ዋልያው ፈርዖኑን ረቷል ! በኮትዲቫር አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ አራት ላይ በቢንጉ ብሄራዊ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ ግብፅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ ከጨዋታ ብልጫ ጋር 2 - 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል ። የዋልያዎቹን የማሸነፊያ ግቦች ዳዋ ሁቴሳ እና አምበሉ ሽመልስ በቀለ አስቆጥረዋል ። ዋልያዎቹ ከ እ.ኤ.አ 1989 በኋላ በኋላ የግብፅ ብሄራዊ ቡድንን ማሸነፍ ችሏል ። የዛሬው ውጤት ተከትሎ ሀገራችን በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ። @TIKVAH_Sport123 719 views18:07