Get Mystery Box with random crypto!

ሰላም ዋላችሁ? ብዙዎቻቹ እንደጠየቃችሁኝ የዛሬው ቅዳሴ ይለያል ወይ ላላችሁት ምነው ተለየብኝ ላላ | ፀረ ዝሙት

ሰላም ዋላችሁ?

ብዙዎቻቹ እንደጠየቃችሁኝ የዛሬው ቅዳሴ ይለያል ወይ ላላችሁት ምነው ተለየብኝ ላላችሁት ለመመለስ መጥቻለሁ መልካም ቆይታ።


የዛሬው ቅዳሴ ተለይቶ ሳይሆን በቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሁላችሁም እንደምታውቁት 14 የቅዳሴ አይነት አለ ።


ሁሉም አንድ ሆነው ልዩነትም አላቸው ።


ለምሳሌ ቅዳሴ ሐዋርያት ሐዋርያትን የሚነካ
ቅዳሴ ማርያም ደሞ ማርያምን የሚገልፅ
ቅዳሴ እግዚእ ደሞ የጌታ ቅዳሴ ነው።


እናም ዛሬ መጋቢት 10 በዓል ስለሆነ መስቀልን የሚነካ መሆን አለበት ።


ስለዚህ ስለ መስቀል በብዛት የተረከው ወይም የደረሰው በቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው ስለዚህ ።


የዮሐንስ አፈወርቅን ቅዳሴ ዛሬ ይቀደሳል ማለት ነው። እንጂ ሌላ የተጨመረ ወይም የተቀነሰ አዲስ ነገር የለም።


2 ተኛ ጥያቄያቹ ደሞ የ የ የ ይላሉ ምን ማለት ነው በቅዳሴው ላይ ብላቹህኛል።


ተሳስታቹሀል


የ ሳይሆን ዬ ነው የሚሉት ትርጉሙም ወየው (ወይኔ) እንደማለት ነው።



3 ተኛ ጥያቄያቹ ደሞ ሠራዊቱስ የለያል ወይ ?


አዎ ይለያል የዮሐንስ አፈወርቅ ሰራዊት አለ እሱ ነው የሚባለው።


ስለጠየቃችሁኝ አመሠግናለሁ

ዲ/ን ፍቅረ አብ መለስኩላቹ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ቻናል ውስጥ

ሌላም ጥያቄ ካላቹ በዚህ ጠይቁን


@serate_bte_krstian
@serate_bte_krstian
@serate_bte_krstian