Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.75K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-09 18:29:26
. #የአዳም_ሐሙሱ
▭▭◎⃝◎⃝◎⃝ ◎⃝◎⃝◎⃝◎▭▭

ባምስት ቀን ተኩል ፡ በተስፋ ለመዳን
በቃል የተሠጠች ፡ የቃል እናት ኪዳን
«ከልጅ ልጅህ» ተብላ ፡ ወርዶ ሊያቆም ርደት
የአዳም ሐሙሱ ፡ ማርያም የኛ ልደት!

✧ እምድኅረ ሐሙስ መዋዕል ወመንፈቀ መዓልት እምሕረከ ወእሰሃለከ በብዝሐ ሳህልየ ወምሕረትየ ወእወርድ ውስተ ቤትከ ወአሐድር ውስተ ከርስከ በእንቲአየ ☞ ከአምስት ቀን እና ከግማሽ ቀን በኋላ እምርሐለሁ ይቅርታም አደርግልሃለሁ በይቅርታዬ ብዛትና በምሕረቴ ብዛት ወደአንተ ቤት እወርዳለሁ ስለአንተም ድኅነት በወገንህ ማሕጸን አድራለሁ
[መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ፫፥፲፱]
7.0K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-05 17:44:20 የትንሳኤ መዝሙሮች ስብስብ







7.5K viewsDrshaye Akele, 14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-05 12:01:57
የበዙቱ የቀደመ መነሻውን ከግሪኩ ተውሰው ሰላምታውንም በሰጣዊ ተሰጣዊ (ሰጪና ተቀባይ) ቃል ልውውጥ ይከውኑታል እንዲህ ሲሉ

#ሰጣዊ ☞ ክሪስቶስ አኔስቲ Χριστός ἀνέστη! Christ is Risen! ✧ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን

#ተሰጣዊ ☜ አሊቶስ አኔስቲ "Ἀληθῶς ἀνέστη! " - "Truly He is Risen!" or "He Has Risen Indeed!" ✧ (አሜን) በአማን ተንሥአ

በአረማይኩ ግን ጥቂት የተሰጣዊ ምላሽ ልዩነት ያለው ሆኖ ይነገራል

☞ ክሪስቶስ ሃሪያቭ ኢ ሜሬሎዝ Քրիստոս հարյա՜վ ի մեռելոց: Christ is risen! ክርስቶስ ተንስሥኣ እሙታን

☜  ኦርኺያል ኤ ኻሮውቲዮን ክሪስቶስ Օրհնյա՜լ է Հարությունը Քրիստոսի: Blessed is the resurrection of Christ!" ቡሩክ ትንሣኤሁ ለክርስቶስ

በሀገርኛ ልሣናት አገባቡ እንዲህ ሊገለጥ ይችላል

⇝ በአማርኛ (☞ ክርስቶስ ተነስቷል ፣ ☜ በእርግጥ ተነስቷል!)

⇝ ኦሮሚፋ /Oromiffa (☞ Kiristoos du'aa ka'eera ፣ ☜ Dhugumaan ka'eera)

⇝ በትግሪኛ (☞ ክርስቶስ ተንሢኡ፣ ☜ በኻቂ ተንሲኡ)

⇝ በጉራጊኛ (☞ ክርስቶስ ተረሳም ፣ ☜ በውረም ተረሳም)
.
.
.
⇨ (በሌሎችም ሀገርኛ ልሳናት የቻላችሁትን ጨምሩበት)



(ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ በማዕዶት ፳፻፲፪ ዓ.ም. ተጽፎ በማሻሻያ ለዛሬ በድጋሚ የተለጠፈ )
5.9K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-04 18:31:25
#ቆዳ_ለሐመረ_ብርሃን

በአዲስ አበባና አካባቢው የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በረከት አያምልጣችሁ። እንደዋዛ የምትጥሉትን የፍየሎችና የበጎች ቆዳ ለሐመረ ብርሃን በመስጠት የታሪክ ባለቤት መሆን የምትችሉበት መንገድ ተመቻችቶላችኋል ስለዚህ በየሚቀርባችሁ ቦታ ወስዳችሁ በመስጠት ጥሩ ምንጭ ኢትዮጵያን በጥራት አስቀጥሉ።
የእንስሳቱ ቆዳ ከዚህ በታች የምትመለከቱትን ብራና ሁነው ይጠብቋችኋል።

የፍየል እና የበግ ቆዳ ለሐመረ ብርሃን
የትንሣኤ ዕለት ሚያዝያ 27

ፒያሳ አሮጌው ፖስታ ቤት
መካኒሳ ቅዱስ ሚካኤል
አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት
ሰአሊተ ምሕረት
ቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤል

ለበለጠ መረጃ፦ 0966767676 | 0944240000 | 0909444400 ይደውሉ።
5.7K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-04 16:06:49
5.8K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 21:06:20 ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት የሰሙነ ህማማት በገና መዝሙር በዲያቆን ድርሻዬ አከለ // ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ** Ethiopian Orthodox







7.4K viewsDrshaye Akele, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 10:21:54 የሆሣዕና ዝማሬ በዘማሪት ህጻን ሳሮን
የሆሣዕና ዝማሬ በዘማሪት ህጻን ሳሮን







5.8K viewsDrshaye Akele, 07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 23:37:54 . መፃጉዕ እና ኒቆዲሞስ
【 ዮሐ ፫ / ዮሐ ፭ 】
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
የዐቢይ ጾም ሳምንታት ከ፶ ሚሊየን ሕዝብ በላይ ባላቸው ተዋህዶን በሚያምኑ በጽባሓውያኑ ኦርቶዶክሳውያት አብያተ ክርስቲያን ዘንድ [ Eastern Christian churches adhering to Miaphysite Christology; Oriental Orthodox Churches】እኛ ከዘወረደ እስከ ሆሳዕና እንደምንዘክረው ከሆሳዕና በቀር በስያሜ የተለያየት መታሰቢያ ተሠጥቶት ይዘከራል
በብዙዎቹ ① ከብካበ ቃና ☞ ② ለምጻሙን ማዳኑ ☞ ③ ሽባውን ማዳኑ ☞ ④የከነናዊቷ ሴት እምነት ልጇን ማዳኑ ☞ ⑤ እኩለ ጾም/ በዓለ መስቀል ☞ ⑥ ደጉ ሳምራዊና ጀርባዋ የጎበጠች ሴት ☞ ⑦ ዘእውሩ ተወልደ ☞ ⑧ ሆሳእና ይታሰቡበታል።

በዚህ ውሥጥ በየሳምንታቱ የእነዚህ ታሪኮች መጻፍና መዘከር ምክንያቱ ታሪክ ‘አዋቆች’ ብቻ እንድንሆን አይደለም። ለምሳሌ በቅዱስ መጽሐፍ የቅዱሳን እና የርኩሳን፣ የቡሩካንና የርጉማን ፣ የጻድቃንና የኃጥዓን ታሪክ ሁሉ ተዘግቧል ምክንያቱ ደግሞ በሁለት መንገድ መረዳት ይቻላል። እንድንታነጽና እንድንገሠጽ

፩) የመልካም ሰዎች ታሪክ ⇨ ለጽናት በተስፋ ለመጽናናት
“በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።” 【ሮሜ ፲፭፥፬】

፪) የአመጸኞች ታሪክ ⇨ ለተግሳጽ
“ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።” 【፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፩】

በዚሁ መንገድ ሊቃውንትና መና**ፍቃን ፣ የካዱና የጸኑ ፣ በጎ ሠሪዎችና ክፉ አድራጊዎች … ግለሰቦችም ታሪካቸው ተዘግቦ ተነግሯል። ዐላማው እንደቀድሞው ለሁለት ጥቅም ነው ፤

፩) መልካም አድራጊዎች እንድናውቃቸው ምሳሌና አብነት እንድናደርጋቸው
☞ "ወአእምርዎሙ ለእለ ከመዝ ⇨ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው”
【፩ኛ ቆሮ ፲፮፥፲፰】

፪) ክፉ አድራጊዎችን ግን እንድናውቅባቸው ለመጠንቀቅ
☞ "ተዓቀቡ አንትሙሂ ወዑቅዎሙ ለከለባት ወዑቁዎሙ ለገበርተ እኪት ⇨ ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ።” 【ፊል 3፥2】

መፃጉዕና ኒቆዲሞስም በ፫ ክፍል ታሪክ የዚህ መንገድ አስተማሪዎች እንዲሆኑ በዐቢይ ጾም ሰንበታት የሚታሰቡ ግለሰቦች ናቸው

✧ ክፍል 【፩】 በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ እና ምዕራፍ ፭

ኒቆዲሞስ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወመልአኮሙ ለአይሁድ
ወውእቱ መጽአ ኀበ እግዚእ ኢየሱስ ቀዲሞ ሌሊቱ

መፃጉዕ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘሠላሳ ወሰመንቱ ክረምቱ እምዘደወየ ወኪያሁ ርእዮ እግዚእ እግዚእ ኢየሱስ ይሰክብ ውስተ ዐራቱ

ልዩነት
ኒቆዲሞስ ወደ ጌታው የመጣ
መፃጉዕ ጌታው ወደ እርሱ የመጣ
ኒቆዲሞስ ቀድሞ በሌሊት የሚገሰግሰው ከጌታው እግር ስር ሊማር (ለትምህርት)
መፃጉዕ ቀድሞ ወደ መጠመቀቂያው ውኃ ለመውረድ ደጅ የሚጠና ምኞቱ ሊማር (ለምሕረት)
ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ፣ ባለ ሥልጣንና ባለሀብት
መፃጉዕ ምሁረ ደዌ ፣ ሰው የሌለው ፣ ድኃ (ንብረቱ አልጋው ብቻ)
ኒቆዲሞስ ስሙ የተጠቀሰ መፃጉዕ ግን በህመሙ ደረጃ መገለጫው እንጂ በስም ያልተጠቀሰ 【የመፃጉን ስም አልተጠቀሰም መፃጉዕነት የደዌ መጽናት እንጂ ስም አለመሆኑን ልብ ይሏል ፤ ልክ እንደ አልአዛርና ነዌ (ባለጠጋው) 】

ስሙ አለመጠቀሱ ባለመታመኑ ነው፤ የጻድቃን መንገድና የታመኑ ሰዎች ስም መታወቁ በመንግሥቱ እውቅና እንዳላቸው ያስገነዝባልና
“ኄር እግዚአብሔር ለእለ ይትኤገስዎ በዕለተ ምንዳቤሆሙ ወያአምሮሙ ለእለ ይፈርህዎ ⇨ እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”።【 ናሆም 1፥7】
“እስመ እግዚአብሔር የአምር ፍኖቶሙ ለጻድቃን ወፍኖቶሙሰ ለኃጥኣን ትጠፍእ ⇨ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።”
【 መዝሙር 1፥6】

✧ ክፍል ፪
በአይሁድ ክስና ውንጀላ ውስጥ
☞ መፃጉዕ ወደ አይሁድ ሔዶ ክርስቶስን ከሰሰ ☞ ለክርስቶስ መገደል ምክንያትም ሆነ
በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ከቁጥር ፻፫ ጀምሮ እንደተነገው
«ዳሩ ግን በዚያ ስፍራ ሕዝብ ስለ ነበሩ ኢየሱስ ፈቀቅ ብሎ ነበርና የተፈወሰው ሰው ማን እንደ ሆነ አላወቀም። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው። ሰውዬው ሄዶ ያዳነው ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገረ። ስለዚህም በሰንበት ይህን ስላደረገ አይሁድ ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር።

☞ ኒቆዲሞስ ግን አይሁድ ወደእርሱ በመጡ ጊዜ ጥብቅና የቆመና እንዳይያዝ የሞገተ ሆኑ ተገኝቷል
በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፯ ከቁጥር ፶ ጀምሮ
« ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ፦
⁵¹ ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።»

✧ ክፍል ፫

መጻጉዕ ፦ ጌታውን በዕለተ ዓርብ በጥፊ መትቶ የመታበት እጁ ሰሎ ቀርቶ ከደዌው የታረቀ
ቀድሞ እንዲህ ሲል አስጠንቅቆት ነበር "ናሁኬ ሐየውከ ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ ⇨ ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው።” 【ዮሐ ፭፥፲፬ 】
እርሱ ግን "በዚያ ቆሞ የነበረው ከሎሌዎች አንዱ፦ ለሊቀ ካህናቱ እንዲህ ትመልሳለህን? ብሎ ኢየሱስን በጥፊ መታው።” 【ዮሐ ፲፰፥፳፪】

ኒቆዲሞስ ፦ በከበረና ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ ገዝቶ ለአምላኩ የመግነዝ ሥርዓት ፈጸመ፤ ከስውሩ ደቀመዝሙር ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ሆኖ አምላኩን ሥጋ ከመቃብር አውርዶ አካሉን በአዲስ በፍታ ሸፍኖ ወደ አዲስ መቃብር ያኖረ
【 ዮሐ ፲፱፥፴፰ እስከ ፵】
«ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።
የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።»

ኒቆዲሞስ በልሳነ ጽርእ ኒኮዴይሞስ "Νικόδημος" ይባላል በትርጉሙ ኒኮስ (νῖκος) እና ዴይሞስ (δῆμος) አገናኝቶ መዋዔ እም ሕዝቡ ይለዋል ከሕዝቡ ድል ያደረገ "victorious among his people" ይለዋል

ቤተክርስቲያናችን ሦስት ጊዜ ትዘክረዋለች
፩) የዕረፍቱን መታሰቢያ ነሐሴ ፩ ቀን ሠይማ
፪) በዐቢይ ጾም ደግሞ የ፯ኛ ሳምንት መጠሪያን ሠጥታ
፫) ለሁልጊዜው ደግሞ የቤተመቅደሱን አጥር ቅጥር እንደመግነዙ በመቁጠር የመግቢያ በሩን አዕማድ ለዮሴፍና ኒቆዲሞስ መታሰቢያ እንዲሆናቸው በማውሳት

የቅዱሱን የማታ ሰው የኒቆዲሞስን በረከት በሁላችን ላይ ያሳድርብን!

መልእክቱን በድምጽና በምስል ለመከታተልና ለመስማት በተከታዩን ሊንክ ታግዘው ማግኘት ይችላሉ


6.5K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 20:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 21:17:00

ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
5.7K viewsDrshaye Akele, 18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 20:39:57



ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
6.2K viewsDrshaye Akele, 17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ