2022-08-26 21:18:46
ብሒላዊ ምክር
ሐሜት፦ ያለ መሣሪያ ሰዉን መግደል ነዉ።
ማጉረምረም፦ ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነዉ።
ቁጣ ፦ ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሠረት ነዉ።
ብስጭት ፦ የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን
የሚጎዳ መርዝ ከክህት የሚያደርስ የኃጢአት ምንጭ
ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
መዋሸት፦ እዉነተኛ ሰዉ ሳይታዩ የሚጎዱበት ረቂቅ የሰይጣን ጦር ነዉ።
መርገም፦ አቅም ሲያንስ ወደላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነዉ።
መሳደብ፦ህሊናን የሚያቆስል
ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱላ ነዉ።
ዋዛ ፈዛዛ፦በስልት የሚቃኙት
የሥራ ፈቶች በገና ነዉ።
የማይገባ ፦ሣቅ ሐላፊ አግዳሚዉን የሚያጠምዱበት የአመንዝሮች ወጥመድ ነዉ።
መሳለቅ፦በአካል ጉዳተኛ ሰዉ ላይ የሚዘብቱበት የመርገም ስንቁ ወግ ነዉ።
ዘፈን ፦ ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ክፉ ፍላፃ ነዉ።
ድንፉታ፦ የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ ነዉ።
መንፈግ፦ የሚለምነዉን ሰዉ የሚወጉበት የሰስታምች ፍላፃ ነዉ።
በክፉ ማንሾካሾክ፦ ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድለበት የአሳባ ቂዎች ጩቤ ነዉ።
ነገር ማመላለስ፦ የሚዋደዱተን የሚለያዩበት የዲያብሎስ የግብር ልጆች መሣሪያ ነዉ።
ቃልን መለውዋወጥ፦ የዚህን
ከዚያ እያመላለሱ የሚያዉደለድሉበት የነመሰዬ ልደር ልዩ ትቅቅ ነዉ።
የአደራ ገንዘብ መብላት፦ ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የስነፍ ሰዎች መሣሪያቸዉ ነዉ።
በሐሰት መማል፦ ሰዉን ለማዘናጋት ሆን ብለዉ የያዙት የግብዞች ማደሪያ ነዉ።
እስጣለሁ ብሎ መንሳት፦ ደግ ለመባል የተናገሩት የእነልወደስ ባይ መግደያ ነዉ።
ሰዉን ማስነወር፦ ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም
ለማጥፉት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነዉ።
መሳለቅ ፦የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነዉ።
መጠራጠር፦ ወደ ክህደት የሚመራ የከሀዲዮች መንገድ መጥረጊያ ነዉ።
ማሽሟጠጥ፦ ሰዉን የሚደበደቡበት የእነአይዩኝ ባይ
ዱላ ነዉ።
ነገር መለዋወጥ፦ የሐሰተኞች ከተያዙበት ወጥመድ የሚያመልጡበት መንኮራኩር ነዉ።
ምኞት፦ የቁም ህልም ነዉ። ሕልሙም በሐሳብ ተፀንሶ በቅዥት የሚወለድ ነዉ።
ተስፋ፦ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሽጋገር የሚያገለግል ደልድይ ነዉ።
ጠብ፦ እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
ችኮላ፦ የትዕግስት ጣላት የፀፀት አባት ነዉ። ልጁም ወይኔ ይባላል።
ሙከራ፦ የሥራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነዉ።
የጥበብ መጀመሪያ፦ እግዚአብሔርን መፍራት ነዉ።
369 viewsማኢጎ ጉቤ, 18:18