Get Mystery Box with random crypto!

"መምህር ምህረተአብ አሰፋ ምን አስተማሩ"

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortoteach — "መምህር ምህረተአብ አሰፋ ምን አስተማሩ"
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortoteach — "መምህር ምህረተአብ አሰፋ ምን አስተማሩ"
የሰርጥ አድራሻ: @ortoteach
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.95K
የሰርጥ መግለጫ

ኑ መልካሙን መልካሙን እናውጋ፣እናውራ

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

3

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-29 10:54:48
የጌታየ እናት ድንግል ማርያም ሆይ ላመሰግንሽ ልቤ ይነሳሳል አንደበቴ ግን ይሰንፋል፤ ህሊናየ በፍቅርሽ ደስታ ተነሳስቷል አፌ ግን ቃል ያንሰዋል።
እናቴ ሆይ፦ ክርስቶስ ምንኛ ወደደን? አዛኝ እናቱን አንቺን ሰጥቶናልና ሃጥያታችን እጅግ ብዙ ቢሆን የአንቺ የፀሎትሽ ሃይልም ብዙ ነው።
በየቀኑ እንበድላለን በየቀኑም ንስሃ እንድንገባ አንቺን በህሊናችን እንመለከታለን። የዚህ አለም ውበት በእጅጉ ይስበናል የአንቺና የልጅሽ ፍቅርም በእጅጉ ይማርከናል፤ ወደ ኃጢአት እናመራለን ወደ አንቺና ወደ ልጅሽም እንመለሳለን። የልጅሽ ምህረቱ ብዙ ነው ያንቺ ፀሎትም ልዩ ነውና እንደጠፋን አንቀርም ፡ እንዳወዳደቃችንም
አንሰበርም፡፡
ድንግል ሆይ ድኩማን መሆናችን እጅግ እንዳደከመሽ አስባለሁ፤ የዘወትር በደላችንም አሰልቺ ነው አንቺና ልጅሽ ግን በእኛ ተስፋ አትቆርጡም፡፡
ድንግል ሆይ፦ ይህ የልጅሽ ፍቅር ከአእምሮ በላይ መሆኑ ድንቅ ነው፤ የአንቺም የእናትነት ፍቅር ብርቱ መሆኑ ልዩ
ነው።
ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ሆይ፦ ስለዚህ እወድሻለሁ ከፍ ከፍም አደርግሻለሁ። ከልጅሽ ጋር ሆነሽ ከእኔ እንዳትለይ አውቃለሁ። ይህም ለልቤ ደስታ ነው፡፡
አሜን ፀጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን አሜን
965 views07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 10:54:48 የኔስ ማኩረፊያዬ!
የእኔስ ማኩረፊያዬ! የኔስ የቁጭት መርዶ መጽናኛዬ ፣ የከባድ ኀዘኔ ጭነትና የጭንቀቴ መክፈያዬ፣ የደስታዬ መፍሰሻ፣ የብስጭቴ ማርከሻ ፣የእልሄ መታገሻ፣ እኔስ ያላንቺ ማን እናት አለኝ??አንቺው ነሽ እንጉርጉሮዬና ዜማዬ!!
እናት ዓለም የስሜ ዐርማ ፣የሕይወት ወዝ፣ የዓይኔ ማማ፣ የማትነፍጊ፣ የማታቅማሚ ፣ረኀቤን የምትራቢ፣ ጥማቴን የምትጠሚ፣ ቁስሌን የምትታመሚ።
የዘመን ቅርስ መክሊቴ!
የጌታዬ እናት እመቤቴ!
የሐዲስ ኪዳን መሠረቴ!
ቸሪቱ፣አዛኝቱ ፣አማላጅቱ ማርያም እወድሻለሁ!!
780 views07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 07:16:22
አብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ
እሳት የሆነ ቅናት
እሳት የሆነ መከፋፈል
እሳት የሆነ ዘረኝነት
እሳት የሆነ ክፋት
እሳት የሆነ የአለም ሀሳብ
እሳት የሆነ የርኩሰት ስራ
እሳት የሆነ የገንዘብ ፍቅር
እሳት የሆነ ጠብ ክርክር
እሳት የሆነ መገዳደል
እሳት የሆነ ባልጀራን መጥላት
እሳት የሆነ የአመፅ እንጀራ መብላት
እሳት የሆነ የወንድም ደም ማፍሰስ
እሳት የሆነ የስጋ ምኞት
እነዚህ ሁሉ ነግሰውብን ፍፁም ከእግዚአብሔር ርቀን በሀጥያት ረክሰን ወደ አዘቅት ወርደን ወድቀናልና
አብሳሪው መልአክ ሆይ በበትረ መስቀልህ እሳቱን አቀዝቅዘው , ለሀገራችን ለኢትዮጵያም ሰላምን ስጣት
ጠላታችን ዲያብሎስን ከእግራችን በታች ጣልልን አሜን
1.0K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 15:21:04 «እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ»

....."በአካል ሦስት ሲሆን በመለኮታዊ ባሕርዩ በአንድነቱ ጸንቶ የሚኖር የብርሃን መገኛ እሱ እግዚአብሔር አብ ለቃል ኪዳንሽ የተሰጠውን ልዩ ክብር ብሩህ አድርጎ ያሳየኝ ዘንድ የቸርነቱ ጸዳለ ብርሃን ዓይነ ልቡናዬን ያብራልኝ። የቃል ኪዳኗ እመቤቴ ሆይ ከእግዚአብሔር በታች በሰማይም በምድርም አንቺ የሁሉ እመቤት ነሽ" ።
[መልክአ ኪዳነ ምሕረት]
849 views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 10:56:19 ሀይማኖትን እንሁን !!!
አንድ ሰው እግዚአብሔርን ቢያመሰግን ክብሩና ሽልማቱ ለራሱ ነው። ባያመሠግን የሚቀርበት ለራሱ ነው። እግዚአብሔርን አይጠቅመውም። ከዓለም በፊት ብቻውን ሲኖር የነበረ አምላክ ነው።
አንድ ሰው በተለያዬ መንገድ በጸሎት፣ በመዝሙር፣ በሰዓታት ፣ በኪዳን፣ በቅዳሴ ...እግዚአብሔርን የሚያመሠግነው ወይም የሚማጸነው የሌለውን ለማግኘት አልያም፣ የተሰጠውን ለማቆየት፣ አልያም ጤናውን ለማግኘት ነው። የሰው ልጅ ሲበዛ ራስ ወዳድ በመሆኑ ሁሉም ቢሟላለት እግዚአብሔርን አያስተውስም። ሁሉ ቢሟላለት የጸሎት መጽሐፍ ይዞ ቤተክርስቲያን አይሄድም ፣ ማይክ ጨብጦ አይሰብክም አይዘምርም።
ሰባኪ ሆኖ ወንጌልን ቢሰብክ፣ ዘማሪ ሆኖ መዝሙርን ቢዘምር ... ከእግዚአብሔር ለመሸለምና ገነትን ለመውረስ ነው። ሁሉም የሰው ልጅ ገነት ቢገባ ኖሮና ቅጣት ባይኖር ማንም ከሀይማኖት ስርዓት ይወጣል።
ቀዳሚው ነገር በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረውን ወንድምና እህቱን እንደ ራሱ አድርጎ የሚወድ ሰው ቢኖር እሱ ፍፁም ነው። ሰውን ወዶ ከሰው የተወለደውን እግዚአብሔርን ይመስላል። ነገር ግን እንዲህ አይነት ሰው በምድር ላይ ቢኖሩም ፤ ጥቂት ናቸው። ብዙዎቻችን ባዶዎች ነን። ላያችን እግዚአብሔር መስሎ ውስጣችን ሳጥናኤል ነው። የህሊናችን ሀሳቦች እንደ ፊታችን በአደባባይ ቢገለጥ በየሰከንዱ ስንት ሰው ገድለን ይሆን?
ፍቅር የሆነችውን የሀይማኖት መንገድ ገና አልጀመርናትም። ያለምንም ልዩነት ሰውን ሁሉ ማክበርና መውደድ ስንጀምር ያኔ ከራስ ወዳድነት ስንወጣ ሀይማኖት ተጀመረ ማለት ነው። ሀይማኖት አእምሮ ውስጥ ነው። መምሰል ሳይሆን መሆን ነው። ደግ መሆን፣ ቅን መሆን፣ እውነተኛ መሆን፣ ታዛዥ መሆን፣ አፍቃሪ መሆን፣ ፈራጅ አለመሆን፣ ሀሜተኛ አለመሆን፣ ንፁህ መሆን ... ሥላሴ የሚወደው ይሄን ነው። እንደ ዚህ ከሆነ ራሱ ሥላሴ ተገልጾ ያነጋግረናል፣ እመቤታችን ተገልጻ ታነጋግረናለች፣ ቅዱሳን መላእክት ይገለጽሉናል፤ ያነጋግሩናል። ያለበለዚያ በወሬ እንደኖርን እያወራን እንሞታለን። እንደ ቸርነቱ ወደ አምላክ እንሄዳለን ። ኢያሱ እስከዚያው
820 views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:44:23
በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ አይውጣ" ኤፌሶን 4፥29/ ታላቁ መጽሐፍ
በርካቶች ከአፋቸው እንደ ሰገራ ቤት የሸተተ ስድብ ያስወጣሉ።
በርካቶች ከአፋቸው እንደ ኮሶ የመረረ ቃል ይተፋሉ።
በርካቶች አጥንት የሚሰብር ቃል ይወረውራሉ።
በርካቶች ህሊና የማይረሳው መርዝ ቃል ይረጫሉ።
ህይወት እንደ ጅረት ነው። ዛሬ ያገኘኸው ሰው፣ ነገ ምናልባት ከአምስት ዓመት ቡሃላ አታገኘውም።
የተናገረው በጎ ወይም መጥፎ ቃል ግን በህሊና መዝገብ ይከዘናል። መርሳትም ይከብዳል።
ሆኖም በበጎ እየመለሱ መኖር የህሊና ሠላም ይሰጣል። አካል ያረጃል። ወደ ሞትም ይደረሳል። በድንገትም ይሞታል። ቢያምንም ባያምንበትም ወደ ዘላለማዊ የልቅሶ ቦታ ሲዖል በመንፈስ ይወረወራል።
የዘራውን የማያጭድ ሰው የለም። መልካም የዘራ መልካሙን ያጭዳል።
በጎ እናስብ ! በጎ እንናገር ! በጎ እንስራ !
977 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:44:23 ልደታ ለማርያም ፩
ከሀና ማህጸን የአዳም ተስፋ ታየች
በኀጢአት የደረቀው የሰው ህይወት በድንግል መወለድ በተስፋ ለመለመ
ጨለማው ዓለም በድንግል መወለድ ብርሃን ሆነ
የሊባኖስ ተራራ በብርሃን ተከበበ
ሊባኖስ የብርሃን መቀነት ታጠቀች
ሊባኖስ በብርሃን አጥር ታጠረች
ኢያቄም የደስታ ካባ ደረበ
ሀና የደስታ አክሊል ደፋች
የብርሃን እናት ድንግል ተወልዳለታለችናችና
የዓለም ሞት በህይወት ተቀየረ
ሰማይ ከሀና ማኅፀን ተወለደች
የሐና ማሕጸን የሰማዯ መውጫ ሆነ
የውርስ ኀጢአት ከድንግል ራቀ
ሰወች ሁሉ በውርስ ኀጢአት በሚወለዱበትን ያለውርስ ኀጢአት ንጹህ ሁና ወላዲተ አምላክ ተወለደች
ከኢያቄም አብራክ ነጭ እንቁ አበራች
ከሀና ማኅጸን ጸአዳ ርግብ ወጣች
የሀና ታሪክ ተቀየረ
ሀና የእግዚአብሔር ወልድ አያቱ ተባለች
ሰማያት ሰለሰማዯ መወለድ ዝማሬ ዘመሩ
ምድር ሰማይን በመሸከሟ እልል አለች
ሰማዯ በምድር ታየች
የአበው ተስፋ መሰረት ተጣለ
አይሁድ አፈሩ
ቤተ ክረርስቲያን የድንግልን መወለድ አበሰረች
በ5485 ዓመተ ዓለም ድንግል ተወለደች
ፀሐይ ሊወጣ ሰማይ ተገኘች
ሰማዯ ከሰው ተወልዳ ፀሐይን ወለደች
እመቤቴ በመወለድሽ የአበው ተስፋ እውን ሆነ።
የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለያችሁ
829 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 14:44:23 #ዛሬ_የናቶች_ቀን_ነው_እንዴ?
የእናቶች ቀን ከ አመት 1ግዜ ብቻ ማሰብ አይከብድም?
ይከብዳል ምክንያቱም እናት ልጇን ስትወድ ወይም ስታከብር ቀን ስለሌላት ነው።
እናት ዛሬም ነገም ከነገ ወዲያም ልትከበር ልትወደድ የምትገባ ፍጡር ነች።
እናት ለልጇ ያላት ፍቅር ዘላለማዊ ነው።
ትላንት ገና ህፃን እያለህ ምላስህ እየተኮላተፈ ቃላቶችን አገጣጥመህ መናገር ሳትጀምር የምትሳሳልህ እናትህ ዛሬም ፍቅሯ ያው ነው አልተለወጠም። ዛሬም አድገህ የራስህን ህይወት ጀምረህ እንኳን እናት ስላንተ ማሰብና መጨነቅ አላቆመችም። አንተ ግን ዛሬ ከአመት አንዴ ፍቅርህን ትገልፅላታለህ
ከአመት አንዴ ፎቶዋን ለጥፈህ እናቴ እወድሻለሁ ትላታለህ ድንቄም መውደድ።
እናትህን ከወደድክ ሁሌም ውደዳት ሳትሰለች በየቀኑ ፍቅርህን ግለፅላት።
በቃላት ሳይሆን በተግባር አሳያት። ፍቅር ቃላት ሳይሆን መሆን ነው።
እናትህ ላንተ ስትል ወጣትነቷን ውበቷን እድሜዋን ገብራለች፣ ስላንተ የደም ላብ አልባለች። ከኢየሱስ ክርስቶስ ቀጥላ ስላንተ ህይወት ስትል ትልቅ ዋጋን የከፈለች እናትህ ናት። በተለይ በችግርና ብድህነት ተሰቃይተው ያሳደጉን እናቶች ስለልጆቻቸው የከፈሉትን ስቃይና መከራ ሁሌም ሊረሳ አይገባም
ስለዚህ አንተም (አንቺም) እሷን ሆነህ ለሷ ያለህን ፍቅር አሳያት።
በቃ ለኔ የእናቶችን ቀን ማክበር ያ ነው።
ፍቅራችንን በቃላት ሳይሆን በተግባር እንግለፅላቸው።
786 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 21:00:32 #ዛሬ_የናቶች_ቀን_ነው_እንዴ?
የእናቶች ቀን ከ አመት 1ግዜ ብቻ ማሰብ አይከብድም?
ይከብዳል ምክንያቱም እናት ልጇን ስትወድ ወይም ስታከብር ቀን ስለሌላት ነው።
እናት ዛሬም ነገም ከነገ ወዲያም ልትከበር ልትወደድ የምትገባ ፍጡር ነች።
እናት ለልጇ ያላት ፍቅር ዘላለማዊ ነው።
ትላንት ገና ህፃን እያለህ ምላስህ እየተኮላተፈ ቃላቶችን አገጣጥመህ መናገር ሳትጀምር የምትሳሳልህ እናትህ ዛሬም ፍቅሯ ያው ነው አልተለወጠም። ዛሬም አድገህ የራስህን ህይወት ጀምረህ እንኳን እናት ስላንተ ማሰብና መጨነቅ አላቆመችም። አንተ ግን ዛሬ ከአመት አንዴ ፍቅርህን ትገልፅላታለህ
ከአመት አንዴ ፎቶዋን ለጥፈህ እናቴ እወድሻለሁ ትላታለህ ድንቄም መውደድ።
እናትህን ከወደድክ ሁሌም ውደዳት ሳትሰለች በየቀኑ ፍቅርህን ግለፅላት።
በቃላት ሳይሆን በተግባር አሳያት። ፍቅር ቃላት ሳይሆን መሆን ነው።
እናትህ ላንተ ስትል ወጣትነቷን ውበቷን እድሜዋን ገብራለች፣ ስላንተ የደም ላብ አልባለች። ከኢየሱስ ክርስቶስ ቀጥላ ስላንተ ህይወት ስትል ትልቅ ዋጋን የከፈለች እናትህ ናት። በተለይ በችግርና ብድህነት ተሰቃይተው ያሳደጉን እናቶች ስለልጆቻቸው የከፈሉትን ስቃይና መከራ ሁሌም ሊረሳ አይገባም
ስለዚህ አንተም (አንቺም) እሷን ሆነህ ለሷ ያለህን ፍቅር አሳያት።
በቃ ለኔ የእናቶችን ቀን ማክበር ያ ነው።
ፍቅራችንን በቃላት ሳይሆን በተግባር እንግለፅላቸው።
1.1K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ