Get Mystery Box with random crypto!

ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)

የቴሌግራም ቻናል አርማ paulosfekadu — ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)
የቴሌግራም ቻናል አርማ paulosfekadu — ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)
የሰርጥ አድራሻ: @paulosfekadu
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.79K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-02-11 22:47:08 “ስለ ቤዝዎት የማስበው ልክ እንደ አቶ ካልቪን ነው። በዚህ ረገድ የአንዲት ጠጉርን ስፋት ያህል ከእርሱ ጋር ልዩነት የለኝም።”

(ጆን ዌስሊ )
715 viewsedited  19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 11:51:36

804 views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 14:55:07 የገላትያ መልእክት እና የሮሜ መልእክት የሚወራረሱበት ነገር አላቸው። ለምሳሌ በሁለቱም መልእክቶች ውስጥ ድነት በእምነት መሆኑ በግልጽ ተተንትኗል። ከሁለቱ መልእክቶች ገላትያ በመጀመሪያ እንደ ተጻፈ ግልጽ ነው። ጉዳዩ አሳሳቢ በመሆኑ ሐዋርያው ጳውሎስ ፈጣን ምላሽ ነው የሰጠው፤ ከሙግቱ ውቅር ይልቅ የምላሹ አስፈላጊነት ይታያል። የሮሜው መልእክት ላይ ግን የሙግቱን ውቅርና ፍሰት አለማድነቅ አይቻልም። አንድ የነገረ መለኮት ሊቅ የሮሜን መልእክት ጥንቅቅ ተደርጎ የተቀረጸ ሐውልት፣ ገላትያን ደግሞ የዚያ ግርድፍ ሞዴል አደርገው ይገልጹታል። (ኤፍ ኤፍ ብሩስን ሳነብ ያገኘሁት ነው።)

እናላችሁ በሁለቱም ቦታዎች አንዱን ቀን ከሌላኛው ቀን ጋር እያስተያዩ የሚያከብሩ ሰዎች ነበሩ። ሐዋርያው ጳውሎስ የገላትያ ሰዎችን፣ “ቀንንና ወርን ዘመንንም ዓመትንም በጥንቃቄ ትጠብቃላችሁ። ምናልባት በከንቱ ለእናንተ ደክሜያለሁ ብዬ እፈራችኋላሁ” ይላቸዋል (4፥10-11)። የሮሜ ሰዎችን ግን፣ “ይህ ሰው አንዱ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፤ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ እያንዳንዱ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ” (14፥5)። በግልጽ እንደሚታየው የሐዋርያው ጳውሎስ ምላሽ አንድ ዐይነት አይደለም። ነገሩ ብቻ ሳይሆን፣ ነገረ ነገሩም የራሱ ድርሻ አለው።የምናየውን ነገር የምናይበት ሁኔታ የምላሻችንን ድምፀት ይወስነዋልና። ገላትያ የክርክርና የተቃውሞ ድምፀት (polemics) ኖሮት፣ ሮሜ ላይ ይህ ያልሆነው ከዚህ ጋር ተያይዞ ይመስለኛል።

https://t.me/PaulosFekadu
1.6K viewsedited  11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 11:54:55 በጥር ወር በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ ቀርቦ የነበረው "የተከዳው እውነት" የተሰኘው መጽሐፍ ግምገማ ሁለተኛው ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል።





--
በፌስቡክ ገጻችን ይከተሉን:- http://facebook.com/hintset
ቴሌግራም ላይ ይከተሉን:- https://t.me/hintset
ዩትዩብ ላይ ሰብስክራይብ ያድርጉ:- http://youtube.com/hintsetube
ድረ ገጻችንን ይጎብኙ:- http://www.hintset.org
1.4K views08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 20:48:30

687 views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-01 14:17:58 በጥር ወር በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ ቀርቦ የነበረው "የተከዳው እውነት" የተሰኘው መጽሐፍ ግምገማ የመጀመሪያ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል።





--
በፌስቡክ ገጻችን ይከተሉን:- http://facebook.com/hintset
ቴሌግራም ላይ ይከተሉን:- https://t.me/hintset
ዩትዩብ ላይ ሰብስክራይብ ያድርጉ:- http://youtube.com/hintsetube
ድረ ገጻችንን ይጎብኙ:- http://www.hintset.org
598 views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 19:19:18

528 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 12:29:34 እናምናለን!

“እርሱ ብቻ የአብ ልጅ በሚሆን፣ ዓለም ሳይፈጠር ከአብ በተወለደ፣ … በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ።”
(የኒቅያ የሃይማኖት መግለጫ፤ 325 ዓ.ም)

“እርሱም ከዘመናት አስቀድሞ ከአብ የተወለደ አምላክ፣ ከእናቱም በሥጋ በዓለም የተወለደ ሰው ነው።”
(የአትናቴዎስ የሃይማኖት መግለጫ፤ 4ኛው ክፍለ ዘመን)

“በአምላክነቱ ከዘመናት በፊት ከአብ በተወለደ፣ በዚህ መጨረሻ ዘመን በሰውነቱ ለእኛና ለድነታችን ከወላዲተ አምላክ ከድንግል ማርያም በተወለደ ...”
(የኬልቄዶን የሃይማኖት መግለጫ፤ 451 ዓ.ም)
. . .

(ማርቲን ሉተርንና ጆን ካልቪንን ጨምሮ የቤተ ክርስቲያን ሓዳስያን በሙሉ እነዚህን የእምነት መግለጫዎች ይቀበላሉ።)

ከቤተ ክርስቲያን የተሓድሶ እንቅስቃሴ በኋላ የወጡትን የእምነት መግለጫዎችንም ማካተት ይቻላል።

“ከዘላለም በፊት ከአብ የተወለደ፣ እውነተኛና ዘላለማዊ አምላክ በሆነ፣ ... ከብፅዕት ድንግል ማኅፀን ውስጥ ከባሕርይዋ የሰውን ሥጋ የነሣ፣ የተጣመረ ...)
(1571 ዓም የአንግሊካን ቤ/ክ 39 አንቀጾች)

“ወልድ ከዘላለም ከአብ የተወለደ ...”
(1643-46 ዓ.ም የዌስትሚኒስተር የእምነት መግለጫ)

“ክርስቶስ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። በሥጋዌ ኢየሱስ ክርስቶስ ... ከድንግል ማርያም ተወለደ ...”
(1925 ዓ.ም ሳውዘርን ባፕቲስት ጉባኤ)

በዚህ ጉዳይ ትክክለኛውን አስተምህሮ ሳይገነዘቡ፣ ልከኛ አማኞችን የሚቃወሙ የክርስትና ጠበቆች መኖራቸው ያሳዝናል። እርግጥ ነው፤ የምናወራው ስለ እግዚአብሔር ስለሆነ በዚህች አእምሮአችን ሁሉን መረዳት አንችልም። እግዚአብሔር ከመታወቅ በላይ ነውና የአእምሮአችንን አቅም ያልፋል። ነገር ግን ክርስትናን ከሐዋርያት ተቀብለው የሰጡን አባቶች ምን ምን እንዳስተማሩ ቢያንስ በአንቀጸ ሃይማኖት (በእምነት መግለጫ) መልኩ ያስቀመጡልንን መቀበል ካልቻልን እምነታችን ሐዋርያዊ እንዳልሆነ አጠራጣሪ አይደለም። አዎን፣ አንዳንዴ ባይገባንም መቀበል ይኖርብናል። I believe in order to understand ወይም faith seeking understanding የተባሉት የክርስቲያናዊ ነገረ መለኮት መርሖች ከዚህ ጋር የሚሄዱ ናቸው። ለመረዳት ማመን ያስፈልጋል። ነገረ ነገሩ ባይገባንም፣ አምነን ለመረዳት መጣር አለብን። ይህን ሳያደርጉ፣ ተንደርድሮ ሌሎችን ሊተቹ መጣር ያሳፍራል።

https://t.me/PaulosFekadu
845 viewsedited  09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 16:45:42 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንዳንድ እውነተኛ ነቢያት የተናገሯቸው ትንቢቶች በፍሬ ነገራቸው ልክ ሆነው፣ በዝርዝር ጉዳያቸው ለትርጉም የተጋለጡ ወይም አሻሚ ሆነው ተገኝተው ያውቃሉ። እስቲ ከሁለቱም ኪዳናት አንዳንድ ምሳሌ እንውሰድ።

Ladies first! ነቢዪት ሕልዳና። ታሪኩ ከይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ ጋር የተያያዘ ነው። ኢዮስያስ በፍጹም ልቡ እግዚአብሔርን ከመከተል ወደ ግራም ወደ ቀኝም ያላለ ጻድቅ ነበረ። ጣዖታትን ከይሁዳ ምድር ጠራርጎ ያስወገደ፣ ቤተ መቅደሱን ያደሰ፣ በማንም ባልተከበረ ሁናቴ ፋሲካን ያከበረ ንጉሥ ነበር። የጠፋው የእግዚአብሔርን ሕግ መጽሐፍ በዚህ ሂደት መካከል ተገኘ። የፍርድ መልእከት ስለ ነበረው ንጉሡ አዝኖ ልብሱን ቀደደ። ከዚያም የእግዚአብሔርን ሐሳብ ለማግኘት ወደ ነቢዪቱ ሕልዳና መልእክተኞቹን ላከ። ነቢዪቱም እግዚአብሔር ሊያደርግ ያለውን ፍርድ ተናገረችና ስለ ንጉሡ ግን፣ “ስለ ሰማኸው ቃል ልብህ ገር ሆኖአልና ... የተናገርሁትን ሰምተህ በእግዚአብሔር ፊት ተዋርደሃልና፣ ልብስህንም ቀድደሃልና በፊቴም አልቅሰሃልና ... ወደ አባቶችህ እሰበስብሃለሁ፤ በሰላምም ወደ መቃብርህ ትሰበሰባለህ፤ በዚህም ስፍራ ላይ የማመጣውን ክፉ ነገር ዐይኖችህ አያዩም” አለችው (2ነገ. 22፥18-20፤ 2ዜና 34፥26-28)።

ከዚህ መልእክት መካከል “በሰላም ወደ መቃብርህ ትሰበሰባለህ” የሚለው ለትርጉም የተጋለጠ ነው። ለምን? ንጉሡ በጦርነት ላይ ተገደለ እንጂ በሰላም አልሞተማ (2ነገ. 23፥28-29፤ 2ዜና 35፥20-24)። ጠቅላላው መልእክት ከተወሰደ ግን ለንጉሡ የተነገረው ትንቢት፣ “በይሁዳ ኀጢአት ምክንያት እግዚአብሔር በሚያመጣው ፍርድ አትሞትም” የሚል ነው። በትክክልም የሆነው ይኸው ነው፤ የእግዚአብሔር ፍርድ የመጣው በንጉሡ ዘመን አልነበረምና። ጠቅላላውን ትንቢት ከዐውዱ ጋር ወስደን ካልተረጎምነውና "በሰላም ወደ መቃብርህ ትሰበሰባለህ" የሚለውን ብቻ ነጥለን ከወሰድነው ግን፣ ትንቢቱ ሐሰት፣ ነቢዪቱም ሐሰተኛ ይመስሉናል። የትራኬውን ዐውድ ስናይ ግን እውነቱ ይህ እንዳልሆነ መገንዘብ አያቅተንም።

2ኛ ዜና 35፥20-22 ያለውን ታሪክ ጨምረን ከወሰድነው ደግሞ፣ ንጉሡ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ባለመረዳት ራሱን ለሞት እንደ ዳረገም ማሰብ እንችላለን። እንዲህ ከሆነ ደግሞ በነቢዪቱ በኩል የመጣው ትንቢት ሁኔታዊ (conditional) ትንቢት ነበር ማለት ነው። በዚህም ሆነ በዚያ ነቢዪቱም ሆነች በእርሷ በኩል የመጣው ትንቢት ትክክለኛነት ጥያቄ ውስጥ መግባት የለበትም!

ሌላኛው ደግሞ ዝነኛው አጋቦስ ነው። አጋቦስ መልእክቱን ያመጣው ለሐዋርያው ጳውሎስ ነው። የጳውሎስን ቀበቶ ወስዶ የገዛ እጅ እግሩን አሰረና የቀበቶውን ባለቤት ማለትም ጳውሎስን “አይሁድ በኢየሩሳሌም ያስሩታል፤ በአሕዛብም እጅ አሳልፈው ይሰጡታል” የሚል ትንቢት ተናገረ። መልእክቱንም የተናገረው፣ “መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ይላል” በማለት ነበር (የሐዋ. 21፥10-11)። አጋቦስ የተመሰከረለት ነቢይ ነው (የሐዋ. 11፥28)።

በርግጥ ጳውሎስ እንደ ትንቢቱ ታስሯል። “አይሁድ አስረው ለአሕዛብ ይሰጡታል” የሚለው ትንቢት ግን አሻሚ ትርጉም ያለው ይመስላል። ምክንያቱም አይሁድ ጳውሎስን አላሰሩትም፤ ቢያንስ በቀጥታ ይህን አላደረጉም። ታዲያ ምንድን ነው የሆነው? አይሁድ ጳውሎስን ሊገድሉት ተሰባስበው ሁከት ሲፈጥሩ፣ የሁከቱን ወሬ የሰማው የሮም ሻለቃ ፈጥኖ ደረሰና ከእጃቸው ነጥቆ በመውሰድ አሰረው (የሐዋ. 21፥27-33)። በዚህ ረገድ ሲታይ ግራ ትንቢቱ ግራ ሊያጋባን ይችላል። በሌላ በኩል ደግሞ ጳውሎስ የታሰረው አይሁድ በፈጠሩት ሁከት ነው። ጳውሎስን አይሁድ ይዘው “እጃቸውን ጫኑበት” ከዚያም “ከመቅደስ እየጎተቱ አወጡትና ሊደበድቡት ጀመሩ”። ታዲያ ይሄ በአይሁድ መታሰር አይደለምን? ወዴትም እንዳይሄድ በቁጥጥራቸው ሥር አውለው ድብደባ ከጀመሩ “አልያዙትም” ማለት እንችላለን? ሮማውያን ያሰሩት በዚያ ምክንያት ነው። ሻለቃው ሊፈታው ሲል አይሁድ ሊገድሉት እያሤሩ መሆኑን በማወቁ ነበር እንደ ታሰረ ወደ ሌላ ቦታ ያስወሰደው (የሐዋ. 23)። ከዚያም በኋላ ምዕራፍ 24ንም ብናነብ ጳውሎስ ታስሮ የቀረው አይሁድን ደስ ለማሰኘት ሲባል ብቻ መሆኑን እናውቃለን (የሐዋ. 24፥27)። እርሱም ሲናገር፣ "የአባቶችን ሥርዐት የሚቃወም አንዳች ሳላደርግ፣ ከኢየሩሳሌም እንደ ታሰርሁ በሮማውያን እጅ አሳልፈው ሰጡኝ" በማለት ነው (የሐዋ. 28፥17)። ሰበቡ እነርሱ ናቸው። ስለዚህ ትንቢቱ ትክክል ነው።

በሁለቱም ትንቢቶች እንዳየነው ትንቢቶቹ በፍሬ ነገራቸውና በጠቅላላው ሲወሰዱ አሻሚነት የሌላቸው ቀጥተኞች ናቸው። ንጉሡ ኢዮስያስ ከእግዚአብሔር ፍርድ ይጠበቃል፤ ሐዋርያው ጳውሎስም ይታሰራል። በሁለቱ መልእክቶች መካከል ያለው አገላለጥ ግን ለትርጉም የተጋለጠ ነው፤ ሊያሻማና ግራ ሊያጋባ ይችላል። ነቢያቱ ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን መልእክት ለማስተላለፍ የተጠቀሙበትን መንገድ፣ እንዲሁም የታሪኩን ዐውድና ፍጻሜ ሳናስተውል አንዳንድ አገላለጦችን በተናጠል እየመዘዝን በራሳችን ግንዛቤ ብቻ ብንተረጉማቸው ኖሮ ነቢያቱን በስሕተት መክሰሳችን አይቀርም ነበር። ለነገሩማ ትንቢቶችን ብቻ ሳይሆን የቅዱሳት መጻሕፍት ምንባቦችንም ስንተረጉም ጥንቃቄ የሚያስፈልገን ለዚህ ነው።

https://t.me/PaulosFekadu
1.4K viewsedited  13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 15:49:37
በሕንጸት የመጽሐፍ ወርኀዊ የመጽሐፍ ግምገማ መርሓ ግብር፣ በጥር ወር ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ በስሜ ታደሰ (መጋቢ) የተጻፈው “የተከዳው እውነት የተሰኘው ነው።

Join the event on Facebook:
https://fb.me/e/2i6G0Cn3H

--
በፌስቡክ ገጻችን ይከተሉን:- http://facebook.com/hintset
ቴሌግራም ላይ ይከተሉን:- https://t.me/hintset
ዩትዩብ ላይ ሰብስክራይብ ያድርጉ:- http://youtube.com/hintsetube
ድረ ገጻችንን ይጎብኙ:- http://www.hintset.org
664 views12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ