Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.94K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-15 20:36:33
"የተደበቀው እውነት" በአፋን ኦሮሞ "Dhugaa dhokate" በሚል ኢንሻላህ በቅርብ ቀን ይጠብቁ!

እስከዛው በአፋን ኦሮሞ ለሟሟሻ ያክል መጣጥፍ ያንብቡ፦ https://t.me/Wahidomar1/62
7.4K viewsedited  17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-10 15:07:01
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

ያ ጀመዓህ! "የተደበቀው እውነት" የሚለው መጽሐፍ ለሁለተኛ ጊዜ ታተመ። በክርስቲያኖች ሚሽነሪዎች ከፍተኛ ተቃውሞ የደረሰበት ይህ መጽሐፍ በክርስቲያኖች ሚሽነሪዎች አስታዋዋቂነት"promotion" የተነሳ በታተመ በሳምንቱ አልቋል። ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ"፦ "አሏህ ይህንን ዲን ከፈለገ በከሃዲያንም ቢሆን ያጠናክረዋል" ስላሉን በእነርሱ አስታዋዋቂነት ለብዙ አንባቢያን እንዲዳረስ ምክንያት ሆኗል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነሆ ሙሥሊም የሆነች ነፍስ እንጂ ሌላው ጀነትን አይገባትም፥ አሏህ ይህንን ዲን ከፈለገ በከሃዲያንም ቢሆን ያጠናክረዋል"። ﻋَﻦْ ﺃَﺑِﻲ ﻫُﺮَﻳْﺮَﺓَ، ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗَﺎﻝ ﻋﻦ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲّ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﺃﻧﻪ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳَﺪْﺧُﻞُ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻧَﻔْﺲٌ ﻣُﺴْﻠِﻤَﺔٌ، ﻭَﺃَﻥَّ ﺍﻟﻠﻪَ ﻳُﺆَﻳِّﺪُ ﻫَﺬَﺍ ﺍﻟﺪِّﻳﻦَ ﺑِﺎﻟﺮَّﺟُﻞِ ﺍﻟْﻔَﺎﺟِﺮِ‏

የመጀመሪያው ዕትም በታተመ በ 20 ቀኑ ዛሬ ገበያ ላይ ውሏል። መጽሐፉን ለምትፈልጉ፦
፨፦ አዲስ አበባ መርካርቶ አንዋር መሥጂድ ኢሥላማዊ መጻሕፍት መደብር ውስጥ፣
፨፦ አዲስ አበባ ፒያሳ Abdu Book Delivery
0929574133
፨፦ አየር ጤና አንሷር መሥጂድ 0963796354

የበለጠ መረጃ ለማግኘት +251920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!

መጽሐፉ ተደራሽነት እንዲኖረው ባለው የማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!

ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
12.6K viewsedited  12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-08 18:21:50
አልሰማ አላችሁን

መምህር ዮሐንስ ጌታቸው፦ "እግዚአብሔር ዓይን፣ እጅ፣ እግር እንዳለው" በግልጽ ተናግረዋል። ይደመጥ!

እነዚህ የአካል ክፍሎች ትርጉም መስጠት ሠለስቱ ምዕት ከልክለዋል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 19 ቁጥር 33
“ለእግዚአብሔር ዓይኖች እና ጆሮዎች እንዳሉት መጽሐፍት የተናገሩት እና የቀሩት እንዳሉት ስለ እግዚአብሔር የተነገረው ሁሉ የታመነ እውነተኛ እንደሆነ እናምናለን፥ ነገር ግን አይመረመርም አይታሰብም”።

"ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱ፦ "የቀሩት" ያሉት ከዓይኖች እና ከጆሮዎች ሌላ የተገለጹትን የአካል ክፍሎች ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30
“ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።

እርማችሁን አውጡ! ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለ እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጅ፣ ጥፍር፣ እግር እንዳለው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62
“እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”።

በዚህ ዚሪያ ከዚህ በፊት የተጻፈ መጣጥፍ ያንብቡ፦ https://t.me/Wahidcom/3501

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
10.0K viewsedited  15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-06 11:40:04 "የተደበቀው እውነት" የሚለውን መጽሐፍ ዱባይ ላይ የምትፈልጉ እኅት ሰላምን በውስጥ ያናግሩ፦ @SeuweSe
9.0K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 10:21:26 ላብ አደር

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

43፥32 ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ከፊላቸውን ከከፊሉ በላይ በደረጃዎች (በሀብት) አበለጥን፡፡ وَرَفَعْنَا بَعْضَهُمْ فَوْقَ بَعْضٍ دَرَجَاتٍ لِّيَتَّخِذَ بَعْضُهُم بَعْضًا سُخْرِيًّا

"አደር" ማለት የዕለት ለዕለት የአኗኗርን ዘይቤን ለማመልከት የሚመጣ ፈሊጣዊ አነጋር እንጂ "አዳር" ከሚለው ቃል የሚሳለጥ አይደለም፥ ለምሳሌ፦ "ሠርቶ አደር" "ወጥቶ አደር" "አርሶ አደር" "አርብቶ አደር" "ወዝ አደር" "ላብ አደር" ሲባል ይህንን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ስለ ላብ አደር የሠራተኛን ዋጋ ላቡ ሳይደርቅ ክፈሉ" ብለው ነግረውናል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 16 ቁጥር 8
ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የሠራተኛን ዋጋ ላቡ ሳይደርቅ ክፈሉ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أَعْطُوا الأَجِيرَ أَجْرَهُ قَبْلَ أَنْ يَجِفَّ عَرَقُهُ ‏"‏ ‏.‏

አንድ አሠሪ የሠራተኛውን ላብ የማይከፍል ከሆነ አሏህ በትንሣኤ ቀን ከሚጻረራቸው ሦስት ሰዎች አንዱ ይሆናል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 16 ቁጥር 7
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ እንዲህ ይላል፦ "እኔ በትንሣኤ ቀን የሥስት ሰዎች ተጻራሪ ነኝ፥ እኔ የማንም ተጻራሪ ከሆንኩ በትንሣኤ ቀን አሸንፈዋለሁ። በስሜ ቃል የገባ ከዚያም የሚያታልል ሰው፣ ነጻ ሰው ሸጦ ዋጋውን የሚበላ ሰው እና ሠራተኛ የሚቀጥር እና ተጠቅሞበት ከዚያም ደመወዙን የማይሰጥ ሰው ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ ثَلاَثَةٌ أَنَا خَصْمُهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَمَنْ كُنْتُ خَصْمَهُ خَصَمْتُهُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ رَجُلٌ أَعْطَى بِي ثُمَّ غَدَرَ وَرَجُلٌ بَاعَ حُرًّا فَأَكَلَ ثَمَنَهُ وَرَجُلٌ اسْتَأْجَرَ أَجِيرًا فَاسْتَوْفَى مِنْهُ وَلَمْ يُوفِهِ أَجْرَهُ ‏"‏ ‏.‏

አምላካችን አሏህ በቅርቢቱ ሕይወት ኑሯችንን በመካከላችን አከፋሏል፥ ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ሀብትን ሰጥቶአል፦
43፥32 እነርሱ የጌታህን ችሮታ ያከፋፍላሉን? እኛ በቅርቢቱ ሕይወት ኑሯቸውን በመካከላቸው አከፋፍለናል፡፡ ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ከፊላቸውን ከከፊሉ በላይ በደረጃዎች (በሀብት) አበለጥን፡፡ የጌታህም ጸጋ ገነት ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ናት፡፡ أَهُمْ يَقْسِمُونَ رَحْمَتَ رَبِّكَ ۚ نَحْنُ قَسَمْنَا بَيْنَهُم مَّعِيشَتَهُمْ فِي الْحَيَاةِ الدُّنْيَا ۚ وَرَفَعْنَا بَعْضَهُمْ فَوْقَ بَعْضٍ دَرَجَاتٍ لِّيَتَّخِذَ بَعْضُهُم بَعْضًا سُخْرِيًّا ۗ وَرَحْمَتُ رَبِّكَ خَيْرٌ مِّمَّا يَجْمَعُونَ

የአሏህ ገነት ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ናትና ላብ አደርን በዙልም በመዞለም ጀነት ተነፍጎ አሏህ ከሚጻረረን አሏህን ፈርተን የላብ አደሩን ሐቅ መስጠት ትሩፋት አለው። ዲኒል ኢሥላም የሚያስከብረው ላብ አደርን እንጂ የላብ አደር ቀንን አይደለምና ላብ አደርን እናክብር! አምላካችን አሏህ የሰዎችን ሐቅ ከሚጠብቁ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.5K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 15:21:59 ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠጣት ሐላል ሆኗል፦
ዮሐንስ 6፥53-54 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል፡ ደሜም እውነተኛ መጠጥ፡ ነውና።

የክርስቶስ ሥጋ እና ደም ምሳሌአዊ ሳይሆን እውነተኛ መብል እና መጠጥ ነው፥ የጌታ እራት የሚባለው "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም ይለወጣል" የሚል እምነት በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ትምህርት ውስጥ አለ፦
ማቴዎስ 26፥26-28 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።

ካቶሊክ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በኑባሬ ደረጃ ይለወጣል" የሚል ትምህርታቸው "ትራንስ ሰብስታንቴሽን"transubstantiation" ሲባል በኦርቶዶክስ ደግሞ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በተማልሎአዊ ይለወጣል" ሲባል ተማልሎአዊ ለውጥ"mystical change" ነው፥ በሁለቱም እምነት "የበቃ ሰው በከለር፣ በጣዕም፣ በይዘት ተቀይሮ ያየዋል" የሚል እምነት አላቸው። በፕሮቴስታንት ደግሞ "ኅብስቱ ከሥጋው ጋር እንዲሁ ወይኑ ከደሙ ጋር ኅብረት ብቻ አለው እንጂ አይለወጥም" የሚል ትምህርት "ኮን ሰብስታንቴሽን"Consubstantiation" ይባላል።
ይህ ውስብስብ ትምህርት የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠላት ሐላል ነው" የሚል ትምህርት ነው፥ ቅሉ ግን የሰውን ሥጋ መሥዋዕት መሠዋት ሐራም ነው። 1ኛ ነገሥት 13፥1-2 2ኛ ነገሥት 23:20 ዘዳግም 18፥9-12 ተመልከት!  የሰው መሥዋት መሰዋት የዐረማዊ አሕዛብ የሚያደርጉት ርኵሰት ነው።                                                                    

አምላካችን አሏህ የሰውን ልጅ ያከበረው ፍጡር ነው፥ ሐላል ምግብ ከየብስ እና ከባሕር እንዲመገቡት የአደምን ልጆች አሏህ በየብስ እና በባሕር አሳፈራቸው። ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች ከማዕድናት፣ ከዕጽዋት፣ ከእንስሳት በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጣቸው፦
7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ
7፥70 በየብስ እና በባሕር አሳፈርናቸው፥ ከመልካሞች ሲሳዮች ሰጠናቸው፡፡ وَحَمَلْنَاهُمْ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ وَرَزَقْنَاهُم مِّنَ الطَّيِّبَاتِ
7፥70 ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥናቸው፡፡ وَفَضَّلْنَاهُمْ عَلَىٰ كَثِيرٍ مِّمَّنْ خَلَقْنَا تَفْضِيلًا

አምላካችን አሏህ ሰው እርስ በእርስ ሥጋውን እንዲበላላ ሐላል አላደረግም፥ ከዚያ በተቃራኒ የሰው ሥጋ መብላት ሐራም ነው፦
49፥12 ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ! አንደኛችሁ የወንድሙን ሥጋ የሞተ ኾኖ ሊበላው ይወዳልን? መብላቱን ጠላችሁት ሐሜቱንም ጥሉት፡፡ አሏህን ፍሩ! አሏህ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ وَلَا يَغْتَب بَّعْضُكُم بَعْضًا ۚ أَيُحِبُّ أَحَدُكُمْ أَن يَأْكُلَ لَحْمَ أَخِيهِ مَيْتًا فَكَرِهْتُمُوهُ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ تَوَّابٌ رَّحِيمٌ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 106
አነሥ ኢብኑ-ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ወደ ሰማይ በተወሰድኩኝ ጊዜ ከነሐስ የሆነ ጥፍር ኖሯቸው ፊቶቻቸውን እና ደረቶቻቸውን የሚቧጥጡ በሆኑ ሰዎች በኩል አለፍኩ። እኔም፡- "ጂብሪል ሆይ! እነማናቸው እነዚህ? ስለው፥ እርሱም፦ "እነዚህ የሰዎችን ሥጋ የሚበሉ እና ክብራቸውን የሚነኩ ናቸው" አለኝ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لَمَّا عُرِجَ بِي مَرَرْتُ بِقَوْمٍ لَهُمْ أَظْفَارٌ مِنْ نُحَاسٍ يَخْمِشُونَ وُجُوهَهُمْ وَصُدُورَهُمْ فَقُلْتُ مَنْ هَؤُلاَءِ يَا جِبْرِيلُ قَالَ هَؤُلاَءِ الَّذِينَ يَأْكُلُونَ لُحُومَ النَّاسِ وَيَقَعُونَ فِي أَعْرَاضِهِمْ ‏"‏

አምላካችን አሏህ ሡናን ከሚተገብሩ ሙእሚን ያድርገን! አሚን።   

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
10.2K viewsedited  12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 15:21:53 የሰው ሥጋ በባይብል

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ

እስራኤላውያን በሚያጠፉት ጥፋት አምላክ ቅጣቱ የወንዶች ልጆቻቸውን እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ማድረግ ነበር፦
ዘሌዋውያን 26፥29 የወንዶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ፥ የሴቶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ።

"ትበላላችሁ" የሚለው ይሰመርበት! እስራኤላውያንን ጠላቶቻቸው ባስጨነቋቸው እና መከራ ባሳይዋቸው ጊዜ የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ነግሯቸዋል፦
ዘዳግም 28፥53 ጠላቶችህም ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ አምላክህ እግዚአብሔር የሚሰጥህን የሆድህን ፍሬ የወንዶች እና የሴቶች ልጆችህን ሥጋ ትበላለህ።

ለእስራኤላውያን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ የሚያበላው እራሱ አምላክ እንደሆነ ይናገራል፦
ኤርምያስ 19፥9 የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውንም ሥጋ "አበላቸዋለሁ"።

"አበላቸዋለሁ" የሚለው ይሰመርበት! አምላክ የሰውን ሥጋ ለዛውም የገዛ የአብራክ ክፋል ልጅ መብላት ከመፍቀዱ አልፎ ማስበላቱ ምን ዓይነት ቅጣት ይሆን? አስበይው አምላክ በይው እስራኤላውያንን ናቸው። በዚህ ምክንያት አባቶች ልጆቻቸውን ይበላሉ ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፦
ሕዝቅኤል 5፥10 ስለዚህ በመካከልሽ አባቶች ልጆቻቸውን "ይበላሉ" ልጆችም አባቶቻቸውን "ይበላሉ"።

ምቾት ላይ የነበረ ሰው ረሃብ ላይ የምግብ እጦት ስለሚኖር በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል፥ ከመሰሰቱ የተነሳ ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም፦
ዘዳግም 28፥54 በአንተ ዘንድ የተለሳለሰ እና በቅምጥልነት ሁልጊዜ ይኖር የነበረ ሰው በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል።
ዘዳግም 28፥55 በደጆችህ ሁሉ ውስጥ ጠላቶችህ ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ ሌላ ነገር የቀረው የለምና ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም።

የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ ከማጣትም አልፈው ሴት በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ ትቀናለች፦
ዘዳግም 28፥57 በወንድ እና በሴት ልጅዋም፥ በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ፥ በምትወልዳቸውም ልጆች ትቀናለች።

በተግባር ልጅን ቀቅሎ መብላት የተለመደ ነገር ነበር፥ ይህንን ተግባር ኤርሚያስ በሰቆቃ ነግሮናል፦
2ኛ ነገሥት 6፥28-29 ንጉሡም፦ ምን ሆነሻል? አላት፥ እርስዋም፦ ይህች ሴት፦ "ዛሬ እንድንበላው ልጅሽን አምጪ! ነገም ልጄን እንበላለን" አለችኝ። ልጄንም ቀቅለን በላነው፥ በማግሥቱም፦ "እንድንበላው ልጅሽን አምጪ" አልኋት፤ ልጅዋንም ሸሸገችው" ብላ መለሰችለት።
ሰቆ ኤርምያስ 4፥10 ዮድ። የርኅሩኆች ሴቶች እጆች ልጆቻችውን ቀቅለዋል፥ የወገኔ ሴት ልጅ በመቀጥቀጥዋ መብል ሆኑአቸው።
ሰቆ ኤርምያስ 2፥20 ሬስ።አቤቱ፥ እይ፤ በማን ላይ እንደዚህ እንዳደረግህ ተመልከት። በውኑ ሴቶች ፍሬያቸውን፥ ያቀማጠሉአቸውን ሕፃናት ይበላሉን?
7.6K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-01 15:21:21 የሰው ሥጋ በባይብል

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ

እስራኤላውያን በሚያጠፉት ጥፋት አምላክ ቅጣቱ የወንዶች ልጆቻቸውን እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ማድረግ ነበር፦
ዘሌዋውያን 26፥29 የወንዶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ፥ የሴቶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ።

"ትበላላችሁ" የሚለው ይሰመርበት! እስራኤላውያንን ጠላቶቻቸው ባስጨነቋቸው እና መከራ ባሳይዋቸው ጊዜ የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ነግሯቸዋል፦
ዘዳግም 28፥53 ጠላቶችህም ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ አምላክህ እግዚአብሔር የሚሰጥህን የሆድህን ፍሬ የወንዶች እና የሴቶች ልጆችህን ሥጋ ትበላለህ።

ለእስራኤላውያን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ የሚያበላው እራሱ አምላክ እንደሆነ ይናገራል፦
ኤርምያስ 19፥9 የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውንም ሥጋ "አበላቸዋለሁ"።

"አበላቸዋለሁ" የሚለው ይሰመርበት! አምላክ የሰውን ሥጋ ለዛውም የገዛ የአብራክ ክፋል ልጅ መብላት ከመፍቀዱ አልፎ ማስበላቱ ምን ዓይነት ቅጣት ይሆን? አስበይው አምላክ በይው እስራኤላውያንን ናቸው። በዚህ ምክንያት አባቶች ልጆቻቸውን ይበላሉ ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፦
ሕዝቅኤል 5፥10 ስለዚህ በመካከልሽ አባቶች ልጆቻቸውን "ይበላሉ" ልጆችም አባቶቻቸውን "ይበላሉ"።

ምቾት ላይ የነበረ ሰው ረሃብ ላይ የምግብ እጦት ስለሚኖር በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል፥ ከመሰሰቱ የተነሳ ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም፦
ዘዳግም 28፥54 በአንተ ዘንድ የተለሳለሰ እና በቅምጥልነት ሁልጊዜ ይኖር የነበረ ሰው በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል።
ዘዳግም 28፥55 በደጆችህ ሁሉ ውስጥ ጠላቶችህ ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ ሌላ ነገር የቀረው የለምና ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም።

የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ ከማጣትም አልፈው ሴት በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ ትቀናለች፦
ዘዳግም 28፥57 በወንድ እና በሴት ልጅዋም፥ በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ፥ በምትወልዳቸውም ልጆች ትቀናለች።

በተግባር ልጅን ቀቅሎ መብላት የተለመደ ነገር ነበር፥ ይህንን ተግባር ኤርሚያስ በሰቆቃ ነግሮናል፦
2ኛ ነገሥት 6፥28-29 ንጉሡም፦ ምን ሆነሻል? አላት፥ እርስዋም፦ ይህች ሴት፦ "ዛሬ እንድንበላው ልጅሽን አምጪ! ነገም ልጄን እንበላለን" አለችኝ። ልጄንም ቀቅለን በላነው፥ በማግሥቱም፦ "እንድንበላው ልጅሽን አምጪ" አልኋት፤ ልጅዋንም ሸሸገችው" ብላ መለሰችለት።
ሰቆ ኤርምያስ 4፥10 ዮድ። የርኅሩኆች ሴቶች እጆች ልጆቻችውን ቀቅለዋል፥ የወገኔ ሴት ልጅ በመቀጥቀጥዋ መብል ሆኑአቸው።
ሰቆ ኤርምያስ 2፥20 ሬስ።አቤቱ፥ እይ፤ በማን ላይ እንደዚህ እንዳደረግህ ተመልከት። በውኑ ሴቶች ፍሬያቸውን፥ ያቀማጠሉአቸውን ሕፃናት ይበላሉን?

ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠጣት ሐላል ሆኗል፦
ዮሐንስ 6፥53-54 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል፡ ደሜም እውነተኛ መጠጥ፡ ነውና።

የክርስቶስ ሥጋ እና ደም ምሳሌአዊ ሳይሆን እውነተኛ መብል እና መጠጥ ነው፥ የጌታ እራት የሚባለው "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም ይለወጣል" የሚል እምነት በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ትምህርት ውስጥ አለ፦
ማቴዎስ 26፥26-27 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
28: ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።

ካቶሊክ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በኑባሬ ደረጃ ይለወጣል" የሚል ትምህርታቸው "ትራንስ ሰብስታንቴሽን"transubstantiation" ሲባል በኦርቶዶክስ ደግሞ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በተማልሎአዊ ይለወጣል" ሲባል ተማልሎአዊ ለውጥ"mystical change" ነው፥ በሁለቱም እምነት "የበቃ ሰው በከለር፣ በጣዕም፣ በይዘት ተቀይሮ ያየዋል" የሚል እምነት አላቸው። በፕሮቴስታንት ደግሞ "ኅብስቱ ከሥጋው ጋር እንዲሁ ወይኑ ከደሙ ጋር ኅብረት ብቻ አለው እንጂ አይለወጥም" የሚል ትምህርት "ኮን ሰብስታንቴሽን"Consubstantiation" ይባላል።
ይህ ውስብስብ ትምህርት የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠላት ሐላል ነው" የሚል ትምህርት ነው፥ ቅሉ ግን የሰውን ሥጋ መሥዋዕት መሠዋት ሐራም ነው። 1ኛ ነገሥት 13፥1-2 2ኛ ነገሥት 23:20 ዘዳግም 18፥9-12 ተመልከት! የሰው መሥዋት መሰዋት የዐረማዊ አሕዛብ የሚያደርጉት ርኵሰት ነው።

አምላካችን አሏህ የሰውን ልጅ ያከበረው ፍጡር ነው፥ ሐላል ምግብ ከየብስ እና ከባሕር እንዲመገቡት የአደምን ልጆች አሏህ በየብስ እና በባሕር አሳፈራቸው። ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች ከማዕድናት፣ ከዕጽዋት፣ ከእንስሳት በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጣቸው፦
7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ
7፥70 በየብስ እና በባሕር አሳፈርናቸው፥ ከመልካሞች ሲሳዮች ሰጠናቸው፡፡ وَحَمَلْنَاهُمْ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ وَرَزَقْنَاهُم مِّنَ الطَّيِّبَاتِ
7፥70 ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥናቸው፡፡ وَفَضَّلْنَاهُمْ عَلَىٰ كَثِيرٍ مِّمَّنْ خَلَقْنَا تَفْضِيلًا

አምላካችን አሏህ ሰው እርስ በእርስ ሥጋውን እንዲበላላ ሐላል አላደረግም፥ ከዚያ በተቃራኒ የሰው ሥጋ መብላት ሐራም ነው፦
49፥12 ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ! አንደኛችሁ የወንድሙን ሥጋ የሞተ ኾኖ ሊበላው ይወዳልን? መብላቱን ጠላችሁት ሐሜቱንም ጥሉት፡፡ አሏህን ፍሩ! አሏህ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ وَلَا يَغْتَب بَّعْضُكُم بَعْضًا ۚ أَيُحِبُّ أَحَدُكُمْ أَن يَأْكُلَ لَحْمَ أَخِيهِ مَيْتًا فَكَرِهْتُمُوهُ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ تَوَّابٌ رَّحِيمٌ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 106
አነሥ ኢብኑ-ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ወደ ሰማይ በተወሰድኩኝ ጊዜ ከነሐስ የሆነ ጥፍር ኖሯቸው ፊቶቻቸውን እና ደረቶቻቸውን የሚቧጥጡ በሆኑ ሰዎች በኩል አለፍኩ። እኔም፡- "ጂብሪል ሆይ! እነማናቸው እነዚህ? ስለው፥ እርሱም፦ "እነዚህ የሰዎችን ሥጋ የሚበሉ እና ክብራቸውን የሚነኩ ናቸው" አለኝ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لَمَّا عُرِجَ بِي مَرَرْتُ بِقَوْمٍ لَهُمْ أَظْفَارٌ مِنْ نُحَاسٍ
8.2K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 10:42:04
"የስላሴ እሳቤ" እና "የተደበቀው እውነት" መጻሕፍ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ አዳማ እና ደሴ ይገኛሉ።

አዳማ ማግኘት የምትፈልጉ call +251966640370

ደሴ ማግኘት የምትፈልጉ፦
አረብገንዳ ሸህ አብዱ መክተባ
  ሸርፍተራ ፋጡማህ መክተባ 
አሕመድ መክተባ ይገኛል

አዲስ አበባ ደግሞ call 0920781016
12.8K viewsedited  07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 09:21:01
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

ያ ጀመዓህ! "የተደበቀው እውነት" የሚለው ስድስተኛው መጽሐፌ በገበያ ላይ ውሏል። "የተደበቀው እውነት" የሚያውጠነጥነው ስለ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት በተውራት እና በኢንጂል ተነግሮ የመጽሐፉ ሰዎች ይህንን እውነት እንዴት እንደደበቁት የሚገልጥ እና የሚያጋልጥ ነው። ዝርዝሩን መጽሐፉ ላይ ያንብቡ እና ለሎች የሂዳያህ ሠበብ እንዲሆን አስነብቡ!

መጽሐፉን መርካርቶ አንዋር መሥጂድ ኢሥላማዊ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል፥ የበለጠ ለመረጃ +251920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!

መጽሐፉ ተደራሽነት እንዲኖረው ባለው የማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!

ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
14.5K views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ