Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.88K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-05 09:27:50 መምህራችን ክቡር ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ (Hibret Yeshitila Hibret) ከዛሬ 10 ዓመት በፊት ያጋሩን ጽሑፍ ነው! በየዓመቱ እንደ አዲስ የሚነበብና ባለብዙኅ ምሥጢር ትምህርት በመሆኑ ተደጋግሞ እንዲነበብ አጋርቻለሁ!
በጎ ጾም መልካም ንባብ ያድርግልን!

✮༒✮ #ጾመ_ሐዋርያት ✮༒✮

(በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ)

በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ) የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡
እነዚህ አጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸውእሁድ ሲሆን የሚገቡት ደግሞሰኞ ቀን ነው፡፡

በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡ ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27 ሰኞ ዛሬ ተጅምሯል ፡፡ (ጽሑፉ የተለጠፈበትን ዓመት ያመለክታል ለዘንድሮው ሰኔ 1 ዛሬ ሰኞ) ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡

የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውን ያህል እጽፍ ዘንድብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝ አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋና ይድረሰው! አሜን!

ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾም እንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክ በርካታ ምስክሮች አሉ ስለዚህ ጾሙን እንደ እንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎ ማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለት ያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመን አመጣሽአድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾም መሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡

ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)

በመቀጠል እስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይ የሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብ ሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ
ታሪኩን ማንበብ ወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ›› በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናት ያህል ዘግይቶ እንጂወዲያው አይጀምርም ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታ ጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶ ያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል ይህም በጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂ የፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይ ምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾም እንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱ ምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት የተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋ መንፈስቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ስለጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስት ዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹ በምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊ መልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራ እንመለከታቸዋለን፡፡

①ኛ...‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸ ንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለው የመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣ የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራው መውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድና በኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞመርዓት (ሴት ሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› ሲልሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰት ሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውም እንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂ በሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾም ተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያትኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግን ከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩ ያስረዳል፡፡

በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋ አይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣት ይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋ ግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ከጸጸትና ከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)

②ኛ...‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞ ሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይም መጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም) ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥ እንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱን ማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌው ስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
3.2K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 09:27:41
2.7K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 16:07:42 ☞ አንተ ግን ፍሬ በሌለው ተክል ፣ ቅጠል በሌለውም ዛፍ ፣ ፈሳሽ በሌለው ወንዝ ፣ ውኃ በሌለው ጉድጓድ ፣ የመንግሥት ዘውድ በሌለው ንጉሥ ፣ የጦር መሣሪያ በሌለው ወታደር ፣ ዝናም በሌለው ደመና ፣ ፍሬ በሌለው እሸት ፣ ለምግብ የሚሆን ሀብት በሌለው አባት ፣ ጡቶች በሌላት እናት ፣ ጣሪያ በሌለው ሕንፃ፡ መዝጊያ በሌለው ደጃፍ፡ አክሊል ባልደፋ ሙሽራ ፣ ጌጥ በሌላት ሙሽሪት፣ ልብሰ ተክህኖ በሌለው ካህን ፣ ቁርባን በሌለው መሠዊያ ፣ የመርከብ ሥርዓት በማያውቅ ዋናተኛ ፣ ገንዘብ በሌለው ገበያተኛ ፣ የብረት ጥሩር በሌለው ባለሠረገላ፣ ጦሮች በሌሉት ፈረሰኛ ትመሰላለህ ! በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ? በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ?

Let us look from the beginning at that very tradition, teaching, and faith of the «Orthodox Church» which the Lord gave (εδωκεν), the apostles preached (εκηρυςαν) and the Fathers preserved (εφυλαςαν). Upon this the Church is founded. 【Athanasius of Alexandria (First Letter to Serapion, 28)】

በቃን ማለት አልቻልንበትምና ሥሉስ ቅዱስ ራሱ በቃችሁ ይበለን!

ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ከሀረር መካነ ሥላሴ ካቴድራል
1.1K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 16:07:41 «ተውኔተ ጵጵስና ☞ የጵጵስና ጨዋታ»
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥

የኩላዊት ቤተክርስቲያናችንን ትውፊት [παραδοσις] ትምህርት [διδασκαλια] እና እምነት [πιστις] ከመነሻው ስንመለከት በክርስቶስ የተሠጠ በሐዋርያት የተሰበከና በአበው የተጠበቀ መንገድ ነው። በዚህም ቤተክርስቲያን ተመሠረተች!【ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ】

በቀደመው ዘመንማ የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው!

በክርስትና ማኅተም ያልከበርክ
እንዴት ለጵጵስና ተመረጥክ? 【አባ ጊዮርጊስ】

ዛሬ ግንቦት ፯ ቀን በሃይማኖት የተዋቀረ ፦ የማይናወጥ መሠረት፣ የማይፈርስ ግድግዳ ፣ የማያዘነብል ምሰሶ የተባለ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፳ኛው የኢትዮጵያና የግብፅ ፓትርያርክ በ፬፻፸፬ ዓ.ም. ከሥጋ ድካም ያረፈበትን ቀን ቤተክርስቲያናችን ትዘክራለች። ይህ የምሥጢር ምንጭ የጉባኤ ኒቅያ አፈ ጉባኤ ደገኛው መምህር ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ለ፵፯ ዓመት በፕትርክና ሲቆይ ሢሦውን 【፲፭ ዓመት】በስደት ነበር ያሳለፈው።

ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን ጳጳስ ቅዱስ ፍሬምናጦስን【አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን】የሾመልን ባለውለታችንና በመንበረ ማርቆስ የተቀመጠ ፳ኛው ፓትርያርካችን ነው። («ወማርቆስ ወንጌላዊ ‘ወኮነ ሰባኬ ወመጥምቀ ወሠያሜ ካህናት’ በእስክንድርያ ወግብፅ ወኖባ ወምድረ ኢትዮጵያ እስከ ጽንፋ» እንዲል መጽሐፈ ግጽው ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፩ )

ቅዱስ አትናቴዎስ ወደ ክርስትናው የመጣበትና ለጵጵስና የበቃበት መንገድ እጅጉን የሚደንቅና አስተማሪ ነው። ስንክሳራችን በቀደመ ሕይወቱ ከአረማውያን ቤተሰብ የተገኘ አረማዊ እንደነበርና ለመጠራቱ ምክንያት ስለሆነች «የጵጵስና ጨዋታ» እንዲህ እያለ ይነግረናል

ውእቱ ይነብር ምስለ ሕፃናት እለ ይትሜህሩ ኀበ መምህር ርእዮሙ ለእሙንቱ ውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይገብሩ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወይትዋነዩ በበይናቲሆሙ ወይረስዩ እምኔሆሙ ዲያቆናተ ወኤጲስ ቆጶሳተ አደሞ ተላህዮቶሙ። ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ወይቤሎሙ ውእቱ አነ እከውን ክርስቲያናዌ ወተፈሥሑ ቦቱ።

【 እርሱም ከመምህር ከሚማሩ ሕፃናት ጋራ እያለ እርስ በርሳቸው በመጫወት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ ከእነርሱ ውስጥ ዲያቆናትን ኤጲስ ቆጶሳትንም ሲያደርጉ እሊያን የክርስቲ ያንን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእሳቸው ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት እርሱም ክርስቲያን እሆናለሁ አላቸው እነርሱም ደስ ተሰኙበት።】

ወነሥእዎ አሜሃ ወረሰይዎ አምሳለ ሊቀ ጳጳሳት ወመትሕቲሁ አምሳለ መንበር። ወእኀዙ ይስግዱ ሎቱ ወበውእቱ ጊዜ ኀለፈ አባ እለእስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት። ወሶበ ርእዮሙ ለውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይትዋነዩ ይቤሎሙ ለእለ ሀለዉ ምስሌሁ ወለዎ ለዝንቱ ሕፃን ይሠየም ሢመተ ክብርተ ወልዕልተ።
【ያን ጊዜም ወስደው በሊቀ ጳጳሳት አምሳል አደረጉት ከበታቹም ወንበር አድርገው ይሰግዱለት ጀመር። በዚያን ጊዜም ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ በዚያ አለፈ የክርስቲያን ልጆች ሲጫወቱ በአያቸው ጊዜ አብረውት ላሉ ይህ ሕፃን ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች ሹመትን ይሾም ዘንድ አለው አላቸው።】

ወንድማለም እንግዲህ ስማ መሾም ስለምትፈልግ ብቻ አትሾምም! እንኳን ሢመቱ ጭውውቱም ቢሆን ሥርዓት አለው። እንዳየኸው ጥንቱን የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው! መጽሐፉም ቢሆን እንኳን ራስህን በቦታው ልታስቀምጥ በቦታው ተቀመጥ እንኳ ቢሉህ እምቢኝ በል ነው የሚል።
【"ኢመፍትው ለመኑሂ እምሰብእ ይምሥጥ ሢመተ ክህነት ለርእሱ አላ ለእመ ተውህበ እምእግዚአብሔር ☞ #የክህነትን_ሹመት ከእግዚአብሔር ካልተሠጠው በቀር ከሰው ወገን ማንም ለራሱ ይገባኛል ብሎ ቀምቶ እጅ አያድርጋት" መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ ፩፥፷፩】

ዛሬ የሕጻናቱን ያኽል ድፍረት አጥተን መሰል እምነት የሌለው ኢጥሙቅ ልብሰ ጵጵስና ለብሶ ሲተውን አይተን ዝም ከማለት አለፍንና በበር ያልገቡ «መስኮተኞች» አይደለም ጵጵስናው ፕትርክናውም ሳይቀር ይገባናል ሲሉ እየሰማን «ሃይ–ባይ» አለመገኘቱ በእጅጉ ያሳዝናል። «ኧረ ተዉ» የሚል መገስጽ ብቅ ሲል ተቆጪውን መቆጣት ከመንገድ ማጥፋት ሥራችን ሆኖ አረፍነው።

ኧረ ጉድ የዚያ ዘመን የእስክንድርያ ሕጻናት እንዴት አድርገው እንደሚበልጡን እዩልኝማ

«ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ☞ #እሊያን_የክርስቲያን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእነርሱ ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት »

እንዲህ ያለውን ጨዋታ ወዳጅ ፡ አልፎ ሂያጅ «ና ግባና ጰጵስ» ለሚሉ ድንበር አፍራሾች እንዲህ ባለው የሌባ መንገድ እንዳልመጣ የምናውቀው ራሱ ቅዱስ አትናቴዎስ በድርሳኑ "ንሕነሰ ኢንኌልቆ ምስለ ክርስቲያን አላ ምስለ አረሚ ወዐላውያን ☞ እኛ ግን እንዲህ ያለውን ከማያምኑና ከሚያምጹት እንጂ ከክርስቲያን ወገን እንኳ አንቆጥረውም!” እያለ ይዘልፋል 【ሃይ አበው ፳፱፥፲፭】

አባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታና የእግዚአብሔር ምርጫ የሆነውን ሹመት በራሱ ጳጳስ ነኝ ይገባኛል ለሚል ንሥጥሮሳዊ በላከው ተግሳጽ ይህን ይላል ፦

እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ?
ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና
እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ?
ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ
【በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ፡ በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ ?】
【መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፮】

«ወአንተሰ ተመሰልከ ተክለ ዘእንበለ ፍሬ: ወዖመ ዘእንበለ ቈጽል: ፈለገ ዘእንበለ ውሒዝ : ወዐዘቅተ ዘእንበለ ማይ፡ ንጉሠ ዘእንበለ ጌራ መንግሥት : ሐራዌ ዘእንበለ ንዋየ ሐቅል : ደመና ዘእንበለ ዝናም : ወሰዊተ ዘእንበለ መስበልት : አበ ዘእንበለ ሀብተ ሲሳይ : ወእመ ዘእንበለ አጥባት : ንድቀ ዘእንበለ ተድባብ : ወኆኅተ ዘእንበለ ማዕፆ : መርዓዌ ዘእንበለ አክሊል : ወመርዓተ ዘእንበለ ባዝግና : ካህነ ዘእንበለ ኤፉድ : ምሥዋዐ ዘእንበለ ቊርባን : ኖትያዌ ዘእንበለ ሥርዐተ ሐመር : ወምሥያጣዌ ዘእንበለ ንዋይ : ሠረገላዌ ዘእንበለ ድርዐ ሐጺን : ወፈረሳዌ ዘእንበለ ኲያንው! እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ? ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና ፣ እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ? ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ »
1.0K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 16:05:45
1.0K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 10:38:26
https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
1.6K viewsDrshaye Akele, 07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 10:37:38 #መፆር_እምዕፀወ_ሊባኖስ (የሊባኖስ እንጨቶች ዙፋን ) ቅድስት ድንግል ማርያም!

በወንጌል "ዕፅ ሰናይ ፍሬ ሰናየ ይፈሪ" (ማቴ ፯፥፲፯) እንዳለው ከመልካም ዛፍ ቤተሰብ የተኘች ምግባረ መልካም ደምግባተ ቀና፣ የሊባኖሷ ብላቴና አማናዊት መፆር (ዙፋን) እግዝእትነ ማርያም ናት! እርሷ ፆረቶ በከርሳ ፣ፆረቶ ዲበ ዘባና ፆረቶ ዘኢይፀወር እያሉ ሊቃውንቱ የሚያወድሷት ለአምጻኤ ዓለማት መፆሩ ፣ ለመጋቤ ዓለማት አገሩ ፣ ለአኅላፌ ዓለማት መንበሩ ናት!

♧ በሰቆቃ ወድንግል "አብርሂ አብርሂ ናዝሬት ሀገሩ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መፆሩ። … ናዝሬት ሀገሩ አብሪ አብሪ ከዙፋኑ ማርያም ጋር ንጉስሽ ወዳንቺ ደርሷልና" ተብላለች፤

♧ በሰአታቱ ገነይነ ለኪ እና ኵሎሙ ዘእግዝእትነ ምስጋናው አፈ ሊቃውንት አባ ጊዮርጊስ
♢ "ሐዳስ መቅደስ መፆረ ንጉሥ። ወላዲቱ ለኢየሱስ።… አዲሲቷ መቅደስ የንጉስ ዙፋኑ ለኢየሱስ ወላዲቱ " ብሏታል፤
♢ "አንቲ ውእቱ ለንጉሠ ነገሥት መፆሩ ለአዳም ተድላ መንበሩ ብኪ ተመይጠ ኅበ ዘቀዳሚ ማኅደሩ።… ለነገሥታቱ ንጉሥ ዙፋኑ ፣ ለአዳም ወደቀደመ ማደሪያው መመለሻ የደስታው ማረፊያ አንቺ ነሽ" ሲል ይገልጣታል፤

♧ የተአምረ ማርያማችን መቅድም "አልቦ ዘፆረ እሳተ ወአልቦ ዘኢገብረ ኅጢአተ እንበለ እግዝእትነ ማርያም። … ከእመቤታችን በቀር ኀጢአትን ያልሠራ ለእሳት ዙፋን የሆነ የለም " ይለናል

♧ ውዳሴ ማርያም ከአንቀጸ ብርሃንና ከቅዳሴው ጋር በምስጢር እየተሳሰረ "ማዕጠንት ዘወርቅ እንተ ፆርኪ ፍሕመ እሳት … የእሳተ መለኮት ዙፋን የወርቅ ማዕጠንት" ይላታል።

♧ የመልክአ ቁርባን ምስጋናም "ናዛዝትነ እምኃዘን ወኃይለ ውርዙትነ እምርስዓን በማኅፀንኪ ተፀውረ ብሉየ መዋዕል ሕፃን።… ከሃዘን የምታረጋጋ መጽናኛችነን፣ ከድካም የምታበረታን የወጣትነት ኃይላችን ፣ ዘመኑ ጥንት የሆነው ሕፃን ማኅፀንሽን ዙፋን አድርጎ አደረ" እንላታለን።

#መፆረ_ገብረ_ለርእሱ (ለራሱ ዙፋን ሰራ)

ይህንን በመሰለው ምሥጢር ውስጥ የተገለጡ ሁለት ፍሬ ነገሮችን እንመርምር

፩ ለራሱ ዙፋኑን የሠራት ራሱ ነው!

ይችን ወላዲተ ቃል መሠረተ ንጽሕ ድንግል
በዚህም በአባት ዘር ከሚመጣ ቁራኝነት በእናት ደም ከሚያርፍ የመርገም ጽነት ለይቶ እኩያት ፍትወታት ኀጣውእ ሳይደርሱባት ራሱ ሠራት ቅዱስ ያሬድ "ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ፀዓዳ … ማርያምስ በአዳም ገላ ውስጥ እንደ ነጭ እንቁ ታበራ ነበር " እንዳላት
ቅድስናዋ የመመረጥ አንድም እንድትመረጥ ሆና በተገባ ለመገኘት ጽናት ያለበት ነውና! ሊቁ "አቀባ መንፈስ ቅዱስ እምከርሰ እማ" ያለውን እንዲህ አብራርቶታል "የበጎ ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ የሚሆን እግዚአብሔር ብዙ ስጦታ ከብዞች መናፍስት የሚቀዳ አይደለም ካንድ መንፈስ ነው እንጂ የክፉ ዕድል ፈንታ ግን የሚገኝ ከሰይጣን ነው፡ እንዳትበድል ድንግልን ከናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ እንዳትረክስም ያነጻት ለወልድ ዋህድም ማደሪያ ያደረጋት እርሱ ነው፡፡ አብ ወደዳት ወልድ ከርሷ ሥጋ ለበሰ መንፈስ ቅዱስ ጋረዳት፡፡ "

፪ ራሱ የሠራት ለራሱ ዙፋንነት ነው!

ይኽችን የንጉሥ ዙፋን የአብ ሙሽራ (መርዓቱ) ፣ የወልድ እናት (ወላዲቱ)፣ የመንፈስ ቅዱስ እልፍኝ (ጽርሐ ቤቱ) ከሰማይ ከወረደ ቃል በቀር ሌላ አድሮባል እንዳያሰኝ "ወትረ ድንግል ማርያም" ብለን እንድናምን እና ድንግሊቱ "ብቻ መውለድን ቀምሶ አቀመሰኝ" እንዳለች ከእርሱ ውጪ ሌላ ልጅ እንደሌላት "እምድኅረ ወለደት ኪያሁ ነበረት በድንግልና" ብለን እንድንመሰክር ዙፋኑን ለራሱ ሠራ ይላል።

ሁለቱ የሊባኖስ እፀው ቅድስት ሀናና ቅዱስ ኢያቄም መሰላቸውን ሳይተኩ በመቆየታቸው ያዘኑት ሐዘን ማንም የማይተካትን የዓለም ሁሉ መክበሪያ አስገኘ! ይህስ ሐዘን የፍጥረት ሁሉ ሐዘን ነበር ዳግሚት ሰማይ ዳግሚት ምድር በመውለድ ደስታቸውን ወደ መካፈል አሳደጉን ከዚቁ ይህን ብለን የዛሬውን በዛሬ እንቋጭ፦

" አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ
ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ
ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ
ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ
ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ
ምስራቀ ምስራቃት ሙፃዕ ፀሐይ
እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ "
አረጋውያኑ ― በእጅጉ ቢያለቅሱ፣
በደል በምታርቅ ― በሴት ልጅ ተካሱ፤
ለወንጌልም ልጆች ― መሸሻቸው ካለም ፣
ሰማይን ወለዱ ― ሃናና ኢያቄም ፣
ሰማይዋም (ሰማዯም) ፀሐይን ― አውጥታለች ለዓለም፤
የምሥራቃት ምሥራቅ ― መውጫዋ ለፀሐይ ፣
የፍጥረት እመቤት ― የመናዋ ሙዳይ ፣
ዛሬ ተወለደች ― ዳግማዊቷ ሰማይ ።

⊙✧⇥ ይቆየን !

ከቴዎድሮስ በለጠ ( ክፍለሥላሴ)
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓፦ ግንቦት ፩ ቀን ፳፻፲ ዓ·ም ከደብረ እንቊ ልደታ ለማርያም
1.5K viewsDrshaye Akele, 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 04:56:21

++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?!  እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ኝ የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦  አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
2.3K viewsDrshaye Akele, 01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 21:58:40
+++ ጣዖት ምንድን ነው? +++ [እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?] «ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ) የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት…
781 viewsDrshaye Akele, edited  18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 21:58:11 +++ ጣዖት ምንድን ነው? +++
[እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?]

«ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ)

የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት ማለት ከዕንጨትና ከቀለጡ ማዕድናት የተሠራ፣ የማምለኪያ ምስል...» እያለ ይተረጒምና ምእመናን ከጣዖት መራቅ እንዳለባቸው ገልጦ «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» በማለት ደምድሞ አስቀምጦታል።

ይህች ዓለም ጣዖትን ያመለኩ በርካታ ነጋሽ እና አንጋሾችን አፍርታለች። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክም ይሁን በገድላትና በድርሳናት እንደምናነበው «ሃይማኖታችሁን ካዱ፥ ለጣዖት ስገዱ» በማለት እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ደጋግ አባቶችን ሲያሳርዱ የነበሩ ክፉ ጣዖታሞች ነበሩ። አሉ። ለወደፊቱም ይኖራሉ።

እነዚህ ልበ ደንዳኖች ምስል ቀርጸው፣ ጣዖት አቊመው፣ ዕጣን አጢሰው፣ ለምስሉ ሲሰግዱና ሲያሰግዱ በመኖራቸው እንደ ክፋታቸው መጠን በየጊዜው ዋጋቸውን አግኝተዋል። ለወደፊት እነሣለሁ የሚሉም ዋጋቸውን ያገኛሉ።

ጣዖት የምንለው የተቀረጸ ምስል ብቻ አይደለም። እግዚአብሔር የማይከብርበት ከንቱ ሥራ ሁሉ ጣዖት ነው። አንዲት ሴት መልክና ደም ግባቷን በመስታውት እያዬች ዘወትር የምትኮፈስ ከሆነ መልኳ ደምግባቷ ለእሷ ጣዖት ሆኖባታል። አንድ ሰው የዝሙት ልምድ ካለውና ያንን ክፉ ሥራ መልቀቅ ካልሻተ ዝሙቱ ጣዖት ነው። «ወዘመዉ በጣዖቶሙ» እንዲል (መዝ ፻፮፥፴፰)

ወዳጄ በየቤቱ ብዙ ጣዖት ያቆመ አለ። ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚበልጥበት ራሱ ያቋቋመው ቀኖና ጣዖት ሆኖበት የሚያስቸግረው ስንቱ ነው? ጫቱ፣ ሲጋራው፣ መጠጡ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው? ዝሙቱ፣ መዳራቱ፣ ውንብድናው፣ ፍቅረ ነዋዩ፣ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው?

ለዚህ አይደል ሐዋርያው «የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፩) ብሎ የዘጋው። ቅዱስ ጳውሎስ አድበስብሶ አላለፈም። ይልቊንም «ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፬) ሲል ቊርጥ ያለ ቃል አስቀምጧል። ወልደ ነጐድጓድ ዮሐንስም በመልእክቱ «ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።» ሲል ያስጠነቅቃል። (፩ኛ ዮሐ ፭፥፳፩)

ከዚህ አንጻር እግር ኳስ ጣዖት ነው አይደለም ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ ምን ያሕል ሞኝ መሆኑን እንመን። ወዳጄ አንተነትህን ለማያውቅህ ለአውሮጳ ኳስ ተጫዋች ጨርቅህን ጥለህ ስታብድለት እየዋልህ ጣዖትነቱን እንዴት ዘነጋኸው? በቴሌቪዥን ስክሪን አፍጥጠህ ስታይ እያመሸህና አጋንንት እንደተቆጣጠረው ድውይ ልብህ እስኪወልቅ ስትጮህ እያደርህ ጣዖት መሆኑ እንዴት ተረሳህ?

ልብ በል እንጅ! «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ [ባዕድ] ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» ተባልህ'ኮ። ደግሞስ የኳስ ጥቅሙ ምንድን ነው? የሚረባህንና የሚጠቅምህን ሳትይዝ ስለ አውሮጳ እግር ኳስ ልብህ እስኪወልቅ መደገፍ ምን ይሉታል?

አንተ ከድጋፍ (በሌላው ከመደ'ገፍ) ሳትወጣ የአውርጳን ኳስ ትደግፋለህ አይደል? አንተ ከሰው ጫንቃ ሳትወር የሌላው ደጋፊ መሆንህ አይገርምም? እስኪ ወደራሳችን እንመለስ? ሀገር እንዲህ በሰላም እጦት ተወጥራ ከኳስ ጋር ልናብድ ይገባል? መንፈሳውያን ነን የሚሉ ሰዎች ብሰው ሳይ አዝናለሁ።

«ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፫)

ቀሲስ ጌትነት ዐይተነው (ክንፈ ገብርኤል)
ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም
815 viewsDrshaye Akele, 18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ