Gospel singer : በረከት ተስፋዬ በዓለም ፍቅር እንዳልነደፍ ከሚጠፉት ጋር እንዳልሰለፍ አረማመዴን አቅናውና የራስህ አድርገኝ ቀይረኝና አዝ:- ከሚጠፉት እንዳልሆን ጠብቀኝ ጌታ ሆይ ምህረትህን አብዛልኝ (፪x) አንተ የሌለህበት የዓለም ዝና የዓለም ዕውቀት ኢሄ ሁሉ ከንቱ ነዉ ንፋስን እንደመከተል ነው አዝ:- ከሚጠፉት እንዳልሆን ጠብቀኝ ጌታ ሆይ ምህረትህን አብዛልኝ (፪x) በአንደበቴ እንዳልረክስ ወንድሜንም እንዳልተነኩስ አቤቱ ማስተዋልን ስጠኝ መንፈስ ቅዱስ ና አስተምረኝ አዝ:- ከሚጠፉት እንዳልሆን ጠብቀኝ ጌታ ሆይ ምህረትህን አብዛልኝ (፪x) ዓይኔን ወደ አንተ እንዳቀና መንፈስ ቅዱስ ናልኝና ፈውሰኝ ቀድሰኝ መጠቀሚያ ገንዘብህ አድርገኝ አዝ:- ከሚጠፉት እንዳልሆን ጠብቀኝ ጌታ ሆይ ምህረትህን አብዛልኝ (፪x) 291 views08:07