Get Mystery Box with random crypto!

@whoweareinchrist #መከራን_እንታገስ_ወይስ_በመከራ_ውስጥ_እንታገስ???? በተለያየ | In Christ(በክርስቶስ)

@whoweareinchrist
#መከራን_እንታገስ_ወይስ_በመከራ_ውስጥ_እንታገስ????
በተለያየ መንገድ መከራ አማኞች ላይ ሊደርስ ይችላል ነገር ግን መከራውን እንድንሰብክ አልተጠራንም(ዮሐ 16:33)
አንድ ባህላዊ(Traditional) አባባል አለ መከራ እና ችግር እምነትን ያሳድጋል የሚል ይህ ግን መፅሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም

#እምነት_የሚያድገው_በእግዚአብሔር_ቃል_ነው። (ሮሜ 10:17፤ እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።) እምነት በእግዚአብሔር ቃል የሚመጣ ከሆነ በደንብ(More) #የእግዚአብሔር_ቃልን_ስንሞላ_እምነታችን_ያድጋል።
ነገር ግን መከራ እና ችግር እምነታችንን ይፈትናል(Challenge ያደርጋል) የዛኔ ግን የተፈተነው እምነታችን ትዕግስትን ያስገኝልናል።
ያዕቆብ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ወንድሞቼ ሆይ፤ ልዩ ልዩ መከራ ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት፤
³ ምክንያቱም #የእምነታችሁ_መፈተን #ትዕግሥትን_እንደሚያስገኝ_ታውቃላችሁ።
“በዚህ ብቻ ሳይሆን በመከራችንም ሐሤት እናደርጋለን፤ #ምክንያቱም_መከራ_ትዕግሥትን_እንደሚያስገኝ_እናውቃለን።”ሮሜ 5፥3 (አዲሱ መ.ት)
#ስለዚህ_መከራ_ሲደርስብን_መከራውን_ሳይሆን የምንታገሰው የተነገረን የተስፋ ቃል ላይ ሙጭጭ ብለህ በትዕግስት እምነታችንን ሳንጥል እንድንኖር ነው መፅሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረን። #ምክንያቱም_ትዕግሥት_ማለት_ቁጭ_ብሎ_መጠበቅ_ማለት_ሳይሆን_ትዕግሥት_ማለት_ፅናት(#endurance) #ማለት_ነው። ለምሳሌ እግዚአብሔር አለምን በወንጌል ትዞራለህ ካለህ #ትዕግሥት ማለት በቃ አንድ ቀን ቀኑ ሲመጣ እዞራለው ብሎ #መቀመጥ #ሳይሆን_እግዚአብሔር_የተናገረውን_የተስፋ_ቃል_ይዞ_እዛ የተስፋ ቃል #ላይ_መፅናት_ማለት_ነው።
“#በእምነትና #በትዕግሥት_የተስፋውን #ቃል_የሚወርሱትን_እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንድትሆኑ አንፈልግም።” ዕብ 6፥12 (አዲሱ መ.ት)
“#አብርሃምም #በትዕግሥት_ከጠበቀ #በኋላ_የተሰጠውን_ተስፋ_አገኘ።”ዕብ 6፥15 (አዲሱ መ.ት)
አንድ የእግዚአብሔር ሰው ስለ ትዕግስት እንዲህ ብሎ ነበር "#ትዕግስት_የመንፈስ_ፍሬ_እንጂ_የመከራ_ፍሬ_አይደለም።" ገላትያ 5:22፤ #የመንፈስ_ፍሬ_ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ #ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት.......
#ትዕግስት_የእግዚአብሔር_ባህሪ #ነው "
እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ። እግዚአብሔር፥ #እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ #ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥" (ዘጸ 34:6)
".....#ማንም_እንዳይጠፋ_ወዶ_ስለ_እናንተ_ይታገሣል።"(2ኛ የጴጥ 3:9)
ስለዚህ እምነት ከፍቅር ጋር እንደሚሰራ ሀሉ ከትዕግስትም ጋር ይሰራል
ስለዚህ ሁልጊዜ ስለ ትዕግሥት ስናስብ ማሰብ ያለብን ትዕግሥት በእግዚአብሔር ቃል ላይ የሚመሠረት ነው። #ስለዚህ_ትዕግሥት_ማለት_በእግዚአብሔር_ቃል_ላይ_መፅናት_ነው።
#ለምሳሌ የስንዴ ዘር ዛሬ ዘርተህ ነገ መብቀል አለበት አትልም መሬቱ የፈለገ አመቺ ቢሆንም ዝናቡ በትክክል ቢዘንብም ስንዴ አድጎ ለማፍራት የሚፈልገው ጊዜ አለ ስለዚህ ገበሬው መታገስ አለበት ማለት ነው።
ስለዚህ በትዕግስት በመፅናት በእግዚአብሔር ላይ ባለን እምነት ሳንጠራጠር እንድንኖር መፅሐፍ ቅዱሳችን ያስተምረናል።
ዕብ 6:12-18( ህያው ቃል)
እንዲሁም እግዚአብሔር ተስፋ ለሰጣቸው ሰዎች የተናገረውን #ቃሉን #የማያጥፍ #መሆኑን በዕርግጥ #አውቀው #በትዕግስት እንዲቆዩ ቃሉን በመሃላ አረጋግጦላቸዋል።****እግዚአብሔር መዋሸት ስለማይችል በተስፋውና በቃል ኪዳኑ #የማይናወጥ_እምነት_ሊኖረን_ይገባል።(Emphasis added)

ያዕ 5:11፤ እነሆ፥ #በትዕግሥት_የጸኑትን_ብፁዓን_እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።
ቡሩካን ናችሁ!!!!!!!!!!!!!!

@whoweareinchrist