◈ ━━━⸙ ፍቅሬን በግጥM ⸙━━━━◈ አረ እግዜር በናትህ ፥ በጭንቅ አማላጇ ባጠቡህ ጡጦቿ ፥ ባጎረሰህ እጇ ወይ ህፃን ሆነህ ና ፥ ወይ ሙሴን ስደደው የማንም ወጠጤ፤ የቃል ኪዳን ምድሯን ፥ ክብሯን አወረደው ዳዊትን ላክልን ፥ ወይ ደግሞ ወንጭፉን ጎልያዶች በዝተው፤ የሚመካከሩት ፥ መች እንደሚያጠፉን እባክህ እግዜር ና፤ ወይ ሎጥን ፍጠረው ፥ ከመካከላችን ዝም ያልህ እንደሆን፤ ነበር መሆኑ ነው ፥ ምድር ላይ ስማችን። እኔን ባይ 138 views17:34