Get Mystery Box with random crypto!

“ለመልካም አሰበው።” — ዘፍጥረት 50፥20 ከሚያቃጥል እሳት ዉሰጥ፥ የማይቃጠለዉ ማንነት የሚ | ሰማያዊ ጥበብ 🌞🌞🌞🌞 ⛪

“ለመልካም አሰበው።”
— ዘፍጥረት 50፥20

ከሚያቃጥል እሳት ዉሰጥ፥ የማይቃጠለዉ ማንነት የሚሰራዉ፥ ከእሳቱ በፊት ባገኘን የእግዚአብሔር እሳት እስከሆነ ድረስ፥ ሰባት እቶን እሳት የሚያመጣዉ ሞትን ሳይሆን ኢየሱስን ነዉ!፤ በአባቱ ቤት ዉዱን ሸማ ከለበሰዉ ዮሴፍ፥ ለገዢዎች እንደ በግ እየተስማማ ያለዉን ዮሴፍ፥ ረሃብ በፊቱ ጉልበት ያጣ እንደነበር ማን ለወንድሞቹ ቀድሞ በነገራቸዉ አትሉም፤ እንግዲያዉስ በጥጋቡም በረሃቡም ዘመን መፍትሄዉ ዬሴፍ ጋር ያለዉ እግዚአብሔር ነበር!

የተጣለ፥ ደብዛዉ የጠፋ፥ የእየዬ መነሻ የሆነዉን ዮሴፍ እግዚአብሔር ለመልካም ያጨበት ጊዜ ነበር፥ እንዴት እያዘጋጃችሁ እንደሆነ ባይገባችሁም እንኳን፥ በእናንተ ላይ የተጠራዉን የዋጋ ድርድር፥ ለመልካም የሚያስብ አባት እንዳላችሁ በዚህ አጋጣሚ ጠቁሜአችሁ ልለፍ፥ መልካምነት ከእግዚአብሔር አንፃር እንጂ በምታዩት ልክ ግን አይደለም።

#እንወዶታለን!

#ሰማያዊ_ጥበብ

#ጌታ_እየመጣ_ነዉ!

ይህንን አገልግሎት ለመቀላቀል ሆነ #Share እንዲሁም #like ለማድረግ ቀጥሎ ያለዉን link ይጫኑ

                    @wisdom3in1
                    @wisdom3in1
#ተባረኩ