Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ሙዚቃ በዓለም ጆሮዎች... ድምጻችን በዓለም እየተሰማ ነው። 'ናዕት' አርባ ሺ Subs | ታታ አፍሮ -Tata Afro

የኢትዮጵያ ሙዚቃ በዓለም ጆሮዎች...

ድምጻችን በዓለም እየተሰማ ነው። "ናዕት" አርባ ሺ Subscribers፣ ከ90 ሺህ በላይ መውደዶች እና ከአንደ ሚሊየን በላይ ተመልካቾችን በአስራ ሰባት /17/ሰዓታት ውስጥ ብቻ አግኝቷል። ይኽ የህዝብ ድምጽ የሆነው የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ አዲስ ሙዚቃ ዓለማችን ላይ በዚህን ሰዓት በስፋት እየተደመጡ ካሉ ሙዚቃዎች ውስጥ የሁለተኛ ደረጃነትን የያዘ ሲሆን በዘመናዊ የሙዚቃ ማድመጫ ድረገጽ /You Tube/ ላይ ከእራሱ ከቴዲ አፍሮ በቀር በኢትዮጵያ በዚህ ፍጥነት የተደመጠ ሙዚቃ በፍጹም የለም።

ናዕት /እያመመው ቁ፪/ ሙዚቃ ገና 24 ሰዓት ሳይሞላው በዚህ ፍጥነት በዓለም ደረጃ መዳረስ መቻሉ እጅግ ሊደነቅ የሚገባ ክስተት ነው። የህዝብ ድምጽ ሁሌም ኃያል ነው። ናዕት የኢትዮጵያውያን ድምጽ ነው። እንደ አገር ከገባንበት ማጥ ለመውጣት እንደ ዜጋ ከተረገጥንበት ትቢያ ለመነሳት እንዲህ ያሉ አስገምጋሚ ድምጾች ያሹናል። እንደ ሰማይ ማስገምገም እንደ ነጋሪት ጉሰማ የአምባ ገነኖችን ልብ የሚያሸብር የነፍስ ጩኸት።

✎ #ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/

አሁንም ከፍ ብሎ ይደመጥ

የሚያዜም ይመስላል ሲያጣጥር ተጨንቆ
ውስጡን ሲሰብቅለት ኡ... እያለ ማሲንቆ
ኡ...ኡ...