Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 35.11K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-10-09 22:47:28 ፍልስጥኤም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ

"ፊልሥጢን" فِلَسْطِين ማለት "ፍልስጥኤም" ማለት ሲሆን በአንድ ወቅት የፍሊሥጢን ንጉሥ "ጃሉት" جَالُوت ማለትም "ጎልያድ" እና ሠራዊቱ ከጧሉት ማለትም ከሳኦል ሠራዊት ተዋግተዋል፦
2፥249 ጧሉትም በሠራዊቱ ታጅቦ በወጣ ጊዜ፡- «አላህ በወንዝ ፈታኛችሁ ነው፥ ከርሱም የጠጣ ሰው ከእኔ አይደለም፡፡ ያልቀመሰውም ሰው በእጁ መዝገንን የዘገነ ሰው ብቻ ሲቀር እርሱ ከእኔ ነው» አለ፡፡ ከእነርሱም ጥቂቶች ሲቀሩ ከርሱ ጠጡ፡፡ እርሱ እና እነዚያም ከእርሱ ጋር ያመኑት ወንዙን ባለፉት ጊዜ፡- «ጃሎትን እና ሠራዊቱን በመዋጋት ለኛ ዛሬ ችሎታ የለንም» አሉት፡፡ እነዚያ እነርሱ አላህን ተገናኝዎች መኾናቸው የሚያረጋግጡት፡- «ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት፤ አላህም ከታጋሾች ጋር ነው» አሉ፡፡ فَلَمَّا فَصَلَ طَالُوتُ بِالْجُنُودِ قَالَ إِنَّ اللَّهَ مُبْتَلِيكُم بِنَهَرٍ فَمَن شَرِبَ مِنْهُ فَلَيْسَ مِنِّي وَمَن لَّمْ يَطْعَمْهُ فَإِنَّهُ مِنِّي إِلَّا مَنِ اغْتَرَفَ غُرْفَةً بِيَدِهِ ۚ فَشَرِبُوا مِنْهُ إِلَّا قَلِيلًا مِّنْهُمْ ۚ فَلَمَّا جَاوَزَهُ هُوَ وَالَّذِينَ آمَنُوا مَعَهُ قَالُوا لَا طَاقَةَ لَنَا الْيَوْمَ بِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ ۚ قَالَ الَّذِينَ يَظُنُّونَ أَنَّهُم مُّلَاقُو اللَّهِ كَم مِّن فِئَةٍ قَلِيلَةٍ غَلَبَتْ فِئَةً كَثِيرَةً بِإِذْنِ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ

ከዚያም በጦርነቱ ተፋልመው ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ዳውድ ጃሉትን ገሎታል፦
2፥250 ለጃሉት እና ለሠራዊቱ በተሰለፉም ጊዜ፡- «ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አንቧቧ፤ ጫማዎቻችንንም አደላድል፤ በከሓዲያን ሕዝቦችም ላይ እርዳን» አሉ፡፡ وَلَمَّا بَرَزُوا لِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ قَالُوا رَبَّنَا أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًا وَثَبِّتْ أَقْدَامَنَا وَانصُرْنَا عَلَى الْقَوْمِ الْكَافِرِينَ
2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ

ቁርኣን ላይ ስለ ፍልስጥኤማውያን የሚናገረው እነዚህ አናቅጽ ላይ ነው። ሚሽነሪዎች፦ "ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም የምትባል አገር የላቸውም" እያሉ ባላነበቡት ነገር ይዘባርቃሉ። ፈጣሪ እስራኤልን ከግብጽ ምድር እንዳወጣ ሁሉ በጥንት ጊዜ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር አውጥቶ የራሳቸው ግዛት ሰቷቸዋል፦
አሞጽ 9፥7 እስራኤልን ከግብጽ ምድር፥ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር፥ ሶርያውያንንም ከቂር አላወጣሁምን?
ኢዮኤል 3፥4 ጢሮስና ሲዶና የፍልስጥኤምም ግዛት ሁሉ ሆይ! ከእናንተ ጋር ለእኔ ምን አለኝ? በውኑ ብድራትን ትመልሱልኛላችሁን?

"የፍልስጥኤምም ግዛት" የሚለው ይሰመርበት ፍልስጥኤም ግዛት ከነበረች ለምን መብቷ አይከበረም? እስራኤላውያን ቦታቸው መጥተው ሰፈሩባቸው እንጂ ጥንትም ቢሆን የእስራኤል ቅም አያት አብርሃም ከከላዳውያን ኡር በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀምጧል፦
ዘፍጥረት 21፥34 "አብርሃምም በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀመጠ"።

ፍልስጥኤም መጤ ሳትሆን የራሷ ምድር ስለሆነ "በፍልስጥኤም ምድር" የሚል ኃይለ-ቃል ተጽፏል። ባይብል ላይ ብዙ ቦታ "የፍልስጥኤም ምድር" እያለ ይናገራል፦
ኤርምያስ 25፥20 የተደባለቀውንም ሕዝብ ሁሉ፥ የዖፅ ምድር ነገሥታትንም ሁሉ፥ "የፍልስጥኤም ምድር" ነገሥታትንም ሁሉ አስቀሎናንም ጋዛንም አቃሮንንም የአዞጦንንም ቅሬታ"።
ዘጸአት 13፥17 እንዲህም ሆነ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ፥ ምንም ቅርብ ቢሆን እግዚአብሔር "በፍልስጥኤማውያን ምድር" መንገድ አልመራቸውም።

ፍልስጥኤማውያን የራሳቸው አገር አላቸው፥ እስራኤላውያን የሰፈሩበት ከነዓን ሁሉ ሳይቀር የፍልስጥኤማውያን ምድር ነው፦
2ኛ ነገሥት 8፥2 ሴቲቱም ተነሥታ እንደ እግዚአብሔር ሰው ቃል አደረገች፤ ከቤተ ሰብዋም ጋር ሄዳ "በፍልስጥኤም አገር" ሰባት ዓመት ተቀመጠች"*።
ሶፎንያስ 2፥5 "የፍልስጥኤማውያን ምድር ከነዓን ሆይ"፥ የእግዚአብሔር ቃል በአንተ ላይ ነው።

ዛሬ አገር እና ግዛት እንደሌላቸው እና መጤ እንደሆኑ ታይቶ እየተፈናቀሉ ነው፥ አሏህ ነስሩን ያቅርብላቸው! አሚን። ይህንን የምንለው ስለ ሐቅ እና ስለ ፍትሕ ነው፥ "ኢሥላም ሰም እና ወርቅ የያዘ ቅኔ ነው፥ ሰሙ ሐቅ ሲሆን ወርቁ ፍትሕ ነው" ስንል ዕውር ድንብ ጸለምተኛ ሙግት ይዘን ሳይሆን ጠቅሰንና አጣቅሰን በመሞገትና በመሟገት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
13.5K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-17 08:02:00 ክርስቲያኖች፦ "ኢየሱስ ፍጥረትን ፈጥሯል" ብለው ከጳውሎስ ደብዳቤዎች ይጠቅሳሉ። እኛ ደግሞ "ኢየሱስ ምንም አልፈጠረም" ብለን ከጳውሎስ ደብዳቤዎች እንሞግታለን። ኢንሻላህ ከታች ያለውን ሊንክ በማስፈንጠር አድምጡ እና አስደምጡ!


12.9K viewsedited  05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-15 20:59:40 በዐፋርኛ ደርሥ ተለቋል። ዐፋርኛ የምትችሉ ግቡ፦ https://t.me/wahidcomafarega/11
12.7K views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-15 16:30:22 ሥላሴአዊ ቅጥፈት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

ከ 260 እስከ 339 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው የቂሳሪያው ኤጲስ ቆጶስ አውሳብዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክ"Church History" በሚል መጽሐፉ ሐዋርያው ማቴዎስ ለዕብራውያን በዕብራይስጥ ቋንቋ ደብዳቤ እንደጻፈላቸው ተናግሯል፦
፨፦ "ስለዚህ ማቴዎስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ደብዳቤ ጽፏል"።
(አውሳቢዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክ መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 39 ቁጥር 16)

፨፦ "እርሱ ማቴዎስ በመጀመሪያ ለዕብራውያን የሰበከው ነው"።
(አውሳቢዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክ መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 39 ቁጥር 16)

ማቴዎስ ይህንን ደብዳቤአዊ ወንጌል ከ 45 እስከ 55 ድኅረ ልደት እንደጻፈ ይገመታል፥ የመጀመሪያ መቶ ክፍለ ዘመን ይኖሩ የነበሩት ኢቦናይት የሚባሉ አይሁዳውያን የኢየሱስ ተከታዮች ማቴዎስ ለዕብራውያን የጻፈውን ይህንን ወንጌል ብቻ ይቀበሉ እንደነበር አውሳብዮስ ይናገራል፦
"እና ለዕብራውያን ተደረሰ የተባለውን ወንጌል ብቻ ይጠቀሙ ነበር"።
(አውሳቢዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክ መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 25 ቁጥር 4)

የቂሳሪያው አውሳብዮስ "የወንጌል ማረጋገጫ"Proof of the Gospel" በሚል መጽሐፉ ላይ ማቴዎስ በዕብራይስጥ በጻፈው ወንጌል ላይ ኢየሱስ ለሐዋርያት ያላቸው፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ! ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተማሯቸው" በማለት እንዳዘዛቸው ተናግሯል፦
፨፦ "ከአንድ ቃል እና ድምፅ ጋር እርሱም ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ! ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተማሯቸው"።
(አውሳቢዮስ የወንጌል ማረጋገጫ ቅጽ 1 መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 6 ቁጥር 132 ገጽ 152)

፨፦ "እርሱም ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ"።
(አውሳቢዮስ የወንጌል ማረጋገጫ ቅጽ 1 መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 7 ቁጥር 136 ገጽ 157)

፨፦ "እርሱም ለእነርሱ እንዲህ አላቸው፦ "አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ"።
(አውሳቢዮስ የወንጌል ማረጋገጫ ቅጽ 1 መጽሐፍ 3 ምዕራፍ 7 ቁጥር 138 ገጽ 159)

"አሕዛብ" የሚለው የግዕዝ ቃል "ሕዝብ" ለሚለው ብዜት ሲሆን በጸያፍ ርቢ "ሕዝቦች" ማለት ነው፥ በዕብራይስጥ ለዕብራውያን በተጻፈው የመጀመሪያው የማቴዎስ ወንጌል ላይ ኢየሱስ፦ "አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ" የሚል ሆኖ ሳለ ስሙ እና ማንነቱ በውል የማይታወቅ ሰው የማርቆስን ወንጌል መሠረት አድርጎ በግሪክ ኮይኔ በማቴዎስ ዳቦ ስም የማቴዎስ ወንጌል አዘጋጀ። በዚህ ወንጌል ውስጥ፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው" የሚል ሥላሴአዊ ቅጥፈት ተቀጠፈ፥ ዓይን ያስፈጠጠ እና ጥርስ ያገጠጠ ይህንን ሐቅ መድብለ-ዕውቀት"encyclopedia" እንዲህ ያትታሉ፦
፨፦ "ማቴዎስ 28፥19 በኃላ በቤተክርስቲያን ሁኔታ በተለየ ብቻ ቀኖናዊ የሆነ ነው፥ ለዛ ነው ዓለም አቀፋዊነቷ ከቀደምት የክርስቲያን ታሪክ እውነታዎች ጋር የሚቃረን የሆነው። የሥላሴአውያን ቀመር ለኢየሱስ ንግግር ባዕድ ነው"።
(ዓለም ዓቀር መደበኛ የባይብል መድብለ ዕውቀት ቅጽ 4, ገጽ 2637)

፨፦ "የጥምቀት ቀመር "በኢየሱስ ስም" ከሚል ወደ "በአብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ስም" ወደሚል በዓለም ዐቀፍ ቤተክርስቲያን በሁለተኛው ክፍለ ዘመን ተለውጧል"።
(የካቶሊክ መድብለ ዕውቀት ቅጽ 2, ገጽ 263)

በተጨማሪም "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው" የሚለውን ሥላሴአዊ ቅጥፈት እና ቅሰጣ የባይብል ማብራሪያ"Commentary" እና እትም"Version" ወሮበላ መሆኑን እንጩን ፍርጥ አርገው ነግረውናል፦
፨፦ "በአብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ስም" የኢየሱስ ቃል ሳይሆን በኃላ የተጨመረ ቃል ነው"።
(ቴንደል የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ቅጽ 1, ገጽ 275

፨፦ "ዘመናዊ ኂስ ይህንን የሥላሴአውያን ቀመር ኢየሱስን ማስዋሸት ነው፥ ያ በኃላ ላይ የቤተክርስቲያን ትውፊት የሚወክል ነው"።
(1989 አዲሱ የተሻሻለ የመደበኛ ባይብል እትም)

የሥላሴ አማንያን"trinitarian" ሆይ! ፈጣሪን "አንድ ነው" ባላችሁበት አፍ «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም በተውሒድ ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.8K viewsedited  13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-09 20:53:24 ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥72 እነሆ በአሏህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ

በኢሥላም አስተምህሮት ሰው በአሏህ ላይ ላሻረከው የሺርክ ወንጀል አሏህ በእርግጥ ጀነትን እርም አድርጎበታል፥ ለሙሽሪክ መኖሪያውም እሳት ናት። አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፥ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፦
5፥72 እነሆ በአሏህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ
4፥48 አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ

ወደ ባይብል ስንሄድም የማያምኑ የሚቀጡበት ቅጣት ዘውታሪ ቅጣት ለመሆኑ እኵሌቶቹ ወደ እፍረት እና ወደ ዘላለም ጕስቍልና እንደሚሄዱ ይናገራል፦
ዳንኤል 12፥2 በምድርም ትቢያ ውስጥ ካንቀላፉቱ ብዙዎች ይነቃሉ፤ እኵሌቶቹ ወደ ዘላለም ሕይወት፥ እኵሌቶቹም ወደ እፍረት እና "ወደ ዘላለም ጕስቍልና"።
ኤርምያስ 23፥40 የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን "የዘላለምን እፍረት" አመጣባችኋለሁ።

ይህ ሆኖ ሳለ "ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት"universal salvation" የሚባለው ትምህርት "ሰው ሁሉ የሚቀጣው ቅጣት ተቀጥቶ ሁሉም ከገሃነም ይድንና ገነት ይገባል" የሚል ትምህርት ነው፥ ይህንን ትምርህት ከሚያስተምሩት የጥንት የቤተክርስቲያን አበው መካከል፣ በ 180 ድኅረ ልደት ቅዱስ ፔንታነስ፣ በ 150 ድኅረ ልደት የእስክንድርያው ቀለሜንጦስ፣ በ 220 ድኅረ ልደት የእስክንድርያው አርጌንስ እና በ 400 ድኅረ ልደት ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ተጠቃሽ ናቸው። እነርሱም ከሚጠቅሱስ ተወዳጆች ጥቅሳት መካከል ግንባር ቀደም ይህ ነው፦
ማርቆስ 9፥49 ሰው ሁሉ በእሳት ይቀመማልና፥ መሥዋዕትም ሁሉ በጨው ይቀመማል።

መሥዋዕት ሁሉ በጨው የሚቀመመው በጨው እንደሆነ ሰውም በእሳት መቀጣቱ ለእርማት መሆኑን ይናገራሉ፦
ዕብራውያን 12፥9-11 ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን? እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል። ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።

"እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል" በሚለው ውስጥ ሁሉም ጥፋተኛ የጥፋቱን ልክ ተቀጥቶ ወደ ገነት ይገባል የሚል ትምህርት ነው፥ "ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም" ማለቱ "የገሃነም ቅጣት ጊዜአዊ ነው" የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሰዋል፦
1 ጢሞቴዎስ 4፥10 ሰውን ሁሉ ይልቁንም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው አምላክ ተስፋ ስለምናደርግ ነው።

ሕያው አምላክ የሚያምኑት ብቻ ሳይሆን "ሰውን ሁሉ" እንደሚያድን ከላይ ያለው ጥቅስ ፍንጭ ይሰጣል፥ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን ይህ ጸጋ የተገለጠው ሰዎች ሁሉ ሊድኑ በሚወድ በአምላክ ፊት መልካም እና ደስ የሚያሰኝ ጳውሎስ ተናግሯል፦
ቲቶ 2፥11 ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና።
1 ጢሞቴዎስ 2፥3 ሰዎች ሁሉ ሊድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካም እና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።
ሮሜ 5፥19 በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።

"ብዙዎች" የሚለው ቃል "ሁሉም" በሚል ይረዱትና ሁሉም ሰው በአንዱ አዳም ኃጢአተኞች ከሆኑ ሁሉም ሰው በአንዱ ክርስቶስ ጻድቃን ይሆናሉ የሚል ትምህርት ነው። ታዲያ ለምን ብዙ ቦታ "በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ" ይላል?፦
2 ተሰሎንቄ 1፥9 ከጌታ ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ። οἵτινες δίκην τίσουσιν ὄλεθρον αἰώνιον ἀπὸ προσώπου τοῦ Κυρίου καὶ ἀπὸ τῆς δόξης τῆς ἰσχύος αὐτοῦ,

እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘላለም" የሚለው የግሪከኛ ቃል "አይኦንዮን" αἰώνιον ሲሆን መጨረሻ የሌለው ዝንተ ዓለም ጊዜ ብቻ ሳይሆን የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን ስለሚያመለክት "ቅጣቱ ጊዜአዊ ነው" በማለት "አይኦንዮን" αἰώνιον ለማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን የተጠቀመበት ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ይሁዳ 1፥7 "በዘላለም እሳት" እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል። πρόκεινται δεῖγμα πυρὸς αἰωνίου δίκην ὑπέχουσαι.

"ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች የተቀጡት ለውስን ጊዜ ቢሆንም ቅጣታቸውን "በዘላለም እሳት" በማለት ተናገረ ማለት መጨረሻ የሌለው ዝንተ ዓለም ጊዜ አይደለም" በማለት ይሞግታሉ። ይህ ሙግት ሥነ ልቡናዊ ሙግት ቢመስልም ውኃ የሚያነሳ እና የሚቋጥር ሙግት አይደለም፥ ምክንያቱም ሰው በገነት ለሚኖረው ዘላለማዊ ሕይወት የገባው ቃል ተመሳሳይ "አይኦንዮን" αἰώνιον ነው፦
ማቴዎስ 25፥46 እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ። καὶ ἀπελεύσονται οὗτοι εἰς κόλασιν αἰώνιον, οἱ δὲ δίκαιοι εἰς ζωὴν αἰώνιον.

"ዘላለም ቅጣት" ለሚለው የገባው "አይኦንዮን" αἰώνιον የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን ካመለከተ ጻድቃን የሚገቡበት "ዘላለም ሕይወት" ለሚለው የገባው "አይኦንዮን" αἰώνιον የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜ ነውን? ገሃነም ጊዜአዊ ከሆነ ቢያንስ "ወደ ገነት ይገባሉ" ይባል ይሆናል፥ ገነት እንደ ገሃነም ጊዜአዊ ከሆነ ከገነት ወደ የት ይገባሉ? ይህ የተመታ እና የተምታታ ትምህርት እነ ቅዱስ ፔንታነስ፣ እነ የእስክንድርያው ቀለሜንጦስ፣ እነ የእስክንድርያው አርጌንስ፣ እነ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ የጠነሰሱት ጥንስስ የጳውሎስን ትምህርት መሠረት አርገው ነው። ዛሬ በዘመናችን ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት የሚባል ትምህርት ከሚያስተምሩ መካከል የእግዚአብሔር መንግሥት ቤተክርስቲያን መስራች ካሳ ኬርጋ እና አዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ የመሳሰሉት ናቸው።
ይህንን ትምህርት የሚያስየምሩት እና ባለማወቅ የሚማሩትን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.7K views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-06 12:49:00
አሥ ሠላም ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር ይህንን የሃይማኖት ንጽጽር መተግበሪያ"application" ለሕዝበ ሙሥሊሙ አዘጋጅቷል። በገጠር አውታረ መረብ"network" የሌላቸው እና በከተማ የአውታረ መረብ ችግር ያለባቸው ያለ አውታረ መረብ ይህንን መተግበሪያ በማውረድ መጠቀም ይችላሉ። አውርደው በውስጡ ያለውን ርእሰ ጉዳይ እንዴት መጠቀም እንዳለብዎ እዚህ ላይ የተቀመጠውን ቪድዮ ይመልከቱ!
ሁላችንም በፓስት፣ በኮሜት፣ በራሳችሁ የጊዜ መስመር"timeline" ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ መሆን ይችላሉ።
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.hexlabs.wahidislamicapologetics
12.8K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-29 04:34:56
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ተውሒድ የሁለቱም ዓለም ስኬት ነው፥ በተውሒድ ዙሪያ "ካሊቂ አድን ቢቶ"(ፈጣሪ አንድ ነው) በሚል ርእስ በስልጥኛ ቋንቋ ያዘጋጀነው 6ኛ መጽሐፌ በአት ተውባህ የመጻሕፍት መደብር ያገኙታል። ለበለጠ መረጃ፦
ወንድም ዐብዱር ራሕማን +251920781016 ብለው ይደውሉ!

የስልጤ ሕዝብ ላይ ካንዣበበት የኩፍር ማንዣበብ ነጻ ለማውጣት "ይህ መጽሐፍ ሁነኛ ፍቱን መድኃኒት ነው" ብለን ስለምናምን ለሌሎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሼር እናድርግ። ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
13.0K views01:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-30 01:02:02 በቅርብ ቀን በቪድዮ ተከታታይ ትምህርት በዚህ ዩቱብ ቻናል ይለቀቃል። ሰብስክራይብ፣ ሼር እና ላይክ በማድረግ ተደራሽነቱን ይወጡ! https://youtube.com/@Wahidislamicapologist
12.6K views22:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-26 12:12:30 ኢየሱስ አብ ነውን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ "አስገኚው"፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

አምላካችን አሏህ በቁርኣን ከተገለጹ ዘጠና ዘጠኝ ስሞቹ አንዱ "አል ባሪእ" الْبَارِئ ማለትም "አስገኚው" ነው፦
59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ "አስገኚው"፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

በዕብራይስጥ ለአንዱ አምላክ "አብ" אָ֑ב ማለት "አስገኚ" "ምንጭ" ማለት ነው፥ አንዱ አምላክ ሰውን ጭቃ አርጎ ስለ ሠራ "አብ" אָ֑ב ተብሏል፦
ኢሳይያስ 64፥8 ያህዌህ ሆይ! አንተ አባታችን ነህ፤ እኛ ጭቃ ነን አንተም ሠሪያችን ነህ፥ እኛም ሁላችን የእጅህ ሥራ ነን። יְהוָ֖ה אָבִ֣ינוּ אָ֑תָּה אֲנַ֤חְנוּ הַחֹ֙מֶר֙ וְאַתָּ֣ה יֹצְרֵ֔נוּ וּמַעֲשֵׂ֥ה יָדְךָ֖ כֻּלָּֽנוּ׃

እዚህ አንቀጽ ላይ አንዱ አምላክ "አብ" אָ֑ב ሲባል ሰዎች "ጭቃ" ተብለዋል፥ ጭቃው የእጁ ሥራ ሲሆን "አባት" የሚለው "ሠሪ" ማለት ስለሆነ "አባታችን" የሚለው "ሠሪያችን" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል። "ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? ሲልም "ለሁላችን አንድ ሠሪ" መኖሩን የሚያሳይ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን? הֲלֹ֨וא אָ֤ב אֶחָד֙ לְכֻלָּ֔נוּ הֲלֹ֛וא אֵ֥ל אֶֽחָ֖ד בְּרָאָ֑נוּ
ዮሐንስ 8፥41 አንድ አባት አለን፥ እርሱም አምላክ ነው። ἕνα Πατέρα ἔχομεν τὸν Θεόν.
ኤፌሶን 4፥6 አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። εἷς Θεὸς καὶ Πατὴρ πάντων,

"አባት" ለአንዱ አምላክ ሲቀጸል በራሱ "አስገኚ" ማለት እንጂ "የባሕርይ አባት" ማለት አይደለም። ይህ ሆኖ ሳለ የሐዋርያት ቤተክርስቲያን በተለምዶው ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" የሚባሉት "ኢየሱስ አብ ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ዮሐንስ 14፥10 ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል። ὁ δὲ Πατὴρ ἐν ἐμοὶ μένων ποιεῖ τὰ ἔργα αὐτοῦ.

ይህ ጥቅስ ጭራሽ "እኔ" የሚለው ማንነት እና "እኔ" በሚለው የሚኖረው አብ ሁለት ማንነት እንደሆኑ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "የሚኖር" ለሚለው የገባው ቃል "ሜኖን" μένων ነው። አብ በኢየሱስ መኖሩ ኢየሱስን አብ ካሰኘውማ በፍቅር የሚኖር ሰው አምላክ ሊሆን ነው፦
1ኛ ዮሐንስ 4፥16 በፍቅርም የሚኖር በአምላክ ይኖራል፥ "አምላክ በእርሱ ይኖራል"። καὶ ὁ μένων ἐν τῇ ἀγάπῃ ἐν τῷ Θεῷ μένει καὶ ὁ Θεὸς ἐν αὐτῷ μένει.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይኖራል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜኔይ" μένει ሲሆን ከላይ ካለው ጋር በተመሳሳይ መሠረቱ "ሜኖ" μένω ነው፥ ታዲያ በፍቅር የሚኖር ሰው አምላክ ነውን? በመቀጠል "ኢየሱስ አብ ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ዮሐንስ 14፥11 እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ። πιστεύετέ μοι ὅτι ἐγὼ ἐν τῷ Πατρὶ καὶ ὁ Πατὴρ ἐν ἐμοί·

"እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ" ማለቱ ኢየሱስን አብ አብን ኢየሱስ ካደረገው ሐዋርያት ኢየሱስ ወይም ኢየሱስ ሐዋርያት ይሆኑ ነበር፦
ዮሐንስ 14፥20 እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ። ἐν ἐκείνῃ τῇ ἡμέρᾳ γνώσεσθε ὑμεῖς ὅτι ἐγὼ ἐν τῷ Πατρί μου καὶ ὑμεῖς ἐν ἐμοὶ κἀγὼ ἐν ὑμῖν.

"እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ" ማለቱ ሐዋርያት ከኢየሱስ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት የሚያሳይ እንጂ ሐዋርያትን ኢየሱስ ካላደረገ እንግዲያውስ "እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ" ማለቱ አብ ከኢየሱስ ጋር ያለውን ግኑኝነት የሚያሳይ እንጂ ኢየሱስን አብ አያደርገውም። በነገራችን ላይ ሥላሴአውያን ለኢየሱስ አምላክነት ከሚጠቅሷቸው ተወዳጆች ጥቅስ አንዱ ነውና ሙግቱ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ አብ ወይም አምላክ ሳይሆን የአምላክ መልእክተኛ ነው። እናንተንም አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.6K views09:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 12:29:22 ኢንጂል

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

ኢየሱስ ከአምላኩ ግልጠተ መለኮት በተቀበለበት በዐረማይስጥ ቋንቋ "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ማለት "ብሥራት" "የምስራች" "መልካም ዜና" ማለት ሲሆን "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ወደ ዐረቢኛ ሙዐረብ ሆኖ ሲገባ "ኢንጂል" إِنْجِيل ሲባል፣ ወደ ግሪክ ሲገባ "ዩአንጌሎስ" εὐάγγελος ሲባል፣ ወደ ግዕዝ ሲገባ ደግሞ "ወንጌል" ተባለ። አምላካችን አሏህ ለዒሣ ኢንጂልን በመስጠት መልእክተኛ አርጎ ልኮታል፦
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

በባይብልም ቢሆን ኢየሱስ ከላከው ከአምላክ መልእክት እየሰማ የሚያስተላለፍ መልእክተኛ ነበር፦
ዮሐንስ 8፥26 የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ "የሰማሁትን" ይህን ለዓለም እናገራለሁ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ "የሰማሁትን" እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። νῦν δὲ ζητεῖτέ με ἀποκτεῖναι, ἄνθρωπον ὃς τὴν ἀλήθειαν ὑμῖν λελάληκα, ἣν ἤκουσα παρὰ τοῦ Θεοῦ·

እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" አሰሚ ባለቤት ሲሆን "ሰው" ሰሚ ተሳቢ ነው፥ በአምላክ እና በሰው መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ"transitive verb" አለ። መልእክተኛው ኢየሱስ የሚናገረው የላከው እንደነገረው እንጂ ከራሱ ምንም አልተናገረም፦
ዮሐንስ 12፥50 ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን "የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ"።

"ትእዛዝ ሰጠኝ" የሚለው ይሰመርበት! ይህቺም ትእዛዝ ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የምትል ተውሒድ ስትሆን የዘላለም ሕይወት ናት፦
ዮሐንስ 12፥50 "ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች" አውቃለሁ።
ማቴዎስ 22፥38 ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ "እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው"..የምትል ናት።

ጥንትም በቅዱሳን ነቢያት ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያትም ከኢየሱስ የተገኘው ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የሚል ጭብጥ ነው፦
2 ጴጥሮስ 3፥2 በቅዱሳን ነቢያትም ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያቶቻችሁም ያገኛችኋትን የጌታን እና የመድኃኒትን ትእዛዝ እንድታስቡ በሁለቱ እያሳሰብኋችሁ ቅን ልቡናችሁን አነቃቃለሁ።

ኢየሱስ "የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ" ሲል ይህንን የአምላክ ትእዛዝ ከአምላክ ተቀብሎ ለሐዋርያት የሰጠው ቃል የአምላክ ቃል ነው፦
ዮሐንስ 17፥8 "የሰጠኸኝን ቃል" ሰጥቻቸዋለሁና።
ዮሐንስ 17፥14 እኔ "ቃልህን" ሰጥቻቸዋለሁ።

ኢየሱስ ወደ አምላኩ ሲጸልይ በሁለተኛ መደብ "ቃልህን" ማለቱ በራሱ የተሰጠው "ቃል" የአምላክ ቃል ነው፥ ሕዝቡም ሲሰማ የነበረው ቃል የላከው የአምላክ ቃል እንጂ የመልእክተኛው የራሱ ቃል አይደለም፦
ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው፦ "ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም"።
ዮሐንስ 14፥24 "የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም"።
ሉቃስ 5፥1 ሕዝቡም "የአምላክን ቃል" እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር።
ዮሐንስ 8፥47 ከአምላክ የሆነ "የአምላክን ቃል" ይሰማል።
ዮሐንስ 3፥34 አምላክ የላከው የአምላክንን ቃል ይናገራልና።

ኢየሱስ መልእክተኛ ነቢይ ሆኖ ከአምላኩ የተሰጠውን የአምላክን ቃል ይናገር ከነበረ እና ከራሱ ምንም ካልተናገረ ኢየሱስ ሙሉ ዕውቀት የለውም፥ ምክንያቱም ከአምላኩ የሚሰማው እርሱ ጋር ከሌለ እና ከአምላኩ ሰምቶ ከተናገረ ከላከው ዕውቀት ጋር እኩል ዕውቀት አይሆንም። እንግዲህ ኢየሱስ ከአምላኩ እየሰማ የተሰጠው የአምላክ ቃል ወንጌል ይባላል፥ ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ስለዚህ ወንጌል እናያለን........

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.9K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ