2022-03-07 20:10:33
ብቸኝነቴን ...... መልሺልኝ
ክፍል ሀያ ሁለት (22)
.
.
.
ከጥቂት ዓመታት በፊት የሚካኤሌ ሀሳብ
ምን መወሰን ምን ማረግ እንዳለበት ግራ ተጋብቶ በዱላው እየተመራ ወደ ሳሎን
ሄደ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ምን ማረግ እንዳለበት እንቅልፍን ሳይተኛ ሲያስብ አደረ
። አማራጩ በዚሁ አይነ ስውር መስሎ መቀጠል እንዳለበት ህሊናውን አሳመነ።
የሚካኤሌ አይን እንደፈጠጠ ሰማይም ቦገግ ብላ ፈካች በዚህ ሰዓት የሰመመን
እንቅልፍ ወስዶት ነበር ። ውስጥ ሲጎዳጎዱ ብንን አለ ግን አልተነሳም እዛው
አይኑን ጨፈነ ። እነሱ ወደ ስራ ለመሄድ ዝግጅታቸውን ጨረሰው ወደ ሳሎን
መጡና እያዩት ተጠቃቀሱና ።
" ጨርሰናል አልጋውን ከፈለከው ጠረኔ አለልህ አንሶላውን ያረጠብንበት እሱን
በአፍጫክ እየማክ ተኛ።" አለችውና ሳቀች ዝም ብሎ ሰማት አይኑን በአንድ ቦታ
ተክሎ ከሰማት በኋላ።
" አይበቃኝም ሰላም ቤቴን ድርጅቴን ሀብት ንብረቴን ለቀሺልኝ ትሄጂ መካፈል
ያለብሽን ወጭ ሆነሽ ተከራከሪ " አላት ሰላምና አድማሱ እየተያዩ ከት ብለው
ሳቁበትና ።
" የምን ሀብት ንብረት ሁሉም በሚሊየን የሚቆጠር ብር ተበድረሀኝ መክፈል
ስላልቻልክ ሀብት ንብረቴን ለእኔ እንደሰጠህ የሚያረጋግጥ አሻራህም
ፊርማህም ያለበት ማስረጃ እጄ ላይ ነው ከዕነ ምስክሮቹ " አለችው ሚካኤሌ
አልደነገጠም ያኔ ዓይነ ስውር እያለ እንደሚስት አምኗት ፈረመላት ከፈረመ በኋላ
በጣም ትልቅ ስህተት እንደሰራ ገብቶታል የሆነ አንድ ነገር ጎትቶ እንደሚመጣ
ታውቆት ነበር ይሀው ሆነ ዝምታን መረጠ ። ሰላም ንግግሯን በመቀጠል "...ያው
እኔ ክፍ ስላልሆንኩ ቤት ተከራይቼልሀለው ከዛሬ ጀምሮ እዚህ ቤት እንዳላገኝህ
ንብረቴን ቀማቺኝ የምትል ከሆነ ፍ/ቤት ክሰሰኝ ከዚህ በኋላ እዚህ ቤት
ድርጅትም ዝር እንዳትል እኔ ባለትዳር ነኝ እሺ " አለችው
" እሺ ..... ግን ማን ነው የሚወስደኝ ወደ ተከራየሺው ቤት " አላት ፍፁም
ትህትና በተላበሰበትና በፈገግታ ።
" ሹፌር እልክልሀለው እሱ ይዞህ ይሄዳል እስከምችለው የቤት ክራይህንና
ምግብህን እችልሀለው ለፈጣሪ ስል ልጁ እስከሚመጣ እቃህን አዘጋጅ ይህን
ስል ልብሶችህንና የምታነባቸውን መፅሀፎች ብቻ ነው ይዘህ የምትወጣው "
ብላው ፈገግ እያለ ዱላውን አንስቶ እየተመራ እየሄደ
" ሄጄ ላዘጋጃ አይመስላቹሁም " አላት በመሳቁ መልስ ሳትሰጠው እየሄደች
ለአድማሱ የምትናደድበት ሰው መናደድ ሲኖርበት የእሱ መሳቅ ነው እናም
እያላገጠባት ይመስላል።
ከለሳብ መልስ አሁን ላይ
የሚጣ ፊት ሀይለኛ ዝናብ የዘነበበት መሬት መስሏል አይኖቿ በለቅሶ
ሞጭሙጨዋል የሰካራም አይን ይመስል ደፍርሷል ። ሚካኤሌ በሀሳብ
ከሄደበት ሲመለስ የእሱም ዓይን እንባ አዝሎ ነበር ጭምቅ አርጎት እንባዎቹን
ከመሬት ፈጠፈጣቸው።
" ጋሼ እሷን ስናስባት ሴጣን የዋህ ነው እንበል " አለቺው እና እሱ ፈገግ ብሎ
ዝም ሲላት ።" .... ጋሼ እረ ቆይ ለምንድን ነው እንዲህ ክፍ የሆነቺው? " አለቺው
" ሚጣዬ እሱን እንኳን እኔ እሷስ ታውቀዋለች " አላት በዚሀ ሰዓት ሰርካለም
የተኛችበት መኝታ ክፍል ተከፍቶ ዶክተሩ በመውጣት ወደ እነሱ በመምጣት።
" የተደረገላት ኦፕሬሽን በተሳካ ሁኔታ ተፈፅሟል አሁን ልታያት ትችላላቹ
በቅድሚያ ግን እንኳን ደስ አላቹሁ አለና ጨበጣቸው ሁለቱም በደስታ እየሮጡ
መኝታ ክፍሉን ከፍተው ሲገቡ ሰርካለም ሚካኤሌን እንዳየቺው በጩሀት
እንዲወጣላት አባረቀችበት ሚጣም እሱም ደንግጠው በቆሙበት ደርቀው ቀሩ።
ኬብሮን ሚስት ሳይሆን ያገባው ፌዴራል እስር ቤት ነው ያለው ብላ በዱላ ጫት
ቃም በዱላ ተኛና ወሲብ አርገኝ በዱላ ሆኖበት ምርር ብሎታል ፊቱ ቆስሏል ።
አሁንም ቁጭ ብሎ እየቃመ እሷ ቡና እያፈላች ነበር ። እናም መፀዳጃ ቤት ደርሼ
ልምጣ በማለት አስፈቅዶ ወደ መፀዳጃ ቤት አስፈቅዶ በመሄድ ሽንቱን እየሸና
ሳለ ሞባይሉ ጮሀ ከኪሱ አውጡቶ ደዋያን ሲመለከት ሰላም ነበረች ማናገር
ጀመረች።
" አንተ ምን አባህ ልሁን ብለህ ነው ብሬን በልተህ የጠፋሀው" አለችው ሰላም
" እረ በመድሀኒያለም ፣ በማርያም ፣በሚካኤል ፣ በገብርኤል እባካቹሁ ሴቶች
ተውኝ በቃ ..... ቆይ ማን ነው በእኔ ላይ ያዘመታቹሁ እኔ የኢትዮጵያ ጠቅላይ
ሚኒስትር አልነበርኩ ማን አቃጥላቹሁ ድፍት ብሏቹሁ ነው?" አለ በምሬት
" አንተ ደግሞ ሰው ሆነህ አንተን ለመግደል ሰው ይላካል ውርጋጥ አሁን ስለ
ሚኪ ንገረኝ አለበለዚያ አስደፋሀለው " አለች ሰላም በዚህ ወቅት መዓዛ መቆየቱ
አናዷት ስትመጣ ከሴት ጋር እያወራ ነው በንዴት አየቺው ።
" ምንም የለኝም ....እሱማ ግልግል ነው ላኪብኝና አድርጊው በጣም ይሻለኛል"
እያለ ዘወር ሲል አያት በድንጋጤ አይኑ ፈጠጠ እሷም ያን ቡጢዋን አቅምሳው
ከሽንት ቤቱ ሲንክ ላይ አጋደመቺውና።
" እኔን ተደብቀህ ትጀናጀናለህ አንተ አህያ እገልሀለው እሷንም እገላታለው"
አለቺው እና በወደቀበት ምራቋን ተፋቺበት።
ኬብሮን ጠዋት የተነሳው የቤቱ በር በለይል ሲንኳኳ ነበር ።ተነስቶ ቤቱን ተዟዙሮ
ሲያይ የለችም መዓዛ ፊቱ ላይ ብልዝና ፕላስተር ሞልቷል በሀይል ወደ ሚንኳኳው
በር ሄዶ ሲከፍት የታጠቁ ፖሊሶች እና ሲቢል የለበሰ በዕድሜው ፀና ያለ
አስቀያሚ ሰውዬ ቆሟል ስሙን ጠርተውት እሱ መሆኑን አረጋገጡ መዓዛ
እንዳለች ጠየኩት አለመኖሯን ተናገረ ሲቢል የለበሰው ሰው በጥላቻ እና በንዴት
እያየው።
" ነፍሰ ጡሯን ሚስቴን በፍቅር አጃጅለህ ብሬን እየዘረፈች እንድትሰጥህ ከደረክ
አስኮብልለህ አብረሀት ትኖራለህ ያዙልኝ ይሄን ወንጀለኛ " አለ ሰውዬው
ፖሊሶቹም ልብስ እስኪለብስ አልጠበቁትም እያዳፍት ወሰዱት።.........
╔═══❖• •❖═══╗
@yegna_yegna
╚═══❖• •❖═══╝
❥❥ ⚘ ❥❥
68 viewsÀbiti, 17:10