለች ወርዳ ለእጀታ ተብሎ የተሰራው ብረት ያዛት ፊቷ
አፏ ደም በደም ሆነች።

ይቀጥላል....

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
44 viewsĴozzz , edited  18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-19 16:27:31 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 14

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
በወ/ሮ ተዋቡ ንግግር እና ሁኔታ ኬብሮን ግራዋ እንደጠጣ ሰው አፍ እሬት እሬት
አለው እሳቸው ተናግረውት ጆሮው የሰማው ነገር በጆሮው ውስጥ መግል
የተቋጠረ መሰለው በግርምት ዘወር ብሎ አያቸውና ተመልሶ ፊቱን አዙሮ ።
" ውይ ውይ ውይ የት አባቴ ሄጄ ልደበቅ ይሆን ?" አለ እሱ ሳይሰሙት በቀስታ
ማውራቱ ነበር ። እሳቸው ግን ሰምተውታል።
" የትም ይሁን አንተ የተመቸህ ቦታ ይመቸኛል " አሉ ፈገግ ብለው ስልሳ አመት
እድሜ የበላውን ወገባቸውን እና ዳሌያቸውን እያወዛወዙ።
" ምኑን ? " አለ በድንጋጤ ዘወር ብሎ ተመልክቷቸው
" የት ሄደን እንደበቅ አልከኝ እኮ አይደል የኔ ማር "
" ማ ... እኔ.... እኮ እኔ ከርሶዎ ጋር ... አይቀልዱ እኔ አሁን የሚጣን ጤንነት
ለመጠየቅ ነው አመጣጤ " አለ በመጀመሪያ በግርምት በመቀጠል ኮስተር
ብሎ። እሳቸውም እርሶዎ በመባላቸው በጣም ተናደው ።
" አኔተ ማንን ነው እርሶወ ያልከው እኮ እኔ ተዋበች በፍቅሯ ስንተ ገዳያን እ...እ
እኔና አንተ ምን ያህል ተበላልጠን ነው እኔን እርሶዎ .... ና ና አልጋ ላይ
ሞክረኛ.....?" አሉ ወገባቸውን ይዘው አንዴ ጡታቸውን ሌላ ጊዜ እሱን እያዩት
በኬብሮን በተናገሩት አፍን ምራቅ ወደ ላይ ሊለው እየተናነቀው እንደሆነ በእጁ
ምልክት አሳይቷቸው አፍን ይዞ ወደ ቤቱ በመሮጥ ሚካኤሌን ገፍትሮት ወደ ቤት
ገባ እሱም ወደ እሱ እንዳይመጡ ብሎ ተከትሎ ገባ።
" ውይ የኔ ቆንጆ የኔ ማር ምነው እኔን ለእኔ ይሁን ....." እያሉ ትንሽ ተከተሉትና
ሚካኤሌ ገብቶ በሩን ሲዘጋ ባሉበት ቆሙ።
" እኔማ ከዚህ በኋላ ከእዚህ ቤት ሴቶች ካልጠፍ አልወጣም እስቲ አስበው ....
ሚኪ እኔ ልሙት አላየሀቸውም በግድ ወጣት ልሁን ያሉ በሜካፕ ያሸበረቁ
የልብስ ቤት አሻጉሊት ነው የሚመስሉት ደግሞ የኔ የእናቴ የታላቋ ታላቅ እህት
ነው እኮ የሚመስሉት እንዴ ሆሆሆሆ ጭራሽ አልጋ ሞክረኝ ... እኔ የምልህ ሚኪ
ወይ እኔ አረጅቼ ይሆን?....... በቃ ተወው አንተ እንዴት ትነግረኛለህ " አለው ግራ
በመገባት መሬት ላይ በተነጠፈው ፍራሽ ላይ ወጥቶ በመከባለል።
" ኬቡ ከሴት ለመራቅ ብዙ ነገር አደረክ ግን አራቁሁም አይደል ሴቶቹ ታዲያ
ለምን እራስህን አትጠብቅም " አለው ወደ አንዱ ሶፋ ላይ በመሄድ እየተቀመጠ።
" ማለትህ ... ማለቴ ምን ለማለት ነው "
" በቃ እራስህን ጠብቅ ፀዳ ነፃ በል እንደዛ ሆነህ ደግሞ እየው አይሻልም " አለ
ኬቡ ግን መልስ አልሰጠውም። በር ደጋግሞ ተንኳኳ ኬቡ ከተጋደመበት
በመነሳት ሄዶ ከፈተ በፍፁም ያልጠበቀው ወሮ ተዋቡ ነበሩ እንዳያቸው ሊዘጋው
ሲል ያዙበትና ።
" ምነው ተሻለህ ልልህ እኮ ነው የመጣሁት ..... እያመመህ ከሆነ ሆስፒታል
ይዤህ ሊሂድ ?" አሉት እየተቀለሰለሱ እሱ በድንጋጤ አያቸውና
" ማ ... ማንን .... እኔን .....ግድ የለም ደህና ነኝ " አለ መልስ ሳይጠብቅ በሩን
ዘጋው ዘወር ብሎ በሩን ተደግፎ ሚካኤልን ሲያየው አፍን አፍኖ ክትክት እያለ
ሲስቅ አየው።
" ምን እንደተረዳሁ ታውቃለህ .... በቃ የፍርድ ቀን እንደደረሰ በቃ እኛም ጫትና
ሲጋራችንን ሳንተው ሰው ማማትን መግደል ሳናቆም ሴቶችም እኔን ማበሳጨት
እነ እማማም ወጣት ማማለላቸውን ሳያቆሙ ጌታ ለፍርድ ሊመጣ ነው እከሌ
ከእከሌ የለም ተጠቅልለን ወደ ሲዖል የእኔ ነገር በምድርም በሰማይም ተቃጥዬ
እችላለው .... ወይኔ እኔ እኮ ገምቻለው ህዝብ በህዝብ ላይ ሲነሳ መንግስት
በመንግስት ላይ ሲነሳ ጠርጥሬ ነበር እኔን ብሎ ደራሲ ቂጣ የማያባላ ከልመና
የማያስወጣ ... መቼም ተረግሜ ነው ካልጠፋ ሙያ ብሽቅ ነኝ ...." በሀይል
ተነፈሰና ፍራሹ ላይ በጀርባው ወደቀ።
ሰላም በአንድ የግል ድርጅት ቢሮ ውስጥ ከድርጅቱ ባለቤት ጋር ተቀምጣ
ታወራለች። ለበሩ ጀርባዋን ነበር የሰጠችው የድርጅቱ ባለቤት ፊት ለፊት
ተቀምጧል ወንዳ ወንድ የሚያምር ወጣት ነው። ሰላምን በትኩረት ሲያያት ቆይቶ
ሁለቱን እጁ ጠረጼዛው ላይ በማድረግ ።
" ሰላም ቆይ ምን አርጋሽ ነው ድሀ እኮ ነች ሰርታ ብትበላ ምን አለበት " አላት
በትህትና።
" ምን አለበት አልኩ ግን ድሀ ሰው ያስጠላኛል እነሱን ሳይ ወደ ላይ ወደ ላይ
ይለኛል ይቸናነቀኛል የሆነ ነገር ቢቀቡም ባይቀቡም ይገሙኛል .... እህል እራሱ
አይገባልኝም የሚቀቡት እርካሽ ቅባት ወይም ዶዶራንት ስለሆነ አጠገቤ ሲሆኑ
አስክሬን አስክሬን ይሉኛል .... " አለች በጥላቻ
" ሰላም እንደዚህ አይባልም ሁሉም እራሱን የሚጠብቀው አቅሙ በፈቀደው
በቻለው መጠን ነው ስላልገባን እንጂ እነሱም ያለ እኛ እኛም ያለ እነሱ ምንም
ነን " አላት እሷ በአሽሙር ፈገግ ብላ ።
" እኔ ያልገባኝ ሰው አይደለሁም በደንብ የገባኝ ነኝ አሁን የምልህን ታደርጋለህ
ወይስ አታደርግም ?" ብላ ስትጠይቀው የቢሮው በር ተንኳኳ እና ሰርካለም
ገባችና።
" ይቅርታ ፈልገውኝ ነበር መሰለኝ " አለች በትህትና ሰላም ጀርባዋን ስለሰጠች
አላየቻትም ነበር ። ሀላፊው በአዎውንታ ጭንቅላቱን ሲነቀንቅ ሰላም ዘወር ብላ
ስታያት ደነገጠች የድርጅቱ ባለቤት ከተቀመጠበት በመነሳት ።
" ይቅርታ ሰርካለም የፈለገችሽ እሷ ነች አዝናለው ..... ሁለታቹሁ ለብቻቹሁ
እንድታወሩ ትቼያቹሁ ልውጣ " አለና በሩን ከፍቶ ወጣና በሩን ዘጋው።
ሰላም ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ እሷ ልትጠጋት አለችና በመጠየፍ ስሜት
ባለችበት ቆመች በእጇ አፍንጫዋን ያዘች ።
" እንኳን ተጠግቼሽ እዚህ ሆኜ እንኳ ጠረንሽ አናቴን አናወጠው በጣም ነው
የምትሸቺው ... እህ ይሄን ጠረን ይሄን ስራ ይዘሽ ነው ከሚኪ ጋር አብሮ መተኛት
ያለምሺው " አለቻት ሰርካለም እልህ ተናነቃት አይኗ እንባ አቆረ ንዴት ጫቃዋ
ላይ እንደ ሸክም ከበዳት ።
" ..... አየሽ ሴት ምንም አቅም እንደሌላት ለሚያስቡ ሁሉ የአቅሜን ጫፍ
አሳያለው ለአንቺም ጨምሮ......." እያለች ሰላም አንድ ጊዜ በስድብ ሌላ ጊዜ
በሟቋሸሽ ስትሰድባት ሰርታ ለልጇ መኖር ስላለባት እንደ ጎርፍ በጉንጯ ላይ
እያነባች ሰማቻት ግን በመጨረሻ ከስራ አበረረቻት ሰርካለም ወደ ቤት ሄዳ
ሚካኤሌን ሜን እንደምታደርገው ታስብ ነበር..

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
72 viewsĴozzz , 13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-15 21:43:24 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 13

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
የሰላም ባል አድማሱ ወደ ቢሮዋ ግራ በመገባት ስሜት ውስጥ ሆኖ በመሄድ
በሩን አንኳኩቶ በመክፈት ገባ እና መልሶ ዘጋው ። በንዴትና በተረበሸ ስሜት
ውስጥ ሆና በጨረፍታ አይነት ስሜት ተመለከተችው ። እሱም አያትና
" ስሜትሽ ጥሩ አይመስለኝም " አላት
" ያልበላህን አትከክ ...... ለመሆኑ ሰራተኞቹን አሳምንካቸው "
" ሁሉም አምፀዋል ሌላ ድርጅት ስራ ጀምረዋል "
" ሲጀመር አንተ እራስህንም ማሳምን አትችልም .... በፍጥነት ሌላ የስራ
ማስታወቂያ አውጣልኝ እና ቶሎ ብለህ ቅጠርልኝ እሺ አሁን ጨርሰናል ከቢሮዬ
ውጣልኝ " አለችው በቸለልተኛ ስሜት ። እሱ በግርምት ተመለከታት እና ።
" ኬብሮን ከዚህ ሲወጣ አየሁት ምን አዲስ ነገር አለ ?"
" ከጎሮቤቱ ጋር ሰርካለም ከምትባልዋ ጋር ፍቅር ጀምሯል የምትሰራበትን ቦታ
ነግሮኛል የቅርብ ጓደኛዬ ነው ከስራ እንዲያባርራት አሁኑኑ ሄጄ እነግረዋለው ድሀ
ለድሀ ከዛ አብረው እንዴት መሄድ እንደሚችሉ ቁጭ ብሎ ማየት ነው"
" ግራ የገባኝ ነገር የሁለቱ መፋቀር አለመፋቀር አንቺን ምን አስጨነቀሽ "
በግርምት ሲያያት ከቆየ በኋላ ።
" ምንም ነገር እንዲሳካለት ስለማልፈልግ የእሱ ስኬታማ መሆን ለእኔ ውድቀት
ነው ...... ይሄ የእኔ ጉዳይ ነው"
" አሀ ዛሬም ድረስ ሚካኤልን ታፈቅሪዋለሽ ማለት ነው ?" አላትጨአይን አይኗን
ሲያያት በንዴት እና በብስጭት አየቺውና ።
" እኔ እኮ ከእንዳተ አይነት ጨው እራስ ጋር አብሬ መሆኔ ነው የሚያናድደኝ .....
ውጣልኝ ከዚህ አሁን " ቃላቶቿ ብስጭት እና ንዴት ያዘሉ ባይሆኑም ከውስጧ
እንደ እሳት የሚነድ ንዴት ውስጥ እንደሆነች ፊቷ ያሳያል።
" እንደዚህማ ልታቋሺሺኝ እንደ ቆሻሻ ከቢሮሽ እንድትጠርጊኝ እና እንድታስወጪኝ
አልፈልግም ... በዚህ ድርጅት በጠቅላላ በሀብት ንብረትሽ የኔ ድርሻም
ሀላፊነትም አለብኝ " አላት አድማሱ የእውነት አናደዋለች ከሚካኤሌ ይህንን ሁሉ
ሀብት ዘርፋ እጇ ስታስገባ ከጥንስሱ ጀምሮ የበለጠው ሴራ እንደውም የእሱ
ነበር ይሀው አሁን ካገኘች በኋላ ተጋብተን አብረን እንኖራለን እንዳላለች አሁን
እንደ ምራቋ ሀክ ቱፍ ብላ እየተፋቺው ነው ካለ ምንም ጥቅም። ሰላም ደግሞ
የእሱ እንደዚህ ማለቱ እንደ ፌጣ ከተቀመጠችበት ፍንጥር ብላ በመነሳት
አይኖቿን አፍጣ ከንፈሮቿ እየተቀጠቀጡ።
" አቤት ... ምን አልክ አለህበት እንዴ? አንድ ብር አይደለም አንድ ሳንቲም ላይ
የለህበትምም አታገኝም " አለች በንዴት
" እረ ያ ማለት ከእኔ ጋር የመኖር ልጅ የመውለድ እቅድ የነበርሽን ሁሉ
ሰርዘሺዋል ማለት ነው " አላት ተስፋ ቆርጦ።
" እረ በፈጠረህ ሲጀመርም ከአንተ ጋር ለመኖር ፍላጎትም የለኝም እንዲሁ
እንድታልመው ብዬ ነው እሺ ልጅህን ያው ከአዳሪ ትምህርት ቤቷ ለዕረፍት
ስትመጣ አንተም እየመጣህ እያት እፈቅድልሀለው ከዛ ውጪ የእኔን አይን
እንዳታይ ውጣልኝ " አለች የመጨረሻውን ቃል እንደ መብረቅ እየጮሀች
አቧረቀችበት።
" እወጣለው ግን አንድ ነገር ልንገርሽ " አላት ወደ እሷ ጠጋ ብሎ።
" አትንገረኝ ስለ ልጃችን ረድኤት ልትነግረኝ ነው እሷን ከአንተ ጋር ተኝቼ
መውለዴ አይፀፅተኝም ለምን ያኔ የምበላው ያጣው ድሀ ነበርኩ አንተ ደግሞ
ከየትም ብለህ ይሄን ችግሬን የምትሸፍንልኝ ስለዚህ ማድረግ ያለብኝን አርጌ
ልይዝህ ይገባ ነበር ያስኩሁ እና ተጠቀምኩብህ አሁን ግን ያ ሁሉ አልፏል ከፊቴ
እንድትርቅ ነው የምፈልገው አንተ አትመጥነኝም የሚመጥነኝ ሰው እፈልጋለው "
አለች እሱ እንዲበሽቅ ያልመጣባትን ያላስቸገራትን ሳቅ በግድ እየሳቀች እሱ ግን
አልተናደደም ፈገግ አለና ።
" ትልቅ ስህተት ተሳሳትሽ ይሄ ስህተትሽ ደም ያስለቅስሻል ከሚኪ ይህንን ሀብት
የቀማሁበትን ሴራ ጠንከር አርጌ ወደ አንቺ አዞረዋለው እመኚኝ ለማንኛውም
ደህና ሁኚ " ብሏት በንዴት በሩን ከፍቶ ወርውሮት ሲዘጋው እሷ ቀሀይለኛው
እየሳቀች ነበር።
ኬብሮን ከመአዛ ጋር በስልክ እያወራ ሲለው በግርምት ሲስቅ ሲለው ደግሞ
ሲናደድ አጠገቡ አብሮት እየተራመደ በሚናገረው ነገር እየሳቀበት ያለውን
ሚካኤሌን እያየው ሲያወራ ቆይቶ በመጨረሻ በሰላም ስልኩን ዘግቶ ሚካኤልን
ተመለከተው እና
" እኔ የምልህ ሚኪ 100 ቁጥር ሚስማር አለ እንዴ " አለው።
" ደሞ መቶ ቁጥር ሚስማር አለ እንዴ? " አለው በፈገግታ።
" ለምን አያመርትም ፋብሪካዎች ቢኖር ወደ እኔ የሚመጡቱን ሴቶች እግራቸውን
በአናፂዎች በደንብ ነበር እግር ከእግራቸው አቆላልፌ የማሳስረው አፋቸውንም
ከእኔ ጋር ብቻ እኔዳያወሩ አርጌ በሀሚር የማጣብቀው "
" ተው አይባልም አንድ ቀን ያስፈልጉሀል ኬቡ " አለው
" እረ መቼም አያስፈልጉኝም ምንምም አልፈልግም እነሱ ... ሆሆ እነሱ " አለው
በምሬት ። ግን ቤታቸው ደርሰው ደረጃውን እየወጡ ስለነበር ።
" ይልቅ ይሄ የማይረባ ወሬህን ተወውና አሁን እኔን እናቷ ስታየኝ ስለምትሳደብ
አንተ አንኳኳና ስለ ልጅቷ ጤንነት ጠይቅ እሺ እኔ እውነት ደብሬያት ከሆነ ክችች
ማለትን ስላልፈለኩ ነው " አለው በትህትና
" አንተን እናትየው ብቻ ነችጨእኔን ግን እህትየውም ጭምር ነች በምን ጫቃዬ
እችላለው አልሄድም " አለ በብስጭት
" የአንተ እህትየው የፍቅር ነው እባክህ " ብሎ ለደቂቃ ሚካኤሌ እየለመነው
ኬብሮን ቀእንቢታ ቆየና በመጨረሻ እሺ ብሎት ሚካኤሌ ወደ በራቸው እየሄደ
ኬብሮን ሁለት ጊዜ ሲያንኳኳ ሰርካለም እንቢ አላረጅም ያለች አክስት አለችኝ
ያለችው ሴትዮ ወ/ሮ ተዋበች መጥተው ከፈቱ። እድሜያቸው 60ዎቹ አጋማሽ
ላይ ይሆናሉ ፊታቸው በሜካፕ ፀጉራቸው በቀለም ተለውጧል ከአይናቸው ኩልና
ከከፈራቸው ቀይ ሊፒስትክ አብዝተው ተለቅልቀዋል በጡት ማስያዣ በትንሹ
ጡታቸው እያሳዩ ወጥረውታል በቦዲ ሰውነታቸው ተገላልጧል አጉልበታቸው
በላይ የሆነ ጉርድ አርገዋል ። ብርድ ልብስ የሚያክል ማስቲካ በአፋቸው ውስጥ
እያላወሱ ያቋቁታል ። ኬቡን እንዳዩት ።
" እንዴት ነው የምታምረው የኔ ቆንጆ " አሉት በፈገግታ ከጉልበታቸው ሰበር ሰካ
እያሉ በፈገግታ ። ኬብሮን ደነገጠ ዙሪያውን አየና ሚካኤሌን ሲያየው እየሳቀ ነው
የእሱም ሳቁ መጣ በግርምት እየሳቀ አያቸውና ።
" እኔን ነው?" አለ በጣቱ ጭምር ወደ ልቡ እያመላከተ።
" አዎ የኔ ፍቅር ቅመም የሆንሽ ልጅ ትመስይኛለሽ ግድ የለም በምቾት ስቃይህን
አሳየሀለው ብቻ እንመቻች " አሉት። ኬብሮን የምር ደነገጠ ግራ ተጋባ ፊቱን
ዘወር አርጎ።
" ጌታዬ ሆይ የባስ አታምጣ " አለና ሚኪን አየው። ....

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
72 viewsZizu, 18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-14 19:14:54 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 12

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
ዝምታ የዋጠው ምሽት። ቀዝቃዛ አየር የውሻ ጩሀት እንደ ዜማ ። ከርቀት
ደግሞ እንደ የጀርባ ሙዚቃ (sawond Track) ከሆቴሎች ከጭፈራ ቤቶች
የሚሰማ ሙዚቆች አሉ።
ለሊቱ የጭንቀት የሀሳብ የሆነባቸውም አሉ ሚካኤሌ ሰርካለም እና እህቷ ።
በየትኛውም አንግል ቢታሰብ የህፃን ልጅ ስቃይ ህመም ማንኛውንም ሰው
ያሳስባል።
ሚካኤሌ የሚጣ ነገር አሳስቦት አልጋ ላይ ቁጭ እንዳለ ለሊቱ እየተገባደደ
ባለበት ሰዓት ሞባይል ስልኩ ጮሀ ። አነሳውና ማናገር ጀመረ ።
" ሚካኤሌ እንኳን ደስ አለህ " አሉ ዶክተር ከሆስፒታል ደውለው። ሚካኤሌ ፊቱ
በደስታ በራ መልስ ከመስጠቱ በፊት ቀና በማለት ፈጣሪውን አመሰገነ።
" ዶክተር እንኳን አብሮ ደስ አለን በሰላም ተጠናቀቀ " አላቸው
" አዎ ወንድሜ ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን .... እድሜ ለአንተ " አለው ዶክተሩ ።
" አይ ዶክተር እኔ ምን አረኩ ዋናው ፈጣሪ ነው ከዛ እርሶዎ "
" አይ ሚካኤሌ እቺ ልጅ ይህን ያህል ብር ባታገኝ ኖሮ እኮ በቃ ህይወቷ
አብቅቶለት ነበር " አለ በማዘን ዶክተር
" አይሳሳቱ መቼም አያበቃም ነበር ለምን ፈጣሪ ያብቃ አላለም እሱ ያብቃ
ቢልም አሁንም ያበቃ ስለነበር ለማንኛውም ትልቁ ነገር ልጅቱ ወደ ጤንነቷ
መመለሷ ነው ደስ የሚለው ይሄ በቂ ነው ዶከተር "
" ለምንድን ነው ግን አንተ እንደከፈልክ እንዳይታወቅ የፈለከው "
" ዶክተር ቢነገር ምንድን ነው ጥቅሙ ለመመሰግን ልጄን እኮ እሱ ነው
ያሳከመልኝ እንድባል የዋህ ምስኪን እንድባል ወይም እናትየው እራሷን እንደ ባለ
እዳ እንድታይ.... ይህን ሁሉ እኔ አልፈልግም ዶክተር በአንድ ወቅት እኔም የልጅ
አባት ነበርኩ የልጅ ህመም እና ስሜቱን አውቀዋለው አቅም ሳይኖር አይደለም
አቅም ኖሮም ቀኑን መዋሉን ለሊቱን ማደሩ እጅግ ከባድ ነው ለማንኛውም
ዶክተር አይነገሯት ... አሁን በሰላም እተኛለው " አለና ትንሽ አውርተው ስልኩ
ተዘግቶ ፊቱ በደስታ እየበራ በጀርባው ከተኛበት ወደ ቀኙ ዘወር አለ።
ብዙም አልቆየም በሩ ሲከፈት ሰማ ኬብሮን እንዳልገባ ያውቅ ነበር ከተኛበት
በመነሳት የመኝታ ቤት በር በመክፈት ወደ ሳሎኑ እየተመለከተ ።
" እረ ጥሩ ነው ከለሊቱ 10 ሰአት መግባት ጀመርክ " አለው
" ጎበዝ ነኛ..... ልመደው አስከማብድ ድረስ .... ታውቃለህ ሴት ልጅ እዚህ
ዓለም ላይ እስካለች ድረስ ወይ ታንቄ እሞታለው አሊያም አብዳለው ምን
ከምድር ሳይሆን ከእኔ እና ከአይኔ ቢያርቅልኝ ምን አለበት ፈጣሪ ሰምቶኝ" አለ
በኬብሮን
" ደግሞ ምን አረጉህ " አለ ሚካኤሌ በሳቅ።
" ምን የማያረጉኝ አለ.... የሚገርመኝ ምን እንደሆነ ታውቃለህ ሴቶች ቃሚ
አጫሽ ንፅህናውን የማይጠብቅ አይወዱም ተባልኩ ይህን ሁሉ አደርኩ ግን እነሱ
ከቆዳዬ ጋር ተሰፍተዋል መሰለኝ አለቅ አሉኝ የትም ብሄድ ይከቱሉኛል ስቃዬን
አበሉኝ ውይ " አለ እና ወደ መኝታው በመሄድ በጀርባው ተጋሎ መሬት
የተነጠፈው ፍራሽ ላይ ተጋደመ።
ቀናቶች በረዋል ጨለማ ብርሀንን እንደገና ብርሀን ጨለማን እየተተካኩ
እየተፈራረቁ ይነጉዳሉ ሚጣም ተሽሏት ወደቤት መጥታለች ። ማክዳ ለኬብሮን
ብሩን ልትመልስለት ፈልጋ ነበር እሱ ግን በልመና መልክ እሷም ብሩም አጠገቡ
እንዳይደርሱ ነግሯታል ሄደ ። አሁን ኬብሮን ከሰላም ጋር በቢሮዋ ስለ ሚካኤሌ
መረጃ እየሰጣት ነበር ሰላም በጣም በደስታ ሰማቺው ፊቷ ፈካ በደስታ
በመጨረሻም አመስግና ከመሳቢያ ውስጥ በርከት ያለ ብር አውጥታ በፖስታ
ሰጠቺው ። እሱም በደስታ ተቀብሏት ሊወጣ ሲል ጠራቺውና
" ኬብሮን እናንተ ጋር ውሀ የለችም እንዴ " አለች ሰላም
" ምነው እናንተ ጋር የለችም እንዴ ችግር የለም ላመጣልሽ እችላለው " አላት።
የኬብሮን በቀላሉ እና በፍጥነት ነገር እንደማይገባው በዚህ ያስተውቃል።
" አይ ለእኔ አይደለም ለአንተ ነው ምን አለበት ገላህን ልብስህን ካሊስህን
ብታጥብ ሰው አጠገብ እንዴት ትቀርባለህ " አለቺው ። የኬብሮን ፊት ወዲያው
በንዴትና በድንጋጤ ተለዋውጦ አያትና።
" ሁሌ የምትረሺውን ስሜን ዛሬ በፍጥነት ማስታወስሽ ገርሞኝ ነበር ......የኔ ገላ
ውሀ አለመንካቱ ምን አስጨነቀሽ... ምነው አብረሺኝ ለመተኛት አስበሻል
እንዴ ?" ሲላት ። ሰላም በንዴት ጨሳ በመጠየፍ ተገፍግፋ ከተቀመጠችበት
ተነስታ
" አንተ .... እኔን....." የምትናገረው ጠፋት በጣም ተናዳለች።
" ስለዚህ የኔ ንፁሁ መሆን አያሳስብሽ እሺ ከፈለግሽ መሰለሉንም እተወዋለሁ
እንደውም ደብሮኛል" ብሏት መልስ አልጠበቀም ወጥቶ ሲሄድ እያየቺው
አብራው የተኛች ይመስል ሰውነቷ በመጠየፍ ተንቀጠቀጠ።
" እንዴ እንዴት እንዲህ ሊደፍረኝ ቻለ ...... እገልዋለው ለዚህ ንቀቱ እና ድፍረቱ
አስገድለዋለው " አለች በር በሩን እያዩች።

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
56 viewsZizu, 16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-12 13:26:38 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 11

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
ሰርካለም እንደ ሬሳ ከበሽተኞች አልጋ ተንጋላ ተኝታለች ነርሶችና ዶክተሮች
ከበዋታል የሆነች አነስተኛ ምርመራ ካደረጉላት በኋላ ዶክተሩ ስትነቃ
እንዲጠሩት ለነርሶቹ ተናግሮ ወደ ቢሮ ሄደ።
ብዙም አልቆየም ነርሶቹ ነቅታለች ብለው ሲጠሩት ወደ ሰርካለም በመሄድ
አያትና።
"ወ/ሮ ሰርካለም አሁን እንዴት ነሽ" አላት በተረጋጋና በትህትና
" ምን ሆኜ ነው ዶክተር " ግራ በተጋባ ሁኔታ
"ልጅሽ አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ያስፈልጋታል ብዬሽ ነበር። አሁንም ልቧ
ለሁለት ተከፍሎ ክፍተት አለበት እያደገች ስትሄድ ሊደፍን ቢችልም እንደዛውም
ህይወቷን በአጭሩ ሊቀጫት ይችላል አሁን ኦፕሬሽን ክፍል ገብታለች ግን አንቺ
ፍቃደኛ ሆነሽ ካልፈረምሽ ልትሰራ አትችልም " አላት ዶክተሩ ሰርካለም አንዴ
በግርምት ሲላት በድንጋጤ ስታየው።
" ዶክተር እኔ የልጄን ደህንነት የአንዷ ፍቅሬ ጤንነት ሳያስጨንቀኝ ቀርቶ መሰለህ
...... "ከአይኖቿ እንባ እረገፍ።
" እና መፈረሙ ምን ከበደሽ ? " አላት ሰርካለም ከእንባዋ ጋር አብሮ በአፍንጫዋ
የመጣውን ፈሳሽ ወደ ላይ ጎትታ ወደ ቦታው በመመለስ።
" ፊርማ ብቻ ነው የጠየቁኝ እንዴ? ..... አነሰ ቢባል ... ተረዱኝ በጣም አነሰ
ቢባል አርባ ሺህ (40.000) ብር ያስፈልጋል ብለውኛል .... ቢበዛስ
ስንት?.....እህህ ይሄ ቀላል ብር ነው ታናሽ እህቴ ቢጨንቃት ከጎሮቤት ልጅ
በአሳፋሪ ሁኔታ ለልጄ ስትል ከሰረቀችው ብር ጋር ስምንት ሺህ (8.000) ከጥቂት
መቶዎች ጋር ነው ያለን ዶክተር ለእሷ ስንል ሌላውን እንተወውና እህል መብላት
አቁመናል ውሀ እንኳ ነፃ ስለሆነ እንጂ የምንጠጣው ለእሷ ስንል ዶክተር...."
ብላ ድምፅ በሌለው ለቅሶ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ። ሀኪሞቹ ለደቂቃ በዝምታ
አያት።
" ወሮ ሰርካለም የጨረሽ መሰለኝ የምትነግሪኝን ነግረሺኝ ... ለማንኛውም አሁን
አንቺ የሚያስፈልግሽ ብር ሳይሆን ፊርማ ብቻ ነው ወደ ሀምሳ ሺህ
(50.000)ብር ተከፍሏል ከአርባ ሺህ ብር በላይ ያለው ካነሰ ተብሎ የተቀመጠ
ነው ከዛም በላይ ቢሆን አንቺ ሳትሆኚ የከፈለው ሰው ነው የሚጨምረው " ሲላት
ደነገጠች ግራ ገባት በህልሟ ይሁን በእውኗ ምንም ልታውቅ አልቻለችም
ከአልጋዋ ብድግ አለች
" አልገባኝም ዶክተር በህልሜ አይደለም አይደል...... ማን ነው የከፈለው "
ትደሰት ትዘን አሌገባትም።
" ማንነቱ እንዲታወቅ አልፈለገም ግን ተከፍሏል ነይ ቶሎ አሁን ፈርሚልን " አላት
ነገሩ ልክ ነው ማንም ይክፈለው ማንም ዋናው ልጇ ደህና መሆኗ ነው ይህን
አሰበችና ሄዳ ፈረመች ግን ጭንቅላቷ የከፈለውን ሰው የማወቅ ፍላጎቷ ጨመረ
በሀሳብ የብዙ ሰዎችን በር አንኳኳች።
" .... ይሄ ሚካኤሌ የሚሉት ይህን ያህል ብር ሊያወጣ ቀርቶ እንደ 19 70ዎቹ
አይነት መኪና ልብሱም አካሉም ጥገና በዝቶበታል እሱ አይታሰብም አባቷም
እንደ ከተማ አውቶብስ ፌርማታ በዝቶበት አንዱ ላይ የጫናትን ሴት በቀጣይ
ያወርዳታል እናም አንድ ጭኖ ሁለት አሊያም ሶስት አርጎ ስለሚያወርዳቸው
ቁጥሩ በዝቶበት የማመን ችግር አለባት ሌላዋ የእኔ አክስት ነች እሷም እንቢ
አላረዥም ብላ ከዕድሜዋ ጋር ግብግብ የያዘች ስለሆነ ለእሷም አይበቃትም በቃ
አከተመ ዶክተር እራሱ ነው ።" አለችና ፈገግ አለች።
".... አንተ ልጅ እረ በመድሀኒያለም አውራ? " አለች ማክዳ በለሊት ጭር ባለው
አስፓልት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ
" እኔን ነው ምን ብዬ ላውራ ?" አለ በመተባተብ በኬብሮን
" እኔ የምታወራውን ልንገርህ እንዴ ?"አለችና ሳቀችበት። አየሩ በጣም ቀዝቃዛ
ስለነበር ኬብሮን ሳይነስ ስላለበት እንደውሀ የቀጠነ ንፍጥ በአፍጫው
በተደጋጋሚ እየመጣበት ይናፈጥ ነበር። ሁኔታውን ማክዳ ስታየው ቆይታ።
" ኬቡ በቃ አታውጣው አብሮ እንዳይወጣ " አለቺው ኬቡ ሴት ከፈጠነችበት
ያፍራል ቁጠኛ ከሆነች ደግሞ ፈሪ ነው።
" ምኑ ነው አብሮ የሚወጣው ?" አላት ግራ ተጋብቶ
" ጠዋት እኮ እያየሁ ነበር ስሜትህ አፍንጫህ ጫፍ ላይ ነው ያለው ... ያኔ
መቼም አልጋ ላይ በሀሳብ ይዘሀኝ ወጥተህ መቼም ...... ዋው ....
አይደል ?....አየህ እሱ ስሜትህ ስለተመቸኝ እንዳታወጣብኝ ብዬ ነው " አለች
በፈገግታ እየቀለደች። ኬብሮን በድንጋጤ አያትና።
" እመብርሀንን ምንም አላረኩም አልወጣሁም የትም .."አላት እሷ ያለቺው ሁሉ
የገባው አለመሰላትም ጭንቃትም ደንጋጣ ፈሪ እንደሆነ ተገንዝባለች በፈገግታ
አየቺውና ሆስፒታሉ በር ላይ ስለደረሱ እጁን ይዛው እየገባች ።
" ኬብሮን ብርህን ከኪስህ እኔ ነኝ የወሰድኩት ግን ከአንተ የበለጠ ብሩ ለሚጣ
ያስፈልጋት ስለነበር ነው አይ ለእኔ ያስፈልጋል ካልክ እመልስልሀለው " አለችው
መልስ ሳይሰጣት ገቡ ወደ ውስጥ።
በኮሪደሩ አልፈው ወደ ውስጥ ሲገቡ ከሰርካለም ጋር ፊት ለፊት ተገናኙ ።
ኪሩቤልን ስታየው በጣም ተናዳ ።
" እ አንተ ግንብ ሁለታቹሁም ቅል ጭንቅላት ነው እንዴ ያላቹሁ ትልቁ ሲሄድ
አንተ የተተካሀው ።"
" እኔን ነው?" አለ ደንግጦ
" እና እኔን ነው ከእህቴ ጋር ምን ፈልገህ ነው ? ውጣ ውጣልኝ ወደ ቤትህ
ሂድ.... ውይ መልከስከስ ይወዳሉ " ስትለው ።ኩምሽሽ ብሎ አናቱ በመጥረቢያ
እንደተመታ መልስ ሳይሰጥ ፊቱን አዙሮ እግሩ በድንጋጤና ፍርሀት እየተርበተበተ
ሄደ።
ከሆስፒታሉ እንደወጣ ጨነቀው ምን አቅብጦት እንደመጣ እያሰበ በእራሱ
ተናደደ አሁን በምን ሊሄድ ነው በእግሩ ድክም ብሎታል በትራንስፖርት አይሄድ
ሳንቲም የለው እየተጨናነቀ ሳለ ስልኩ ጮሀ ። ከኪሱ አውጥቶ ሲያይ መአዛ ነች
ወደ ጆሮው ወስዶ ማናገር ጀመረ።
" አንተ ለምንድን ነው ያልደወልክልኝ " አለችው በንዴት
" መአዚ ይቅርታ እጄ ላይ ሳንቲም ሰለሌለ ነው " አላት መላኳንም እረስቶታል
ነገሩ ምንም የለም።
" የላኩልህን ብር ለሸርሙጦችህ ሰጠህ አንተ ድጋይ እራስ ደደብ መሀይም....."
ቀጠለች ስድቧን ተሳድባ ስትጨርስ።
" ጨረሽ ስድብሽን ደህና እደሪ " አለና ስልኩን ዘግቶት " እባካቹሁ ሴቶች
አልደረስኩባቹሁም ለምን ከእኔ እራስ አትወርዱም ከበዳቹሁኝ እኮ!!!"አለና
አስፓልቱ ላይ ዝርፍጥ ብሎ ተቀመጠ።............

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
55 viewsZizu, 10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-12 13:18:43 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 10

ከዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
" እኔ የምልህ አሁንም እኮ ልብህ እንደ ኳስ እየነጠረች ነው ያለችው
አለቀቀህም እንዴ ?" አለችው ማክዳ ።አይኑ ፈጦ በዝምታ እያያት ያለውን
ኬብሮንን እየተመለከተቺው ከዛም ጠረጴዛው ላይካለው ማኪያቶ ጎንጨት
አረገች። እሱ ደግሞ ውሀ የፈሰሰበት ይመስል ላብ በላብ የሆነውን ሰውነቱን
ባደረገው ቲሸርት ደጋግሞ ይጠርገዋል ግን ሰውነቱ ወዲያው እንደ ምንጭ
ያፈልቃል ። በሀሳቡ ቤት ውስጥ እንዴት ትሆን እንደነበር አሰበ።
ማክዳ የፓንት ያህል ያነሰ የተቆረጠ ጅንስ ቁምጣ አድርጋ አጎንብሳ ቤት
ስትወለውል ጭኗን ዳሌዋን በዘፈኑ ታወዛውዝ ነበር ። ያረገቺው እጅግ ስስ
ቲሸርት ( ቦዲ ) የምንለውን ልብስ ከላይ ስላረገች በብብቷ መሀል አጮልቆ ካለ
ጡት ማስያዣ ደረቷ ላይ የተጠለጠለውን ጉች ጉች ብለው ሾጠጥ ያሉ ትንንሽ
የሚያምሩ ጦቶቿን በጎን እየተመለከተ ነበር ።መመልከቱ አደንዝዞታል እንደ
በረዶ አቀዝቅዞት እና አድርቆት በላብ አጥምቆት በቆመበት አሰቀርቶታል።
ማክዳ እያያት እንደሆነ ገብቷታል በደንብ እንዲያያት ስለፈለገች " ..... እኔ ነኝ
ያለ... እኔ ነኝ ... ያለ" እያለች ዘፈኑን አብራ ትዘፍናለች ። የሚገርመው ለምን
እንዲህ እንደምትሆንለት ነው አፍቃራው ይሆን ሳታፈቅረው አልገባትም ግን
እሱን ለማየትና እሱን ስታይ ያላትን ነገር ለማሳየት እንደምትሞክር አይገባትም ።
ብቻ ዘፈኑ ሲያልቅ አጎንብሳ ከምትወለውለበት ብድግ አለችና በእጇ ግንባሯ ላይ
በላብ የተነሳ የተለጠፈውን ፀጉሯን ለማንሳት አስመስላ ፊቷን አጠር ያለውን
ቲሸርት እጇን ስታነሳ ከፍ ብሎ ስታሳየው እንብርቷን የጓጎለ ሽሮ ምራቁ ሆኖበት
ጉሮሮውን አስጨንቆት ሲውጠው ድምፅ ያሰማ ነበር ።
" እንዴ መጥተህ እያየሀኝ ነው እንዴ ?" አለችው ማክዳ አሁን ያየቺው
በመምሰል እሱ ግን መልስ አልሰጣትም። ከዛም ወደ እሱ እየሄደች ሰላም
አለቺውና ከንፈሩን ሳም ስታደርገው ምንም ሳይናገር በቀጥታ ወደ ቤቱ ሄዶ
በመግባት በሩን ሊዘጋው ሲል ጠራቺውና ሲያያት
" ኬቡ እስቲ ማኪያቶ ጋብዘኝ በጣም አምሮኛል "አለቺው መልስ ሳይሰጣት በሩን
ዘጋው።
" ምንድን ነው የሚያልብህ ..... እህ አናግረኝ እንጂ ኬቡ" አለችው ማክዳ ።
ኬብሮን እንደ መባነን ብሎ ከሄደበት ሀሳብ ተመለሰ። ለእሷ መልስ ሳይሰጥ
ስልኩ ጥሪ አሰማ
እጅግ ያማረውና የተዋበው የሚካኤሌ ላብ ፣ ጉልበት ፣ ገንዘብ የፈሰሰበት ባለ
ሁለት ፎቅ ቤት ዛሬ የሰላምና የፍቅረኛዋ የአድማሱ ቤት ሆኗል ። አድማሱ
በሌሊት ልብስ አልጋው ላይ በጀርባው ተጋድሞ ሰላምን እየጠበቃት ነበር ብዙም
ሳታስጠብቀው እሷ ገላዋን ታጥባ እጅግ አምሮባት በሌሊት ልብስ መጣች
እንዳያት የወሲብ ስሜቱ መላ ሰውነቱን ነዝሮት አቆመው። አጠገቡ መጥታ
አጠገቡ እስከምትተኛ አልጠበቃትም ልብሱን አወላለቀና ዘሎ ወጥቶባት የለሊት
ልብሷን ለማውለቅ ጊዜ አልሰጣትም እየቀደደው ከሰውነቷ አላቀቀውና እሱ
ከእሷ ጋር ተሰፋ።
አንድ የግል ሆ/ል ውስጥ ኮሪደሩ ላይ ወንበር ላይ ሚካኤሌ ቁጭ ብሏል ።
እጅግ የፈጠነ የሴት ኮቴ ሰማ ።
" ይሄን የስድብ ሚሳኤል በምን ልቋቋመው " አለ ሚካኤሌ
" ስማ አንተ ደደብ ነህ እንዴ ?ከልጄ አጠገብ አትደረስ ብዬህ አይደል እንዴ .....
አሁን ሂድልኝ " አለች ሰርካለም በንዴት።
" እሺ እሄዳለው ... ግን አንዴ ውጤቷን ልስማ " አላት ከትንሽ ደቂቃ ዝምታና
ፈገገታ በኋላ።
" ምን አግብቶህ ነው ውጤቷን የምትሰማው ሂድልኝ " አለች በቁጣ ።
ሚካኤሌም ወይ ደውላ ካልነገረቺው እንደማሄድ ቁርጥ ባለ ንግግር ሲነግራት
ተስማማችና የእሱን መሄድ አይታ ወደ ዶክተር ቢሮ ሄዳ ሰላምታ ካቀረበች በኋላ
ስለ ልጇ ጠየቀች የልቧ ጤንነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ኦፕሬሽን ክፍል
መግባቷን ነገራት ሰርካለም ደነገጠች ።
" ዶክተር ብሩን ከየት ላመጣ ነው " አለችና እራሷን ስታ ወደቀች ። ............

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
45 viewsZizu, 10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-11 15:52:10 ​​ ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 9

ደራሲ ዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
" ማን ነች ?" አለው ሳቁን መቆጣጠር እያቃተው ሚካኤሌ።
" እቺ አጁዛ ነቻ .........በእናትህ አንተ ደግሞ አትሳቅ ....... ተቃጥያለው ለእራሴ
አንተ ደግሞ ጭራሽ እየሳክ ታነደኛለህ"
" ትንሽ ብር ነው? "
"ታሾፋለህ መአዛ የላከቺው እንዳለ 6 ሺህ ከጥቂት መቶዎች ይሄ ብር አንድ
የመንግስት ሰራተኛ ወር ቢለፋ ይሄን ያህል ብር አይከፈለውም በሴኮንድ የኪስ
ውስጥ ይሄን ሁሉ ብር የሚገርመው ደግሞ እሷ ብሩን ወስዳ ስድብ ለእኔ
መመረቋ እቺ ....ስድብ ጠፋብኝ ምን ብዬ ልሳደብ አንቄ እቀበላታለው"
ምሽቱን ሚካኤሌ ከመሸ ሰው ቤት አይኬድም ብሎት ቁጭ ጫቱን እየቃመ ሲጋራ
ያለወትሮው ቶሎ ቶሎ እያጨሰ ፅሁፍም ምንም ሳይፅፍ ቁጭ እንዳለ ጨለማው
ተገፎ ፀሀይ ተተካች። ሚካኤሌ ጠዋት ሲወጣ የተኛ በመምሰል ዝም አለና እሱ
ከወጣ ከትንሽ ደቂቃ በኋላ የለሊት ልብሱን ቀይሮ ፊቱን እንደተኛ ሰው ተጣጥቦ
" እገላታለው.... ዛሬማ አለቃትም እገላታለው ...!! " አለና የቤቱን በር ለመክፈት
ወደ በሩ ሲሄድ የልቡ ምት ጨመረ ፈራ ሰውነቱ ተቀጠቀጠ።
" እንዴ ጀግንነቴ እስከራሴው በር ነው እንዴ? ..... ይህማ አይሆንም " አለና
በድፍረት የቤቱን በር ከፈተው።
" ..... እኔ ነኝ ያለ ይሞክረኛ ...... "የሚለው ዘፈን ድምፁ ከፍ ተደርጎ ተከፍቷል።
ከዕነ ማክዳ ቤት ነበር የተከፈተው ዘፈኑ። በሩም ወገግ ብሎ ተከፍቷል። በሀይል
ተነፈሰ ፊቱን በሁለቱ የእጆቹ መዳፍ አሸት አረገና በእርጋታ ወደ በሩ ሄደ ደርሶ
ቆመና ወደ ውስጥ ተመለከተ ባየው ነገር ደነገጠ አይኑ ፈዘዘ አፍን ከፈተ እጅግ
በፍጥነት የልቡ ምት ጨመረ ልብሱን ቀዳ ልትወጣ ደረሰች።
" እእእ... እኔ ነኝ ያለ ይሞክረኛ ቆይ ከየትኛው አቅጣጫ ነው የምንሞክርሽ አሁን
በማየው ወይስ በሌላ" አለ ለመናገር የደረቀውን አፍንና ለቃ የግድ ከፍቶ ከንፈሩ
ደረቀ በምላሱ ሊያረጥበው ሞከረ ነገር ግን ምላሱም ደርቋል ሰውነቱንም ማዘዝ
አልቻለም በቆመበት ሀውልት ሆኖ ቀረ።
ከሰዓታት በኋላ ለሰውነት ምግብ ከሆነችው የጠዋት ፀሀይ ክርር ብላ አናት ወደ
ምትበሳው የከሰአቷ ፀሀይ ተለውጣለች። ሚካኤሌ ሁሌም የሚመጣበትን
ትንሿን ታክሲ ይዞ በመምጣት ለሹፌሩ ሂሳብ ከፍሎት በአንድ እጁ ምግብ የያዘ
ፌስታል በሌላኛው ዱላውን በመያዝ በእርጋታ ደረጃውን በመውጣት ኮሪደሩን
ይዞ ወደ ቤቱ ሲሄድ.....
" ጋ...ጋሼ ሚ......ኪ " አለች ሚጣ በተከፈተው የዕነ ማክዳ ቤት በር ላይ ተዘርራ
ወድቃለች ከጭንቅላቷ ደም መሬቱ ላይ ፈሷል ።
" ልሞት....ነው ......ሀኪም ..... ቤት .... ወሰ....?" አልቻለችም ድምጿ በግድ
በተቆራረጠ አማርኛ ካወራች በኋላ ሳትጨርሰው አይኗን አይኗን ከደነች አፏም
ተዘጋ። ሚካኤሌ ምግቡን እና ዱላውን ጥሎ በወደቀችበት ሄዶ ሲያቅፋት ደሙን
ነካው ቤት ውስጥ ሰው የለም እየጮሀ ምን ሆና እንደሆነ እየጠየቃት መልስ
ስላጣ እየጮሀ አለቀሰ።.......

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
50 viewsZizu, 12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-10 19:45:14 ብቸኝነቴን መልሺልኝ

ክፍል 8

ዳኒ የወሰን ልጅ
.
.
.
ፍዝዝ የሚል የአድናቆት እይታ..... ከደመና መሀል እንደወጣች ፀሀይ ከንፈሮቹን
ሲገልፃቸው የሚያንፀባርቀው ጥርሶቹ ልክ እንደ ፀሀይ ነበሩ ከአይኗ ብሌን ላይ
የሰዓሊ ብሩሽ ሳያስፈልጋቸው በጥበብ በቀለማት ውበት በብርሀን የደመቁ
ምስሎችን እያተመባት ነበር ለሁለቱም ያልታወቀ ህትመት።
" አንተ ሰውዬ ምንድን ነው ከእኔ የምትፈልገው " አለች በንዴት ጭስስ ብላ
ሰርካለም ።
" አየሽ ፈጣሪ እራሱ ልጆችን አትከልክሏቸው ይላል እኔ እጅግ ልጅ እወዳለው
እባክሽ አትከልክያት " አላት በትህትና።
" መቼም አይሆንም ሊሆንም አይችልም ..... የዘድሮ ህዝብ ኢትዮጵያዊያንን
ለማለት ነው መተማመን ጠፍቷል እሺ በፊት እናታችን ጠላ ስትሸጥ ጠዋት
ደንበኞቿ ሲመጡ ቁርስ ምግብ ሰጥታ ባዶ ሆዳቸውን እንዳይጠጡ ጠላውን
ትሰጣቸዋለች ዘድሮ በገንዘቡ ለሚገዛው እንጀራ ጄሶ ጨምረው ይሸጣሉ። ያኔ
ሰካራሞቹ የሚያስቡት እኛን ለማስደሰት ከረሜላ ይገዙልንና ስመውን ቤት
ያደርሱናል ዘድሮ ባዳውን ተወው የራስ አባት በጨቅላ ልጁ ላይ በሴጣናዊ
ስሜቱ ጨፍሮ ይገላታል እንኳን ባዳ አባቷን አምኜ አልሄድም ........ "አለችው
እያቧረቀች
" እህህህ ... ልክ ነሽ ..... ይቅርታ ... " አለ ሚካኤሌ ሌላ ነገር አልተናገረም
ፊቱን አዙሮ ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ ሳለ።
" ስማ ... አንተ ... ሰውየው " አለችው ሰርካለም አንገቷን ሰገግ አርጋ
በማውጣት ። ሚካኤሌ ዘወር በማለት ፈገግታውን አሳያት እና።
" ስሜ እኮ የሚያምርና የፈጣሪ መልክተኛ ስም ነው ብትጠሪውም አያሳፍርሽም
ጥሪው እሺ"
" ባክህ ጠራሁሁ አልጠራሁሁ ክፍያ አላገኝበት .... የምነግርህ ከዚህ ምክንያት
እየፈለክ እኔን ለማየት የምትመጣውን ነገር ተወው እሺ " አለችው ። ሚካኤሌ
ከሰማት በኋላ ከት ብሎ ሳቀባትና።
" ፈልጌ ልይሽ ብል እንኳን ላይሽ አልችልም ...... ግን አንቺን በሆነ ነገር ታዘብኩሽ
...... ለምን በግልፅ አትናገሪም ዝም ብለሽ ቱግ ቱግ ትያለሽ አፍቅረሺኛል ዝም
ብለሽ አፍቅረሀለው አትይኝም " አላትና የቤቱን በር አልፎ ገብቶ ከውስጥ
ሲዘጋው ሰላም በንዴት እየተከተለቺው።
" ምን አልክ አንተ ህልመኛ ...... እኔ አንተን ላፈቅር እረ ጉድ መስሎህ ነው ....
የሆንክ ወጠጤ ቦዘኔ ....ድፍረትህ ሆሆሆሆ..."እያለች በሩን በእጇ ደብድባ
ሄደች።
ያማረ ነገር መልበስ አይወድም ፀጉሩን ፂሙን አይስተካከልም ግን ኪሱ በብር
ከተሞላ እንደሱ ሀብታም ደስተኛ የለም ።ብሩ ቢበዛ ባይበዛ ግድ የለውም
የዕለት ወጪውን ለምግቡ እና ለጫቱ ካገኘ አከተመ ነገን ፈጣሪ በዕራሱ
መንገድ ያዘጋጀዋል ብሎ ነው የሚያስበው። አሁን ለጥቂት ጊዜያት ስለነዚህ
ወጪዎች አያስብም በመአዛና በሰላም ምክንያት ግን የሚገርመው ሁለቱም
ለእሱ አስበው ሳይሆን ለእራሳቸው ብለው ነው ቢሆንም ይሁን።
በእጁ በፌስታል ጫቱን ለስላሳውን ሲጋራውንና ምግቡንቡን በመያዝ ሳሳ ያለ
ቲሸርትና ቱታ ሱሪ አርጓል መዓዛ የላከቺውን ብር ቱታ ኪስ ውስጥ አድርጎ ፊት
ለፊት ብሩ ይታያል ። ከኋላው ማክዳ እየተከተለቺው ስታየው ነበርና አጠገቡ
ደርሳ ሰላም አለቺው እሱም ጥብርር ብሎ ሰላም አላት ገርሟት በንቀት ከላይ
እስከ ታች ስታየው ከቱታው ኪሱ ውስጥ የታጨቀውን ብር አየቺው ደነገጠች እና
ትንሽ አሰብ አደረገችና አቅፈህ ሰላም ልትለኝ ይገባል አቅፈሀኝ ብላ ጭቅጭቅ
አለችበት በመጨረሻ በንዴት ፈቀደላት ዘላ ተጠመጠመችበት እና እየሳመቺው
ለደቂቃ ከቆየች በኋላ ለቀቀቺው ። የቤቷ በር ላይ ደርሳ በሩን ከፈተችና ዘወር
ብላ እያየቺው ።
" አንተ ግን አትኩራ እሺ ኩራት አያምርብህም.....የሆንክ .... ባልጩት እራስ
አናታም " አለችውና በሩን ይዛ ወደ ውስጥ ገባ አለች ። ኪሩቤል በግርምት
ኮስተር ብሎ
" እኔን ነው?"አላት ወደ እሷ ዘወር ብሎ እያያት።
" አዎ አንተን ነው ..... አንሶህ ከሆነ ግድ የለም እያየሁ እጨምርልሀለው "
ስትለው በንዴት ወደ እሷ ሲሄድ በፍጥነት በሩን ዘጋቺው።
ኬብሮን ሚካኤሌን ሰላም ብሎት ፍራሹ ላይ ተቀምጦ ስለ ማክዳ ትንሽ አወሩና
መአዛ ብር እንዳለከቺለት ነግሮት ብሩን ሊያሳየው ኪሱ ሲገባ አጣው በሁሉም
ኪሱ ፈለገው የለም አበደ እንደ መጮህ አለ ግራ ገባው የት እንደጣለው አሰበና

" አዎ እሷ ናት ...... እገላታለው ...እገላታለው " ሲል ሚካኤሌ እያየው
ሳቀ።.............

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
50 viewsZizu, 16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ