Get Mystery Box with random crypto!

💠ኦርቶዶክሳዊ ህይወት💠

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxy_eywet — 💠ኦርቶዶክሳዊ ህይወት💠
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodoxy_eywet — 💠ኦርቶዶክሳዊ ህይወት💠
የሰርጥ አድራሻ: @orthodoxy_eywet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2
የሰርጥ መግለጫ

ተዋህዶ ሆይ ፣ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ፣ ባላስብሽ ፣ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ።
#Share በማድረግ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ !

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-10-25 14:09:13 ✞ የወይን ጠጅ የማይጠጣ ✞

በእግዚአብሔር ፈት ፃድቃን የነበሩ በትዛዙና በስርዓቱ የሚሄድ ካህኑ ዘካርያስ እና ኤልሳቤጥ የመውለጃ ጊዜአቸው አልፎ አርጅተው የወለዱት ያልወለዱበትን ጊዜአት ከተሰጣቸው ልጅ ትልቅነት አንፃር የረሱ ለእነርሱ ብቻ ሳይሆን ለብዙዎች ደስታ የሆነ የልጃቸውን መወለድ መልአኩ በእግዚአብሔር ፈት ፀሎቱ መሰማቱን ከአስታወቀው በኋላ ስለሚወልደው ልጅ እንዲህ ብሎታል " እርሱ በእግዚአብሔር ፈት ታላቅ ይሆናልና የወይን ጠጅ የሚያሰክርም መጠጥ አይጠጣም ፤ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል " (ሉቃ 1፥15) መጥምቁ ዮሐንስ የወይን ጠጅ አይጠጣም ሲል ምን ማለት እንደ ሆነ ( *ርዕሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን* "ጸያሔ ፍኖት") በተባለው መጽሐፍቸው እንዲህ ገልፀውታል እርዕሴም ከዚሁ የተወሰደ ነው ። ወይን ፦ ማለት ደስታ ማለት ነው ። ዮሐንስ ወይን አይጠጣም ማለት ከምድራዊ ደስታ ተለይቶ በሰማያዊ ደስታ የሚዋኝ የሚቃኝ ነው ማለት ነው ። "ቅዱስ ጎርጎርዮስም" እንዲህ ይለናል ወይን የተባለች ፍቅርናት ዮሐንስ ወይን አይጠጣም ማለት በፍቅረ ዓለም ያልተያዘ ዓለምን የናቀ: ከፍቅረ አለም በአፍአ የሚኖር ሰማያዊ ሰው ምድራዊ መልአክ ማለት ነው ብሎ ተርጉሞልናል። ዮሐንስ የወይን ጠጅ አለመጠጣቱ በአማናዊ ወይን በክርስቶስ ስራ ደስ የሚሰኝ ነውና።"እነሆ የዓለሙን ኃጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ " እንዳለ። ወይን መጠጣትስ ይሉሃል "እነሆ የዓለሙን ኃጢያት የሚያነጻ የክርስቶስ ደም ፤ መብልዕ ይሉሃል እነሆ ስርየትን የሚሰጥ የመድኀኔዓለም የክርስቶስ ስጋ ሲለን ነው ። ቅዱስ ዳዊትም "ወይን ያስተፌስሕ ልበ ሰብእ - ወይን የሰው ልብ ደስ ያሰኛል ቅቤም ፈትን ለማብራት " ሲል ተናግሯል (መዝ 103-15) ይህ ማለት ለገጸ ነፍስ ውበት ልጅነት ፥ ለገጸ ልብ ደስታ በክርስቶስ ስጋና ደም ሲል ነው ። ቅብዕ ያላት ልጅነት በስላሴ ማመን ናት ። የልብ ደስታ ያለው ድኅነትን የሚሰጥ መድኃኒት ኀዘንን የሚሽር የክርስቶስ ደም ነው ። ይህን ላልፈው አልወደድኩም ( "አባ ጊዮርጊስ" እንዲህ ይላል ደግሞ * አማንኬ አክራጦን ዘበአማን ደመ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአልቦ ቱስሐት - በእውነት መቀላቀል የሌለበት እውነተኛ ወይን የክርስቶስ ደም ነው ። አባ ገብረ ኪዳን ድንቅ በሆነ ገለፃቸው ይቀጥሉና የወይን ጠጅ አይጠጣም አው ምክንያቱም ይላሉ "መንፈስ ቅዱስ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ይመላበታልና " የደነቀኝ የወይን ጠጅ እሰከፈለክ ድረስ ብትጠጣ ምትፈልገውን ደስታ አታመጣም ነው ያለ መንፈስ ቅዱስ ። ኤልሳቤጥም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የደስታ ምስጋና ዘምራለች በእውነት ምስጋናችንን እንድንለውጥ ምክንያት የሆነችን ድንግል ማርያም ናት ። መጽሐፍም ሚለው "በኤልሳቤጥ መንፈስ ቅዱስ መላባት" ። ካለ በኋላ ምስጋናን እንዳቀረበች ተናግሯል። መንፈስ ቅዱስ ካልመላብን የተፈለገውን ያክል ብንጠጣ ደስታ አናገኝም ። ዛሬ ዛሬ ሰው ሲደብረው ሲጨንቀው እስቲ እንዲወጣልኝ ድብርቱ እንዲለቀኝ ልጠጣ እያለ በየመጠጥ ቤቱ ሲዞር ይውላል እውነተኛ ደስታ ክርስቶስ ነው ። የደስታ ምንጭ እናቱ እናታች ድንግል ማርያም ናት ። ከዚህ ሌላ ደስታ የለም ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ።

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
15/2/2015 ዲላ ኢትዮጵያ

https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
7.2K views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 07:14:59 + ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? +

ዮሴፍ በግፍ የሸጡት ወንድሞቹን ለሁለተኛ ጊዜ ሲያገኛቸው እንዲህ ሲል ጠየቃቸው ‘የነገራችሁኝ ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? ገና በሕይወት አለን?’ እነርሱ መለሱ ፦ አባታችን ደህና ነው ገና በሕይወት አለ አሉት፡፡ (ዘፍ 43:27)

ዮሴፍ የጠየቀው የአረጋዊውን አባቱን የያዕቆብን ደህንነት ነበር፡፡ እርሱ ወንድማቸው መሆኑን ገና ስላላወቁ ‘አባቴ ደህና ነው?’ በማለት ፈንታ  ‘ሽማግሌው አባታችሁ’ አለው፡፡ እርግጥም ያዕቆብ መቶ ሠላሳ ዓመቱ ነበር፡፡ ዮሴፍ እንደፈራው አልሞተም፡፡ ገና በሕይወት ነበረ፡፡

ይህንን ዮሴፍ ለወንድሞቹ የጠየቀውን ጥያቄ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ጻድቁን አቡነ አረጋዊን ለመጠየቅ በሔደ ጊዜ ዳግም ተናግሮታል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ወደ ደብረ ሃሌሉያ ዳሞ ተራራ በደረሰ ጊዜ ከተራራው ግርጌ ዮሴፍና ማትያስ የተባሉ ሁለት የአቡነ አረጋዊ ደቀ መዛሙርትን አገኘ፡፡

‘ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ’ [ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነውን] ብሎም ጠየቃቸው፡፡ ይህ ንግግሩ መልስ አግኝቶ ሳያበቃ ምስጋና ሆኖ በአቡነ አረጋዊ ማሕሌት ይዜማል፡፡ ሽማግሌው አባታችሁ [አረጋዊ አቡክሙ] የተባለለት ጻድቁ አቡነ ዘሚካኤል አረጋዊ ተብሎ ለመጠራት እንደ ያዕቆብ 130 ዓመታት መቆየት አላስፈለገውም፡፡ ገና በዐሥራ አራት ዓመቱ መንኖ ለብዙዎች መመነን ምክንያት የሆነ በዕድሜው ሳይሆን በቅድስናው አረጋዊ ለመባል የደረሰ ጻድቅ ነበር፡፡

ዛሬም ላይ ሆነን የዮሴፍንና የቅዱስ ያሬድን ጥያቄ ደግመን እንመልስ፡፡  ‘’ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? ገና በሕይወት አለን?’’ ለሚለን ሁሉ መልሳችን ‘አረጋዊው አባታችን [አቡነ አረጋዊ] ደህና ነው፡፡ አሁንም ድረስ በሕይወት አለ ፤ እግዚአብሔር ሰወረው እንጂ አልሞተም፡፡ የሚል ነው፡፡

ጻድቁ አባታችን አረጋዊ ሆይ ዮሴፍ ስለ አባቱ ደህንነት እንደጠየቀ እኛ ስለ አንተ ደህንነት አንጠይቅም፡፡ እግዚአብሔር ያከበረህ ሆይ ባይሆን እኛ ልጆችህ ግን ደህና አይደለንም፡፡ ነፍሳችን ዛሬ በፊትህ የከበረች ትሁንና ልጆችህን በምልጃህ አስበን፡፡   ዮሴፍ ሽማግሌ አባቱን በፈርኦን ፊት እንዳቀረበ እኛም አረጋዊ አባታችንን በእግዚአብሔር ፊት ትማለድልን ዘንድ በጸሎታችን እናቀርብሃለን፡፡

ከዳሞ ተራራ ላይ ሆነህ ከችግር መውጫ ቸግሮአት ሰማይ ሰማዩን ለምታይ ሀገራችን የምልጃህን ገመድ ወርውርላት፡፡ ሊተናኮሏት የተጠመጠሙባትን ዘንዶዎችም ወደ መልካም ዘመን መወጣጫ መሰላሎችዋ አድርግላት፡፡ ካለችበት ውድቀት ወደ ከፍታ መወጣጫ ወደ መልካም መሸጋገሪያ ገመድ ትፈልጋለችና የጸሎት ገመድህን ላክላት::

ያን ጊዜ እንዲህ ትላለች ፦
ገመድ ባማረ ስፍራ ወደቀችልኝ ርስቴም ተዋበችልኝ’ መዝ 16፡6

  ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 14 2013 ዓ.ም.
7.7K views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 08:59:21
+ የተሠጠህን ቁጠር +

ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው:: የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም:: ዕባብ ደግሞ የሰይጣን አንደበት ነበረ::

ሰይጣን እንዲህ አላት :- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት።
ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም:: የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ:: ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ::

ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም:: ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር:: ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቶአት ሔደ:: ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች:: የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች::

ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል

በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን:: ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ:: ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ:: አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ::
ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 9 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
7.6K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 17:25:06ዮሴፍ ከተሾመ በኋላ

ወንድሞቹ የሀገሪቱ ጌታ ዘፍ 42፥30፣33 ብለው ጠርተውታል ፤ ቅዱስ ዳዊትም "ወረሰዮ እግዚአ ለቤቱ ፤ ለቤቱ ጌታ አደረገው ለጥሪቱም ገዥ አደረገው" መዝ 105፥21 ብሎ ዘምሮለታል ። በርስቱ አይደለ በባዕድ ምድር የነገሰው ዮሴፍ ስለ ክርስቶስ ፈንታ ይህን ስልጣን ተቀብሏል እንጅ ስለሌላ አይደለም በውኑ ዳዊትን ያኽል ነቢይ ለቤቱ ገዥ አደረገው በጥሪቱም ሁሉ ላይ ሾመው ብሎ ታሪክ ብቻ እየተናገረ ይመስላቹኋል ? ነገሩ እንዲ አይደለም ! በዮሴፍ በኩል ስለሚያየው ስለ ክርስቶስ ስልጣን ይናገረዋል እንጂ በግብፅ ስለተገኘው ስልጣን ዳዊት የዘመረ አይደለም የግብፅ ሹመት ለዝማሬ የሚያነሳሳ አይደለምና ። ይልቁንም በአባቱ ርስት ያይደለ በስጋ ርስት ጌትነትን ገንዘብ ስለሚያደርገው በለመለኮቱ ያይደለ በስጋ ርስት "ስልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ" ብሎ የሚናገር በሰጋ ዳዊት በክበበ ትስብእት የሚመጣው ክርስቶስ ታይቶት ይዘምራል እንጅ ። ቅዱስ ዳዊት "በቤቱ ሁሉ ላይ ጌታ አደረገው" ያለውን ንዑድ ክቡር የሆነው ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ " ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ሁሉ ላይ የታመነ ነው" ዕብ 3፥5 ብሎ ተርጉሞታል ። ሊቀ ካህናት መባል የተገባው በስጋ መሆኑን ልብ ይሏል ። (ተንከተም)


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
8.4K views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-19 17:12:34 ክርስቶስ በወንጌል ስለ ራሱ ሲጠየቅ (በቀጥታ)
“እግዚአብሔር ነኝ” ብሎ ለምን አልተናገረም?
***
ይህ ትችታዊ ጥያቄ በኒኮላስ ዘኩሳ ድርሳን ውስጥ የቀረበ ነው። አይሁድ "ሰው ስትሆን ራስህም አምላክ ስላደረግህ ትሳደባልህ” ባሉት ጊዜ “አዎን አምላክ ነኝ፤” ለምን አላለም? ይህን ያላለውም አምላክ ባይሆን ነው የሚል ትችት በሙስሊሞች ይቀርባል። ( ዮሐ. 10፥33-38) ኒኮላስ መልስ ሲሰጥ አይሁድ እግዚአብሔር እያሉ የሚጠሩትን ክርስቶስ አባቴ እያለ ይጠራው እንደነበር ወንጌልን በመጥቀስ ያስረዳል። ("የሚያከብረኝ እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው።" ዮሐ. 8፥54) ስለዚህ ክርስቶስ ራሱን “እግዚአብሔር ነኝ፤” ቢል በአይሁድ አረዳድ መሠረት “አብ ነኝ፤” እንደ ማለት ስለሆነ ትክክል አይሆንም ነበር።
ነገር ግን አይሁድ እግዚአብሔር የሚሉትን እርሱ አባቴ በማለት የአብ መለኮታዊ ልጅ በዚህም አምላክ መሆኑን እነርሱ በያዙት የተሳሳተ አረዳድ ሳይሆን በትክክለኛው መንገድ ነግሯቸዋል፤ ክርስቶስ አምላክ የሚባለው የአብ
ልጅ ስለሆነ ነውና። በቁርኣን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን እግዚአብሔር አድርጎ እንዳላስተማረ መነገሩም በጥንቁቆች ዘንድ በዚህ የወንጌል ብርሃናዊ እና ቀጥተኛ
መንገድ ተቃንቶ ሊተረጎም ይገባዋል ይላል - ኒኮላስ። (Hopkins, Nicholas of Cusa’s De Pace Fidei and Cribratio Alkorani: Translation and Analysis, p. 992.)
***
የልቡና ችሎት፣ ገጽ 354።


@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
9.1K views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-18 17:19:46
እናቱ ሔዋንን በሞት ለተነጠቀው ዓለም እናቱን እንደ መለሰለት ለማጠየቅ በዮሐንስ አማካኝነት ለክርስቲያኖች ሁሉ እናት አደረጋት ። ስለ አንዱ ልጇ ስታለቅስ ሳለች በቁጥር ለማይታወቁ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ የሚነሱ ልጆችን ሰጣት ። በመከራ ቀን ያጣናትን እናታችንን በመከራ ቀን ዳግም አገኘናት ። በመጀመሪያዋ አርብ ያጣናትን ሔዋንን በመጀመሪያዋ አርብ አገኘናት ፤ ከዕፀ በለስ ስር አጣናት ከዕፅ መስቀል ስር እንደገና ተረከብናት ። ከዚያ ሰዓት ጀምሮ ያ ደቀ መዝሙር ወደ ቤቱ ወሰዳት ፤ ከዚያ እስከ ዛሬ የድንግል ሁሉ እናት ሆና "ይእቲ ማርያም እምነ" ስትባል ትኖራለች። ( "ሕይወተ ማርያም" ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ )

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ


@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
8.5K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-17 09:53:42

7.7K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-16 09:36:43 ቤተክርስቲያን በዚህ ዓለም ክርስቶስን ጠርታ በስሙ ተሸክማ እስከ ዓለም ፍፃሜ የምትሰደደውን ድንግል ጀመረችው ። በዚህም በመፃሕፍት ሁሉ ስሟ ሲጠራ እመ ሰማዕታት መዋዕያን ፤ ያሸናፈዎች ሰማዕታት እናት እየተባለች ትጠራለች በተለይም በዘመኑ መጨረሻ ሐሳዊ መሲህ ነግሶ ቤተክርስቲያንን ለአርባ ሁሉት ወራት የሚያሳድዳት መሆኑን አስቀድሞ በሄርዶስ ንግስና እመቤታችን ለአርባ ሁለት ወራት በመሰደዷ ነገረን ።
8.2K views06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 16:53:02
በኦርቶዶክሳዊ አስተሳሰብ የበዓላት አከባበር አንድን ያለፈ ሁነት (Event) ከማስታወስ ያለፈ ነው። ይልቁንስ "አለፈ" የተባለውን ሁነት (Event) ወደ ራስ ለማምጣ ፤ ራስንም ከሁነቱ ውስጥ ለማስገባት ነው ። ዜማችንም ደጋግሞ << ዮም ፍስሐ ኮነ - ዛሬ ደስታ ተደረገ >> ይላል እንጂ በኃላፈ ጊዜ ተራኪ ቋንቋ << ትማልም ፍስሐ ኮነ - ያን ጊዜ /ትናንት/ ደስታ ተደረገ አይልም ፤ ኦርቶዶክሳዊ ምስጋና ክብረ በዓል ትማልም የሌለው ምንጊዜም ሕያው ነው ።
( "ማስያስ የኦርቶዶክሳዊ ነገረ መለኮት መቅድም ነጥቦች" ዲያቆን ሚክያስ አስረስ)


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
@orthodoxy_eywet
10.6K views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 07:32:15 አዲስ የንስሐ ዝማሬ "የመዳን ቀን ዛሬ" በዘማሪ ዲ/ን አክሊሉ

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።


218 views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ