"ባጭር ቀረን" ስንል - እድሜ ላበደሩን ቀርፀው ላሳመሩን ለኩሰው ላበሩን ቺርስ!! ።።።። ፊታችንን ዐይተው እንደተቸገርን - ካይናችን ላወቁ ስለማርያም ብለን እስክንለምናቸው - ቆመው ላልጠበቁ ቺርስ!!! ።።።። ወድቀው ለማይጥሉ -ነግሰው ለሚያነግሱ ነውራችንን ዐይተው ልክ እንደ ድመት ኩስ ፣ ለሚያለባብሱ ብድር አበድረው ፣ ፈጥነው ለሚረሱ ቺርስ!!!! ።።።።።። ላባ ላረጉልን ፣ የመከራ ሸክሙን ቀልደው ላሳቁን ፣ ተጫውተው ላከሙን በቸከ ዘመን ላይ... ስጋ ለበስ ትንግርት -ሆነው ላስደመሙን ቺርስ!!!!! ።።።።።።።።።።። ( Bewketu Seyoum ) 626 views03:30