Get Mystery Box with random crypto!

👆🏻የዲኔ ጉዳይ ያገባኛል👆🏾

የቴሌግራም ቻናል አርማ yedine_guday — 👆🏻የዲኔ ጉዳይ ያገባኛል👆🏾
የቴሌግራም ቻናል አርማ yedine_guday — 👆🏻የዲኔ ጉዳይ ያገባኛል👆🏾
የሰርጥ አድራሻ: @yedine_guday
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.27K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
♦️#ተውሒድና_ሱና በሰለፎች አረዳድ ብቻ ከተለያዩ የሰለፊያ መሻይኾችና ኡስታዞች ትምህርት ይቀርባል።
♦ እንዲሁም ሙስሊሙን የተመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን እናጋራለን ተቀላቀሉ
ولقد بعثنا في كل أمة رسولاً عن اعبد الله واجتنبوا الطاغوت
https://t.me/yedine_guday
ሀሳብ እስተያየቶን በ👇ያድርሱን
@Yedinegudaybot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 07:18:46 አደራ ሸር በማድረግ አሰራጩት

#በተለይ_በሀገራችን_ወሎ___!!


http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
29 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 07:16:28   ወሳኝ ምክር ለቁርአን ተማሪዎች

ርእስ፦ ሙራጀዓህ ማድርግ ጥቅሙ
እና ከርሱ መዘናጋት ያለው ጉዳት


በአብዱረህማን አቡ ዑሰይሚን

https://t.me/joinchat/AAAAAEo2WD9NnvX8ABbBgw
29 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:37:22 የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ታዲያ ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖትችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ጥፋቶች አሉ። ከነዚህም ውስጥ
1. ቀዳሚው ድግምትና ጥንቆላ ነው፡፡ በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሀሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት እጅግ ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። ጥንቆላና ድግምት:-

* ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል።} [አሶሒሐህ፡ 3387]

* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን እንዲህ ይላል፡- “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም።” [ጦሃ፡ 69]

* ደጋሚዎች የሰዎችን ገንዘብ በማታለል የሚበዘብዙ መዥገሮች ናቸው። ገንዘቡን ለነሱ የሚሰጥ አካልም አላህ ፊት ተጠያቂ ነው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {የኣደም ልጅ በቂያማህ ቀን አምስት ነገሮችን ሳይጠየቅ እግሮቹ አይንቀሳቀሱም። እድሜውን በምን እንዳጠፋው፤ ወጣትነቱን በምን እንደጨረሰው፤ ገንዘቡን ከየት እንዳመጣው፤ እንዲሁም በምን እንዳወጣው፤ ባወቀው ምን እንደሰራ።} [አሶሒሐህ፡ 946]

* ደጋሚዎች የነገር ቋቶች የማህበራዊ ህይወት ጠንቆች ናቸው። የተቸገረ ደንበኛቸው መፍተሄ ፈልጎ ሲመጣባቸው በብዛት የችግሩ መንስኤ የሆነው ወይ ጎረቤቱ፣ ወይ ዘመዱ ወይ ደግሞ የቤተሰቡ አባል እንደሆነ በመጠቆም ሰዎች ውስጣቸው እንዲሻክር አለመተማመን እንዲነግስ ያደርጋሉ። በድግምቶቹ ምክንያት የጤና መጓደል፣ የትዳር መፍረስ፣ የዝምድና መቆራረጥ፣ የጎረቤቶች በጎሪጥ መተያየት አልፎም ደም የሚያቃባ ግጭት እንዲከሰት ሁሉ ሰበብ ሊሆኑ ይችላሉ።

* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም።} [ሙስሊም፡ 5957]

2. ሌላው በ “ዘመን መለወጫ” አካባቢ የሚፈፀመው ጥፋት በአንዳንድ አካባቢ ያለው ጳጉሜን ተከትሎ ለዱዓህ መሰባሰብ ነው። እነዚህ አካላት የጳጉሜ ዱዓህ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) በማለት ነው ወቅቱን በዱዓእ የሚያሳልፏት። በጣም የሚገርመው ለዱዓህ የሚጥጠሩት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ማለታቸው ምንኛ የሚደንቅ ሐቅ ነው?! ዲን ያስተምራሉ ተብለው የሚታሰቡት አካላት ክርስቲያናዊ አቆጣጠርን መሰረት ያደረገ ዒባዳህ እየፈፀሙ ሰዎችን ወደ ጥፋት ሲወስዱ በገሃድ ይታያሉ።

3. ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-

* አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
* እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡ ይህንን ስንል የሚደብራቸው ክርስቲያኖች አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ሰው እንዴት የኔን እምነት ካልተከተላችሁ ብሎ ሌሎችን በአክራሪነት ይፈርጃል?!
የእምነታችንን ጉዳይ ለኛ ብትተውልን። እምነታችን ሌሎች ህዝቦች በሚልለዩባቸው እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
62 views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:01:54 قُلْ إِنَّمَا أَنَا بَشَرٌ مِّثْلُكُمْ يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ فَمَن كَانَ يَرْجُو لِقَاءَ رَبِّهِ فَلْيَعْمَلْ عَمَلًا صَالِحًا وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا

(ሱረቱ አል ከህፍ፥ - 110)
«እኔ አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው ማለት ወደኔ የሚወረድልኝ ቢጤያችሁ ሰው ብቻ ነኝ፡፡ የጌታውንም መገናኘት የሚፈልግ ሰው፤ መልካም ሥራን ይሥራ፡፡ በጌታውም መገዛት አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡
https://t.me/yedine_guday
60 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:24:43
قال الشيخ/ ابن عثيمين رحمه الله:

فأنت إذا تزوجت فتح الله لك باب رزق، يكون رزقا لزوجتك، وليس الزواج سببا للفقر.

فتح ذي الجلال والإكرام ٢٥/١١


‏••══ ༻✿༺══ ••
قناة ( فوائد العلامة ابن عثيمين )
tme/othaymen
ሸይኽ ኢብኑኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ:-
***አንተ ሚስት ካገባህ አላህ ሱብሃነሁወተዓላ የሲሳይን በርን ይከፍትልሃል:: የተሰጠህ ሪዝቅ ለሚስትህም ሲሳይ ይሆናል!!!
ትዳር የድህነት መንስዔ አይደለም!! ::
ምንጭ :- ፈትሁ ዙል ጀላሊ ወልኢክራም 11/20

t.me/Arekityesunnahjemmea
http://t.me/Arekityesunnahjemmea
http://t.me/Arekityesunnahjemmea
71 views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:48:40 الحرب الإثيوبي مع التغراي

"ستنتهي الحرب ويتصافحُ
القادةَ وإلا قبحهم الله ونجى المجتمع من شرورهم ،وتبقى تلك العجوز تنتظر ولدها الشهيد ،وتلك الفتاة تنتظرُ زوجها الحبيب ،وأولئك الأطفال ينتظرونَ والدهم البطل.
‏لا أعلم من باع الوطن ،ولكنّني رأيتُ من دفع الثمن"

الله اكفينا شر الحروب يارب

አላህ ሀገርን ሠላም ያርጋት ሙስሊሞን፡ ሴቶችን፡ ህፃናት አላህ የበለጠ ይጠብቃቸው ልዩ ተጠቂ እነሱ ናቸው ።
190 views14:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:51:00 ሁለት ሰዎች ብቻ በጀማዐ ሲሰግዱ ተከታዩ ከኢማሙ ትንሽ ወደ ኋላ መሆን ልክ ነው?
~
ሁለት ሰዎች ብቻ ጀማዐ ሶላት የሚሰግዱ ከሆነ ተከታዩ ከኢማሙ ትንሽ ወደ ኋላ ሆኖ ሲቆም ማየት የተለመደ ነው። በርግጥ ይህንን የመረጡ ዓሊሞች አሉ። ይሁን እንጂ ትክክለኛው አፈፃፀም ተከታዩ ከኢማሙ ጋር እኩል ሆኖ መቆሙ ነው። ኢማሙል ቡኻሪ ረሒመሁላህ በሶሒሕ ኪታባቸው ውስጥ እንዲህ የሚል ርእስ አስፍረዋል፦
" يَقُومُ عَنْ يَمِينِ الإمَامِ بحذائهِ سواءً، إذا كَاناَ اثْنَيْن".
“ከኢማሙ በቀኙ በኩል እኩል ሆኖ ይቆማል፣ ሁለት ከሆኑ።”
ከዚያም ተከታዩን የኢብኑ ዐባስን ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ አስፍረዋል፦
"بِتُّ فِي بَيْتِ خَالَتِي مَيْمُونَةَ، فَصَلَّى رَسُولُ اللَّهِ ﷺ العِشَاءَ، ثُمَّ جَاءَ فَصَلَّى أَرْبَعَ رَكَعَاتٍ، ثُمَّ نَامَ، ثُمَّ قَامَ، فَجِئْتُ فَقُمْتُ عَنْ يَسَارِهِ، فَجَعَلَنِي عَنْ يَمِينِهِ،... "
“ከየሹማዬ መይሙና ዘንድ አድሬ ነበር። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዒሻእን ሰገዱ። ከዚያም (እቤት) መጡና አራት ረከዐዎችን ሰገዱ። ከዚያም ተኙ። ከዚያም ለሶላት ቆሙ። በግራቸው በኩል ቆምኩኝ። በቀኛቸው አደረጉኝ።...” [ቡኻሪ፡ 697]
“ይሄ የኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ እኩል ሆኖ መቆምን ያስጨብጣል ወይ?” ከተባለ “አዎ” ነው መልሱ። ኢብኑ ሐጀር ረሒመሁላህ “ከቀኝ ጎናቸው አደረጉኝ” የሚለውን የኢብኑ ዐባስን ንግግር ሲያብራሩ “ጉልህ መልእክቱ እኩል ሆኖ መቆም ነው” ብለዋል።
የቡኻሪን ርእስ አስመልክተውም እንዲህ ብለዋል፦
በዚህ ርእስ አሰጣጣቸው የፈለጉት በሶላት ውስጥ ኢማምና ተከታይ ብቻቸውን ከተገኙ ተከታዩ ከኢማሙ በቀኝ ጎን እኩል ሆኖ ማለትም በመቆሚያው ቦታ ላይ መቀደምም ሆነ መዘግየት ሳይኖር እኩል መሆናቸው ነው።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197]
.
በሌላ ዘገባ ላይም ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፦
" أَتَيْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مِنْ آخِرِ اللَّيْلِ، فَصَلَّيْتُ خَلْفَهُ، فَأَخَذَ بِيَدِي، فَجَرَّنِي، فَجَعَلَنِي حِذَاءَهُ، فَلَمَّا أَقْبَلَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَلَى صَلاتِهِ، خَنَسْتُ، فَصَلَّى رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَلَمَّا انْصَرَفَ قَالَ لِي: مَا شَأْنِي أَجْعَلُكَ حِذَائِي فَتَخْنِسُ؟
فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ! أَوَيَنْبَغِي لِأَحَدٍ أَنْ يُصَلِّيَ حِذَاءَكَ، وَأَنْتَ رَسُولُ اللهِ الَّذِي أَعْطَاكَ اللهُ؟
قَالَ: فَأَعْجَبْتُهُ، فَدَعَا اللهَ لِي أَنْ يَزِيدَنِي عِلْمًا وَفَهْمًا... "
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ የሌሊቱ መጨረሻ ላይ መጣሁኝ። ከኋላቸው ልሰግድ ቆምኩኝ። እጄን ይዘው በመጎተት ከሳቸው ጎን ትይዩ አቆሙኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሶላታቸው ላይ ሲያተኩሩ ጊዜ ወደኋላ አልኩኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሰገዱ። ባጠናቀቁ ጊዜ፦ ‘ምነው? እኔ በጎኔ ሳደርግህ ወደኋላ ትላለህሳ?’ አሉኝ።
‘የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በአንተ ትይዩ ሆኖ ለማንስ ሊሰግድ ይገባዋልን? አንተ አላህ ያደለህ የአላህ መልእክተኛ ሆነህ ሳለ?’ አልኳቸው። ገረምኳቸው። እውቀትንና ግንዛቤን እንዲጨምረኝ አላህን ለመኑልኝ።” [አሶሒሐህ፡ 6/174 - 175]
ከጃቢርም ተመሳሳይ መልእክት ተላልፏል። [ሙስሊም፡ 3010]
በተጨማሪም ዐብዱላህ ብኑ ዑትባህ ብኒ መስዑድ እንዲህ ብለዋል፦
دخلت على عمر بن الخطاب رضي الله عنه بالهاجرة «فوجدته يسبح، فقمت وراءه. فقربني حتى جعلني حذاءه عن يمينه»
“ዑመር ብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ ዘንድ ቀትር ላይ ስገባ ሱና እየሰገዱ አገኘኋቸው። ከኋላቸው ቆምኩኝ። በቀኛቸው በኩል አድርገው አቀረቡኝ።” [ሙወጦእ ማሊክ፡ ሐዲሥ ቁ. 364]
.
አልሓፊዝ ኢብኑ ረጀብም ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
" الإمام إذا لم يأتم به غير واحد، فإنه يقيمه عن يمينه بحذائه، ولو كان صبيا لم يبلغ الحلم. وهذا كالإجماع من أهل العلم.
وقد حكاه الترمذي فِي "جامعه" عَن أهل العلم من أصحاب النّبيّ - صلّى الله عليه وسلّم - فمن بعدهم، قالوا: إذا كان الرّجل مع الرّجل يقوم عن يمين الإمام. وحكاه ابن المنذر عَن أكثر أهل العلم... "
“አንድ ኢማም ከአንድ ሰው ውጭ የሚከተለው ከሌለ በቀጥታ ከቀኙ በኩል ሊያቆመው ይገባል። ለአቅመ ሃላፊነት ያልደረሰ ህፃን ቢሆን እንኳ። ይሄ የእውቀት ባለቤቶች ዘንድ ልክ እንደ ኢጅማዕ ነው። ቲርሚዚ በጃሚዐቸው ውስጥ ከነብዩ ﷺ ባልደረቦች እና ከነሱ በኋላ ከመጡ አዋቂዎች ጠቅሰውታል። አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ከሆነ ከኢማሙ ቀኝ ይቆማል ብለዋል። ኢብኑል ሙንዚርም ከብዙ የእውቀት ባለቤቶች ጠቅሰውታል።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197 – 198]
በተጨማሪም ኢብኑ ጁረይጅ ረሒመሁላህ “ 'አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ሆኖ የሚሰግድ ከሆነ ከየት በኩል ነው የሚሆነው?' ብየ ዐጧእን ጠይቄ ነበር” ይላሉ።
ዐጧእ፦ “በቀኙ በኩል” አሉ።
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “አብሮት እስከሚሰለፍ ድረስ በሱው አቅጣጫ ነው የሚሆነው? አንዱ ሌላውን ሳይቀደም?”
ዐጧእ፦ “አዎ!”
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “በመሃላቸው ክፍተት እስከማይኖር ድረስ?
ዐጧእ፦ “አዎ!” [ሙሶነፉ ዐብዲረዛቅ፡ ቁ. 3870]

ስለዚህ ሁለት ሆነው በሚሰግዱ ጊዜ ከኢማም ትንሽ ወደ ኋላ መቅረት ምንም እንኳ የደገፉት ዓሊሞች ቢኖሩም ማስረጃ የሚደግፈው ግን አይደለም። ይህንን ማድረግ የተወደደ ቢሆን ኖሮ ተጨባጭ መረጃ ከነብዩ ﷺ ይተላለፍ ነበር። ነገር ግን የለም። ከሶሐቦችም ይገኝ ነበር። ይህም የለም። መረጃ አለመኖሩ መሰረት እንደሌለው ያሳያል። እንደሚታወቀው ነብዩ ﷺ “ስሰግድ እንዳያችሁኝ ስገዱ” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 631] የሳቸው አሰጋገድ ውስጥ ደግሞ ከአንድ ተከታይ ጋር ብቻ ሆነው በሰገዱበት ላይ ትንሽ የተቀደሙበት አልተገኘም። ይልቁንም የተገኘው ከዚህ በተለየ እኩል ጎን ለጎን መቆም ነው። ይሄኛው አቋም ከዘመናችን ዓሊሞች ውስጥ የኢብኑ ባዝ፣ የአልባኒይ እና የኢብኑ ዑሠይሚን አቋም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
132 views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:40:54 ጥቂት ነጥቦች ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ
~
1. ወገኔ ሆይ! አገርህን አትልቀቅ።

ባለፈው ተፈናቃዮች ላይ የደረሰውን አስታውስ። ደብረ ብርሃንና ባህርዳር ለተፈናቃዮች ከማጎሪያ ካምፕ የማይለዩ እንደነበሩ ሲወራ ነበር። አሁን ደግሞ ነገሮች ከቀድሞው ቢብሱ እንጂ የተሻሉ አይደሉም። ፖለቲከኛውን ተወው። ህዝብ እራሱ ኑሮ ስለከበደው ሊጨካከን፣ ሊሰላች ይችላል። ሩቅ አትሂድ። ደሴ ወልዲያን፣ ወልዲያ ቆቦን ሊሰለች ይችላል። የጎደለበት ደግሞ በትንሽ በትልቁ ይከፋዋል። ስለዚህ በተለየ እፈለጋለሁ ብሎ የሚሰጋ ካልሆነ በስተቀር ጦርነቱ ቀጥታ ከሚካሄድባቸው ቀጠናዎች ለጊዜው ዞር ከማለት ውጭ ካገር ርቆ መሄድ ስቃዩን የከፋ ያደርገዋል።

2. ወገኔ ሆይ! ንብረትህን ጠብቅ።

ሩቅ ብቻ አትመልከት። እዚያው በዙሪያህ ለዘረፋ ተደራጅተው ከግለሰብ ንብረት እስከ ተቋም ሲዘርፉ የነበሩ እንደነበሩ ይታወቃል። ዛሬም ይኖራሉ። ፍሪጅና ቴሌቪዥን ሳይቀር በግመል እየጫኑ የወሰዱ የገጠር ሰዎች እንዳሉ ሰምቻለሁ። “መብራት የላችሁ ምን ያደርግላችኋል?” ሲባሉ “እንሸጠዋለን” ሲሉ ነበር። ስለዚህ ቅድሚያ ለህይወት ጥንቃቄ ካደረግክ በኋላ በቅርብህ ሆነህ በተቻለህ መጠን ንብረትህን ተደራጅተህ ጠብቅ።

3. ወገኔ ሆይ! ለፈተና እራስህን አዘጋጅ!

ወደድንም ጠላንም ፈተና ላይ ነው ያለነው። መጠኑ ከህዝብ ህዝብ በእጅጉ እንደሚለያይ ግልፅ ነው። ፈተናው ምን ያህል እንደሚዘልቅም አናውቅም። የሆነች ያክል የምንዘጋጅባት ሰበብ ካለችን ባለችን መጠን ለሚመጣው ሁሉ ራሳችንን እናዘጋጅ። ምግቡ፣ ወፍጮው፣ ባንኩ፣ መብራቱ፣ ቴሌው፣ መድሃኒቱ፣ ... ብዙ ነገር ይቸግራል። እስካሁንም ብዙ የተፈተነ አለ። ልዩነቱ ብዙ ባይሆን እንኳ የተዘጋጁበትና የተዘናጉበት ፈተና አንድ አይደለም። አላህ ለሁሉም ፈረጃውን ያቅርብልን።

4. ወገኔ ሆይ! ጊዜ አይተህ አትለወጥ!

ለሚያልፍ ቀን ትዝብት ላይ አትውደቅ። የትኛውም ቡድን አጠቃኝ በሚል ማመሃኛ ማንንም ብሄር ለይተህ እንዳታጠቃ። የአማራ ህዝብ ሆይ! ህወሓትን መነሻ አድርገህ ለፍቶ አዳሪ ትግሬን አታጥቃ። “ያው ናቸው” ከሚል ስሜት ወለድ ሂሳብ ራቅ። “ህወኃት እከሌን አካባቢ የተቆጣጠረው ተፈናቃይ ትግሬዎችን ተጠቅሞ ነው” እየተባለ የሚናፈሰው ብታምንም ባታምንም ከንቱ ውሸት ነው። እንዲህ አይነት አሉባልታ ይዘህ ደካሞችን እንዳትጎዳ።
ትግሬው ሆይ! ህወኃት ሲገባ ጠብቀህ አደባባይ ለጭፈራ አትውጣ። ጠቋሚ፣ አፋኝ፣ አሳፋኝ ለመሆን አትሞክር። ሃይማኖት ወይም ሞራል እንኳ ባይገታህ ቢያንስ ለራስህ ፍራ! ነገሮች የተቀያየሩ እለት መግቢያ ታጣለህ። በባለፈው ግጭት አማራውም፣ ትግሬውም፣ ኦሮሞውም፣ አፋሩም ዘንድ ብዙ ደስ የማይሉ ነገሮች ሲወሩ ነበርና አላህን ልንፈራ ይገባል።

5. ወገኔ ሆይ! ለመጣ ለሄደው አታጨብጭብ።

አንድ ኃይል አንድን አካባቢ ሲቆጣጠር ሆ ብሎ መውጣት፤ ሌላው በግሩ ሲተካ አሁንም ሆ ብሎ መነሳት ይሄ ግልብነት ነው። የሃገራችን ፖለቲካ ቂመኛና ተበቃይ ነው። እንኳን የገባበትን፣ የሌለበትንም ጊዜ ተጠግቶ ያጠቃል። ደግሞም በጣም ተገለባባጭ ነው። እዚች አገር ውስጥ ስንት አይሆንም የተባለ ነገር ሆኗል! መንግስት ትግራይን ሲቆጣጠር ህወኃት ዳግም ያንሰራራል ብሎ የገመተ አልነበረም። ህወኃት ሰሜን ሸዋ ከደረሰ በኋላ በዚያ አሰቃቂ ሁኔታ ይመለሳል ብሎ የገመተም አልነበረም። ስለሆነም ጥንቁቅ መሆን ያስፈልጋል። በሁለቱም አይንህ ዛሬ ላይ ብቻ አታፍጥጥ። በአንድ አይንህ ነገን ተመልከት።

6. ወገኔ ሆይ! ህይወት አትርፍ።

አጋጣሚዎችን ተጠቅመው የሚጠሉትን ለማጥቃት የማያመነቱ እርኩስ ፍጡሮች ይኖራሉና ቢቻልህ ያለ ጥፋታቸው የበደለኞች ሰለባ ሊሆኑ የሚችሉ ወገኖችን አትርፍ። ከጎናቸው ቁም። በባለፈው ግጭት ህወኃት ሲገባ ጠብቀው ደካሞችን ያጠቁ ሰዎች አሉ። ከነሱ አንፃር ሲታይ ህወኃት በጣም የተሻለ ነበር። መረጃ ያለው ሰው የምለው ይገባዋል። ህወኃት ከወጣ በኋላም እንዲሁ ከየትኛውም ኃይል ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌላቸው ምስኪኖች ተጎድተዋል። ከተቻለን ጊዜ አይተው ከሚያጠቁ ነውረኞች አንድ ነፍስ እንኳ ብናተርፍ ዋጋው የትና የት ነው!! በቅርቡ ኦሮሚያ ውስጥ በነበረውን ግጭት የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ኦሮሞዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። አማራ ውስጥ የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው ትግሬዎችን ያተረፉ ስንት አማራዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ትግሬዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። ሰው ማለት፣ ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት!

7. ወገኔ ሆይ! ወቅታዊ ግጭቶችንና ተያያዥ ጉዳዮችን ከሃይማኖት ጋር እንዳታጠላልፍ።

የየትኛውም ቡድን ደጋፊ ልትሆን ትችላለህ። የኔ የምትለው ወገን ከሌሎች በተለየ እንደተገፋ ሊሰማህ ይችላል። ግን እወቅ! ሌሎችም መሰል ህመም አላቸው። ቢቻል በፖለቲካውም ሞራል ግብረ ገብነት ቢኖርህ እሰየው። ያለበለዚያ ግን የሃይማኖት ተቋማትም፣ አስተማሪዎች እና የደዕዋ መድረኮችም አንተ በምትፈልገው መልክና መጠን እንዲያወሩ፣ የፖለቲካ ፍጭቶች ማራገፊያ እንዲሆኑ አትፈልግ። ማህበራዊ ሚዲያዎችም ላይ ሆነ መሬት ላይ እየተከተልክ በአክቲቪስት ቋንቋ እንዲያወሩ አጉል አትወትውት። ልትረዳ ቢያቅትህ ቢያንስ አደብ ይኑርህ። ከፖለቲከኛ ጋር የለመድከውን እሰጥ አገባ በየደረስክበት አትድፋ።

8. የሃይማኖት አስተማሪ ሆይ! ከመንጋው ተለይ!

ብሄርህን ተከትለህ ቅስቀሳ ውስጥ አትግባ። ሌላው አካል ለጦር ቢቀሰቅስ አንድ ሁለት ነገር ተመልክቶ ነው። አንተ ተጨማሪ አርቀህ የምትመለከትበት አላህን መፍራቱ ሊኖርህ ይገባል። ያለበለዚያ በምንህ ነው ከሌሎች የምትለየው? ኢን ሻአላህ ነገ ሰላም ይመጣል። እሱን ታሳቢ አድርግ። መንጋው ሊያግባባህ፣ ሊገፋፋህ፣ አልሆን ሲለው ሊያወግዝህ ይችላል። የፈለገውን ይበል እሱ በቀደደው አትፍሰስ። የሃይማኖት አስተማሪ ሆነው በቀጥታ የግጭት ተሳታፊ፣ ወይም ቀስቃሽ፣ ወይም ደጋፊ፣ ወይም የዘር ጥላቻ ጠማቂ የሆኑ መርዘኛ ሰባኪዎች ሁሉም ብሄር ጋር አሉ። እነዚህ አካላት ነገ ችግሩ ቢያልፍ እንኳ የማያልፍ ጠባሳ እየጣሉ ነው። ጦሳቸውም ከራሳቸው አልፎ ለህዝብ ይተርፋል። ከሃይማኖትህ ተማር። እስካሁን ካለፈው ተማር። ከሌሎች ድክመት ተማር። የትኛውንም ውሳኔ ብትመርጥ ከትችት ላታመልጥ ነገር የሰው ስሜት ተከትለህ እንዳትወስን። አላህን አስብ።
በመጨረሻም አደራ የምለው እንተዛዘን፣ እንተሳሰብ፣ ዱዓእ እናድርግ፣ ወደ ጌታችን እንመለስ። አላህ ከገባንበት መከራ አውጥቶ የሰላም አየር የምንተነፍስ ያድርገን። ኣሚን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
120 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:55:37 ቀብር አምላኪዎች ቀብር ለይ መስጂድን ለመገንባት የሚያመጡት ሹብሃ አጠር ካለ መልስ ጋር

ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ

https://t.me/MedrestuImamuAhmed
121 views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:30:48 ወርቃማ ምክር ለእውቀት ፈላጊዎች

"እውቀት በስንፍና እና በእረፍት አይገኝም "!

لفضيلة الشيخ الدكتور محمد بن سعيد رسلان حفظه الله تعالى.

•من الدرس الخامس (شرح فضل العلم).

https://t.me/Umu_Meryem/4450
128 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ