#↑ከአፈር እስከ ጠፈር↓ ````` (ገጣሚ ብሩክ ቃልኪዳን) በቁንጅናሽ ትምክህት ከጨረቃ ጋራ ~ አትፎካከሪ፣ ከእቅፌ ላይ ወድቀሽ ከኮከብ ንጉስ ጋ ~ በአሳብ አትዳሪ። አንዳንዴ ብንጋጭ እኔ ላንች ሰንኮፍ ~ አንች ለኔ ጌጤ፣ ወደ አጽናፍ አታንጋጭ ሰው ነው ያንች እኩያ ~ ሰው ነው ያንች ቢጤ። እርግጥ እውነት አለሽ አንድ አይነት ነው ግብርሽ ~ ከጨረቃ መሳ፣ ለአንች መዋቢያሽን ደሞ ለጨረቃ ~ ፀሐይን ቢነሳ፤ በደምግባታችሁ ~ መች ትመጻደቁ፣ በውሰት የወዛ ፍግ ነው ተፈጥሯችሁ ~ ቢሸፈንም በእንቁ። ውበት የአፈር ዑደት በስንዝር የዕድሜ አንጓ ~ የሚከሰት ማማር፣ ቁንጅናን ለመግለጽ ውብ ቃላት የሚያምጥ ~ እርባን ቢስ ነው ጦማር። የልህቀቱ ተመን አሀድ ቢገኝለት ~ ሚዛን ላይ ቢሰፈር፣ ቢከብደን ለማመን ይሄ ነው የ ሰው ልኬት ~ ከአፈር እስከ ጠፈር "። ቢያንስ አፈር ነው ልኩ ~ መሬት ላይ የረጋ ~ እንደ አቧራ ብናኝ ፣ ቢገዝፍ ጠፈር አያልፍ ~ ግዛቱን ቢያሰፋ ~ እንደ ህዋ መናኝ። አፈር ትቢያ ጉድፍ ፣ አፈር የገላ እድፍ፣ ሰው የመሆን ግብዓት ~ መዋቅር ነው "አተም"፣ ኑረቱን የሚያውጅ በፈጣሪ ፍቃድ ~ "በትንፋሽ" ማኅተም። ያንችም የኔም ገላ ለትቢያ የታጨ ~ ትቢያ ነው መነሻው፣ የሥጋ ጥርቅም የህላዌ አቅም ከኑረቱ ማግስት ~ መበሰበስ ነው ድርሻው። ነገ በእርጅና ውርጭ ለሚቆረፍደው ~ አታድሊ ለሥጋ፣ የተፈጥሮን ቅኝት ከነፍስ ቁርኝት በአቻነት ሚዛን ላይ ~ ለማስሄድ ካልተጋ፤ ሰብ ሟች ነው ~ ሰብ ጠፊ፣ ግብዝ ግብር ጋልቦሽ ወዙን ያጣ አፍቃሪ ~ ሲቀርብሽ አትግፊ። ሰብ የሸክላ ውጤት በአምሳሉ ለንቁጦ ~ ያበጀው ኤልሻዳይ፣ አፈር የሰው ቁራሽ ~ ለሰው "ትንፋሽ" ጉዳይ። የሚል ነው ስብከቴ፣ አፈር ሁነሽ ሳለ አፈር ስትገፊ ~ ገርሞኝ መመልከቴ። ሌሎች እንዲያውቁ እናካፍል፡ መልካም እንሁን በፍቅር እንኑር። @TIBEBnegni @TIBEBnegni @TIBEBnegni 306 views08:38