ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የእጅ ኳስ ፌዴሬሽን የዞን አምስት ውድድርን እንድታዘጋጅ ተመረጠች ኢትዮጵያ ከ10 ሃገራት እና ከ350 በላይ ልዑካን ቡድን የሚሳተፉበት በዓለም አቀፍ የእጅ ኳስ ፌዴሬሽን የሚዘጋጀው ዞን አምስት የምስራቅ አፍሪካ እጅ ኳስ ዋንጫ እንድታዘጋጅ መመረጧን የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ገልጿል። የምስራቅ አፍሪካ ዞን አምስት ሃገራት ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ሲሆኑ ውድድሩ ከግንቦት 03 - 11/2016 ዓ.ም ከ18 ዓመት በታች እና ከ20 ዓመት በታች የብሄራዊ ቡድን የሚሳተፉበት የእጅ ኳስ ውድድር መሆኑ ተገልጿል። @TikvahethMagazine 23.0K views17:51