Get Mystery Box with random crypto!

ሽርፍራፊ ድልድዮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ poemmylove — ሽርፍራፊ ድልድዮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ poemmylove — ሽርፍራፊ ድልድዮች
የሰርጥ አድራሻ: @poemmylove
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 917
የሰርጥ መግለጫ

ማንበብ ና ማወቅ ፋሽን እናድርግ!!❤
ውስጥህ ሲነካ በምን ልትናገረው ወደድክ በግጥም በሙዚቃ በስዕል ነው በዝምታ ስማኝ ዝምታ መልስ እንጂ ጥያቄ ሊሆን አይችልም እና ውስጥህን ሰታስረዳ ጥሩ እንቅልፍ ትተኛለክ ይሄ የሁላችን አፍ ነው የኛ ጥበብ አለም፡፡
ግጥም ፣መፀሀፍት በpdf ለማግኘት ተቀላቀሉን።
ሀሳብ አስተያየት ካሎት 👉👉 @kiyaa124

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-29 23:54:02 አዲስ አመት እየመጣ ነው ኧረ እመጣሁላችሁኮ ነው ደርሻለሁ i miss u meski
90 viewsMeskerem Mekonen , 20:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:13:08 @poemmylove
134 viewsMeskerem Mekonen , 07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 09:56:31
"ሰላም" የሰው ስም ብቻ ሆኖ ይቅር ?

The face of W.a.r ሳልቫዶር ዳሊ በ1940 አካባቢ የሳለው ስዕል ነው። ያን ጊዜ በስፔይን የእርስ በእርስ ጦCነት ተገባድዶ የሁለተኛው የአለም ጦCነት ሊጀመር አከባቢ ነው። በዚህ ጊዜ ነው ዳሊ ስዕሉን የሳለው።

ሰላም የሰው ስም ብቻ ሆኖ ይቅር ? አድካሚ ነው ብቻ... አድካሚ ... አንዳንዴ ተስፋ ማድረግም እኮ ይደክማል።

@poemmylove
@poemmylove
137 viewsMeskerem Mekonen , 06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:51:54
if you could tell your younger writing self one thing , what would it be?

እናንተ ምን ትላላችሁ????

@poemmylove
147 viewsMeskerem Mekonen , edited  17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:20:56 ክፋ ነገር በራሱ ረሀብና ጥማት የተሰቃየ ደግ ነገር ነው፣እናንተም ደግ የምትሆኑት እናንተነታችሁን ስትናፍቁ ብቻ ነው።

@poemmylove
142 viewsMeskerem Mekonen , 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 16:00:27 ላለቀስነው እንባ
እግዜር ምን አጨድን?
ለማይዘሩ አሞሮች ቀለብህ ግን በድን!
ስቀን እናውቃለን
ብለን እስክንተርክ የለቅሶ ቤተኛ
የፍጡራኑን ውል ማን አፍርሶት ይሆን
ተራመድ ባልክበት እግር 'ምታስተኛ?
ላለቀስነው እንባ
ላሟጠጠንነው ወዝ ግን
እንዴት አቤት እንበል
ሸክላ አርገኸን ኑረህ
ማለት ከብዶን ለምን?
#Random
ናታን ኤርሚያስ

Share to your loved ones
ለሚወዷቸው ያጋሩልን
.
@nathanErmias
@nathanErmias
113 viewsNathan, 13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 14:29:35
@poemmylove
142 viewsMeskerem Mekonen , 11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:35:17 #እቱ_ጉንጬን_ሳሚኝ
.
.
ሰርክ ተናፋቂ የአመሻሽ ጨረቃ፣
በኮኮብ መቀነት ተንዠርግጋ ደምቃ።
እንደ ፍቅር አምላክ፤
እንደ ከመት ጣዖት አምራ ተሽሞንሙና፣
'ካማልኩቱ ሰፌድ ህብረ ቀለም ዘግና።
ልክ እንደ መሽቀርቀር እራሷን ብትኩልም
እመኚኝ የኔ ውድ፤
ቅንጣት ነው ውበቷ አንቺን አታክልም።
ፀሃይን አወቅሻት ?፤
አንቺን አታክንም፤
በወል ብርሃኗ በምትፈነጥቀው፣
አንቺን ያየሽ ሁሉ፤
ለገፅሽ ተማርኮ ውብ ፀዳሏን ናቀው።

በመስተፋቅርሽ፤
በመስተዋድድሽ፤
ስቀሽ የሰወርሺው መኖሩን የረሳ፣
አይንሽን ሊሳለም የቀዬው ጎረምሳ።
ከመንገድ ዳር ቆሞ ላንቺ እየማለለ፣
"መዓዛዋ ወይራ ናርዶስ ልጅ ናት" አለ።
አንቺ ናርዶስ ሽቶ፤
አንቺ ውብ መዓዛ፤
ከፃድቃን ፊት ቆሜ ሀጥያቴን ስታጠብ፣
ካባተለኝ እድፍ ስርቅ ከስጋ ጠብ።
እንደሰው ቤተኛ ለፅድቄ ተገኚ፣
ከእግዜር እግር ፈሰሽ ምህረት ለምኚ።
ወትሮም በጥበቡ፤
ሞትና መሰንበት አምላክ ሲያራቅቀው፣
በውድቀቱ በኩል፤
በሔዋኑ በኩል ወንዱን አፀደቀው።

እስቲ ጉንጬን ሳሚኝ፤
ደባብሺኝ ደባብሺኝ ላመል ለነገሩ፣
በቅዱስ ከንፈርሽ፤
ግርጣቴ ሲለዝብ ይግረመው ሀገሩ።

እቱ ጉንጬን ሳሚኝ፤
ለኩሺኝ እንደ ጧፍ፤
መዛሌን ላበርታው ከል ምሽቴን ልርታው፣
የዳበስሺው ሁሉ
አንቺ የሳምሺው ሁሉ
እግዜር ቢመርቀው ቀን ሆነለት ማታው።
ብርሃን ፀዳል ልልበስ፤
ካማልክቱ መሃል እንዳንዱ ልቆጠር፣
"በከንፈርሽ አምላክ"
መኖሬ እልፍ ይሁን መሞት እድሜው ይጠር።

ወትሮ የለመንኩት የማለድኩት ረቢ፣
"ይሁን ይሁን" ብሎ
ብርሃን ሊያጠምቀኝ ልትስሚኝ ስትቀርቢ፣
ደርሶ ያለወትሮው፤
እግሬ እየከዳኝ መንፈሴ ካልነቃ፣
ጣዖታዊ ውበት፤
ልቤን ሊሰወረኝ ማርኮኝ ኖሯል በቃ።

ያዳም ዘር በሙሉ፤
በአስማተ ተፈጥሮ፤
ልቡን እየደቃው አንዳች ሲማርከው፣
የዛን ለት ለካ፤
ካምላኩ አስበልጦ ጣዖት የሚያመልከው።

ልክ ነኝ ጣዖቴ?፤
ጉንጬን የሳምሺኝ ለት፤
ተፈጭሮን ገደፍኳት።
ጨረቃዋን ናኳት ፀሃይ ቅንጣት ሆነች፣
አለም የምንላት፤
'ባሴት በደስታዋ አንቺን መች አከለች።

ልክ ነኝ ጣዖቴ ?፤
ጉንጬን ስትስሚኝ፤
ጥልቅ ማሰላሰል እሩቅ ማሰብ ጠላሁ፣
ጣዖቴ ነሽ ስልሽ፤
ከፈጠረኝ አምላክ ከእግዜሩ ተጣላሁ።
አንቺ መላዕክ ስልሽ፤
አንቺን ጣዖት ስልሽ፤
ግራ ቢገባቸው፤
መላዕክቶች ሁሉ ሸሹ ከኔ ራቁ፤
ላፈቀረሽ ልቤ፤
እግዜርና ሰይጣን ተደበላለቁ።

አየሽ የኔ መላክ፤
በዳይ አባታችን፤
አዳም ለውድቀቱ በሴት ዘር ተማረ፣
ወትሮ ለፍቅር ሲል፤
ወድቆ የተገኘው ግን በሄዋን ነበረ።
ምድረ ተዕባት ሁላ፤
ከስር መሰረቱ ከጥንትም ጀምረን፣
በውል ባናውቀውም ማን እንደመከረን።
አምላክን አስትቶ እውነት አስረስቶ፤
የሴት ልጅ ውበቷ፤
ገዳይ ደም ግባቷ፤
ለግዞት ሊቃኘን ማርኮ ስለረታን፣
ከ"አጥፊ"ያችን ጋራ አብሮ እግዜር ይፍታን።
.
.
.
"አንቺዬ........
አጥፊዬም አይደለሽ፤?
አንቺም እግዜር ይፍታሽ።"


ዓቢይ ( @abiye12 )

Join & share

@sinekal
@sinekal
@sinekal
125 viewsAbiy, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 10:32:36
#ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት ታሪክ ውስጥ እጅግ ትልቅ ስፍራ ያላቸው አንጋፋው እና ስመጥሩ የስፖርት ሳይንስ ባለሞያ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

ፕሮፌሰር ዶ/ር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው የኮተቤ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ (በአሁኑ አጠራር የኮቴቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ) እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በስፖርት ሳይንስ ትምህርት መምህር የነበሩና እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ

√ በአትሌቲክስ ስፖርት ሳይንስ ስፔሻላይዝ ያደረጉ ባለሙያዎችን ያፈሩ፣

√ በስፖርት አስተዳደር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተርነት፣

√ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ልዩ ልዩ አካዳሚያዊ ጽሑፎችን በማዘጋጀት፣

√ በበርካታ ሚዲያዎች ለስፖርት ጠቃሚ ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ በሙያቸው ‹‹አንቱ›› ከተባሉ ምሁራን ጎራ ቀድመው የሚጠሩ ሰው ነበሩ፡፡

ዶክተር በዛብህ ወልዴ በቅርቡ አሜሪካን ሀገር በተካሄደው እና ኢትዮጵያ ውጤታማ በነበረችበት 18ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የልዑካን ቡድኑ አመራር እንደነበሩም ይታወሳል።የቀለም አባትነታቸውም የሚዘነጋ አይደለም።

ስርዐተ ቀብሩ በዛሬው ዕለት ቅዳሜ 21/12/2014 አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ይፈፀማል ከዛ በፊት በ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አሸኛኘት ይደረግላቸዋል።

@poemmylove
202 viewsMeskerem Mekonen , 07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:16:06
(መስከረም መኰንን)
( @kiyaa124 )

አንዳንዴ ፈጣሪ የሚወስደውን አያውቅም ፤ ማርያምን ስንት መሞት የሚገባው ሰው እያለ ቢዘል ቢዘል እኔን ይዝለል ብቻ አላውቅም ሞቱን በህይወቴ መቀየር ብችል እግዚአብሔርን አደርገዋለሁ ቢያንስ ለትንሿ ልጁ ይኖራል ።ፈጣሪ አንተ ከኔ ታውቃለህ አይደል የሚባለው!!

ለራሴ እንዲህ አልኳት መስኪ አላማ ያለሽ ሴት ብትሆኚም ፣ ሺ ጊዜ ጠንካራ ሴት ብትሆኚም ግን ለነገ ብለሽ እንደምታስቢው ዛሬን መልካም ቅን ሆነሽ ኑሪው፣ሰዎች ...ዓለም ብዙ ነገሮች ልብሽን ጥላሸት ቢቀቡትም ፣ ደጋግመው እየሳሙ ቢወጉና ቢያደሙሽም ፣ ልብሽን ቢሰብሩትም ሁሌም ይቅር ባይ ልብን ያዢ።አትጥያቸው ውደጃቸው። አትርሺ ህይወት የቅፅበታት ውልብታ ነው ...አንቺ ደሞ የዚህ ቅፅበት አንድ አካል ነሽ ነገ ለራሱ ያውቃል አንቺ ግን የዛሬ ነሽ አልኳት ምክንያቱም ነገ ምን እንደሚሆን ና እንደምሆን አላውቅም። እባካችሁ የሚቆጫችሁን አታድርጉ ዛሬን ያላችሁበትን ህይወት ኑሩት...ትላንትን ለትላንት ተዉትና ዛሬ ላይ ቁሙ ። ትላንትን እያየ ዛሬ አላማ አለኝ ላሳካ በማለት ራሳችንን አናታል። ስም ከሞት አያድንም። እኛ ሁሌም ውሸት ዓለም ውስጥ ያለን እውነቶች ነንና እውነት እንደሆንን ዛሬን እንኑር!!

R. I. P

መምህሬ መካሪዬ አባቴ ጋሽዬ ፕሮፌሰር ዶ/ር በዛብህ

@poemmylove
@poemmylove
211 viewsMeskerem Mekonen , 06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ