ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች መግቢያ የዚህ መጽሐፍ ዓላማ: ይህ መጽሐፍ ጳውሎስ ከእስር ቤት ሆኖ ከ | Yeka Abado Full Gospel Belivers'church
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች
መግቢያ
የዚህ መጽሐፍ ዓላማ:
ይህ መጽሐፍ ጳውሎስ ከእስር ቤት ሆኖ ከጻፋቸው አራቱ መልእክቶች ውስጥ አንዱ ነው:: (ሌሎቹ መጽሐፍት ኤፌሶን፤ ቆላስያስ እና ፊልሞና ናቸው)
ይህ ቤተክርስቲያን በአውሮፓ የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ነው::
በሐዋርያት 15:40-19:22 በጳውሎስ ሁለተኛው የወንጌል ጉዞ ላይ በህልሙ (በሐዋ 16:9) ወደ መቄዶንያ መተህ እርዳን የሚለውን ራዕይ ካየ በኃላ ነው የመጣው::
ፊልጲስዮስ በመቄዶንያ ግዛት ውስጥ የምትገኝ ወይም በአሁንዋ ሰሜናዊ ግሪክ ውስጥ ያለች ግዛት ናት::
የመጽሐፉ ጸሐፊ እራሱ ጳውሎስ ነው::
በዚህ መልዕክቱ:-
1. ስለሰጡት ስጦታ ሊያመሰግናቸው (ከነሱ ከተለየ በኃላ ስጦታ በተደጋጋሚ የላኩለት ከዚህ ቤተክርስቲያን ብቻ ነው (2ቆሮ 11:9 እና ፊል 4:10-20)
2. ሊያበረታታቸው
3. ሁልጊዜ በጌታ ደስ እንዲላቸው (ምንም እንኳን ከእስር ቤት የጻፈው መልዕክት ቢሆንም 16 ጊዜ ስለደስታ ጽፏል)