Get Mystery Box with random crypto!

አቤት የዛሬ ቀን አቤት ይችህ ዕለት ዕለተ አርብ በዓለ ስቅለት ጌታችን አማላካችን ሐሙስ ማታ 3 | ስለ ፅዮን ዝም አንልም

አቤት የዛሬ ቀን አቤት ይችህ ዕለት
ዕለተ አርብ በዓለ ስቅለት

ጌታችን አማላካችን ሐሙስ ማታ 3 ሰዓት በይሁዳ አመልካችነት ስሞ አሳልፎ ሰጠው
ጠዋት 12 ሰዓት የዓለም ቤዛ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክረስቶስ ጲላጦስ ፊት የቆመበት ሰዓት ጲላጦስ በጥያቄ ጌታችን ይጠይቀው ነበር ጌታ ግን ከዝምታ ውጭ ምን አልመለሰም " ወዲያውም ማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎችና ከጻፎች ከሸንጎውም ሁሉ ጋር ከተማከሩ በኋላ፥ ኢየሱስን አሳስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።"
(የማርቆስ ወንጌል 15:1)
ጠዋት ሶስት ሰዓት ጌታችን ጲላጦስ ገረፈው በሰሰለት አስሮ ገረፈው ለአይሁድ አሳልፎ ሰጠው እኔ ከእርሱ ምንም በደል አላገኘሁበትም ዕያለ አሳልፎ ሰጠው አይሁድ እየተሳለቁ 6666ግራፋት ገረፉት ምራቅ ተፉበት በጥፊ ማን መታህ በዱላ መን ገጨኸ እያሉ ተዘባበቱበት
" ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት።"
(የማርቆስ ወንጌል 15:19)

ቀን 6 ሰዓት የዓለም ጌታ በወንጀለኛ መቅጫ ጎለጎታ /የራስ ቅል በተባለ ስፍራ በመስቀል ሰቀሉት ሳዱር አላዶር ዳናት አዴራ ሮዳስ በተባሉ ቀነዋተ መስቀል ቸነከሩት የሾክ አክሊል ደፉበት
" ቀይ ልብስም አለበሱት፥ የእሾህ አክሊልም ጎንጉነው ደፉበት፤"
(የማርቆስ ወንጌል 15:17)

ቀን 9 ሰዓት ጌታችን ነፍሱ ከሥጋው በገዛ ስልጣኑ እና ፍቃዱ የለየበት ሰዓት ነው ሰባቱ የመስቀሉ ቃለት የተናገረበት
" ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 27:45)
ጌታችን በተአምራቱ !እያዩ እንኳን ልባቸው ሊመለስ አልቻለም

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 27)
----------
50፤ ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።

51፤ እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤

52፤ መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤
አንድም ሁለቱ አብረውት የተሰቀሉ የነበሩት ጥጦስና ዳርክስ ወይም
ፊያታዊ ዜማ እና ፊያታዊ ዘፀጋ እየተነጋገሩ ሳለ ጥጦስ እኛስ በወንጀላችን ነው የተሰቀልነው እርሱ ግን ምን አላደረገም አለ ዳርክስም አምላክ ከሆነ እራስህን አድን አለ ፊያታዊ ዜማ ግን አቤቱ በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ አለ ጌታም ሲመልስለት

(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 23)
----------
41፤ ስለ አደረግነውም የሚገባንን እንቀበላለንና በእኛስ እውነተኛ ፍርድ ነው፤ ይህ ግን ምንም ክፋት አላደረገም ብሎ ገሠጸው።

42፤ ኢየሱስንም። ጌታ ሆይ፥ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ አለው።

43፤ ኢየሱስም። እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ አለው።

ሰርክ 11 ሰዓት ጌታችን በአዲስ መቃብር ኒቆዲሞስና አርማታዊ ዮሴፍ ገንዘው ቀበሩት

ቅዳሜ ለሊት 6 ሰዓት ሞትን በሞቱ ሽሮ የተነሳበት ሰዓት
" እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:5)
እንበለ ደዊ ወሕማም እንበለ ጻዕማ ወድካም ያብጽሀኒ ያብጽያክሙ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሠላም
ሰሙነ ሕማማቱ በሠላም አስፈፅሞ ለብርሃን ትንሳኤው ያድርሰን የትንሳኤው ብርሃን ያሳየን

https://t.me/tsiyon1621