Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵያዊነት

የቴሌግራም ቻናል አርማ nubiya — ኢትዮጵያዊነት
የቴሌግራም ቻናል አርማ nubiya — ኢትዮጵያዊነት
የሰርጥ አድራሻ: @nubiya
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 124
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጰያን ምን ያህል ያውቋታል?
ኑ ስለ ኢትዮጲያዊነት እንወያይ

አርጀንቲና! ኢትዮጵያን በስም ብቻ ነው የማውቃት ነው ያልከው?እውነት ብለሃል ኢትዮጵያን በስም ብቻ ማወቅህ አይገርምም፡፡እንኳን አንተ ዜጎቿ ራሳቸው በስም ብቻ ነው የሚያውቋት፡፡........የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ!!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-06 16:15:09 https://t.me/yelbenlenante
30 viewsአብርሃም, 13:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 15:34:14
46 viewsአብርሃም, 12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 15:34:11 #ዘቅጠናል በቃ እንመን !!

እኔ አንተ ሁላችን እውነትነቱ ባልተረጋገጠ ነገር ሀገር እናጫርሳለን። ለፖለቲካ ጥቅም ያውም ልንበላው ወይም ላንበላው ለምንችለው ነገር ንፁሃን ዜጎችን ደም እናፋስሳለን።

እኮ እንመን ዘቅጠናል!

ቅዱስ ቁርዓንም ሆነ መፅሐፍ ቅዱስ እንዲሁም የሌሎች ኃይማኖታዊ ማስተማሪያ መጽሐፍት (ሰይጣናዊ ካልሆኑ በቀር) የትኛውንም ኃይማኖት በማጥፋት ያንተን አስፋፋ ፣ ኃይማኖትህን አስተምር ፣ ግደል ጨፍጭፍ አይልም። እኛ ግን እያደረግነው ነው ።

እኮ ዘቅጠናል እንመን።


እኛ በፖለቲካ ፣ በኃይማኖት ፣ በብሔር ፣ በጎሳ እንናከሳለን ምስኪናን ወገኖቻችን የሚያርሱበት በሬ አጥተው ትከሻቸው እስኪላጥ ፣ መዳፋቸው እስኪገሸለጥ እየጎተቱ ሲያርሱ እኛ በለው፣ ፍለጠው ፣ አቃጥለው ወዘተ እንላለን።
ነገ የኑሮ ውድነት ተፈጠረ እያልን እናማርራለን ዛሬ ግን ጎራ ለይተን እንናከሳለን።

እኮ ዘቅጠናል እንመን ።


ነገ ከእነዚህ ሰዎች ጥቂቶቹ አሁን እያከናወኑት ባለው ነገር ( በእጃቸው ሲያርሱ ቢሞቱ ) ከእኛ በላይ አልቃሽ፣ ከእኛ በላይ ነጠላ ዘቅዛቂ የለም። ነገር ግን ዛሬ እኛ አናውቃቸውም ።

እኮ ዘቅጠናል እንመን በቃ እንመን !


አንተ የኃይማኖት ሰባኪ ነህ ...አንቺ የትልቅ ተቋም መሪ ነሽ ፣ እናንተ ባለስልጣናት ናችሁ ዛሬ ስሩ ነገ እዬዬ አትበሉ።

ይገርማል!!



እኔ አባቴን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ቤተሰቦቼ የእሴልምና እምነት ተከታዮች ናቸው። ታድያ ማን ማንን ይግደል?

አባትህ /ሽ ባይሆን እንኳን የሆነ ዘመድሽ የሌላ ኃይማኖት ተከታይ ነው እና ልትገዳደሉ ነው?

እኮ እመነዋ ዘቅጠናል።

ለኃይማኖትህ ስትል ሌላ እየገደልክ እኔ መንግሥቱን እወርሳለሁ ፣ ስሙን አወድሳለሁ ፣ በቤቱ እሰግዳለሁ ... ሶላት አወርዳለሁ እያልክ ታስባለህ ...? ታዲያ አልዘቀጥክም ዘቅጠሃል እመን ...... !!


የሆነች ነገር ስታገኝ ኢትዮጵያዬ እያልክ ታላዝናለህ ግን በቅፅበት ረስተህ ልትንዳት/ ልታፈርሳት ዜጋዋን ታፈናቅላለህ ፤ ታቃጥላለህ ፤ ታርዳለህ እኮ ዘቅጠሃል እመን ...!!

ስማኝ ሀገርህን በደስታህ ጊዜ ብቻ አትውደዳት ፣
ችግሯንም ችግሬህ አድርገህ ተቀበል።
ኃይማኖትህም ፣ አንተም ቤተሰብህም የምትኖሩት ሀገርህ ስትኖር ነው።


ወገኔ ሌሎች ሀገራት ላይ የደረሰው የግድ እኛ ላይ መድረስ እኮ የለበትም።

ከአፍጋኒስታ ፣ ከየመን ፣ ከኢራቅ ... ከሶርያ ልንማር ይገባል።

አምላካችን ሆይ የሰይጣንን ክንፉን ሰብረህ ሀገራችንና ዜጎቿን ጠብቅልን !!


t.me/yelbenlenante
42 viewsአብርሃም, 12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-03 06:29:20 ነግቷል ተነሱ
" ኤጭ_ደሞ_ነጋ!" የሚል አለ

" እሰይ_ነጋ!" የሚል አለ::

ህይውት ውብ ብትሆንም ለአማራሪ ግን ፉንጋ ናት::በውስጡ የተሸከመው ጨለማ አስተሳሰብ የህይወትን የውበት ብርሃን ይጋርድበታል::
ህይወትም አትወደውም::ስለሚጠላት ትጠላዋለች::ዳሩ ግን ጠልታው ሳይሆን የሰጣትን መልሳ ስለምትሰጥ ነው::

ከህይወት በላይ ህይወትን የምትመለከቱበት መንገድ ዋና ነው::ምልከታችሁ የህይወት መነፅራችሁ ስለሆነ ተጠንቀቁ::አንድ ጊዜ ህይወትን የምትመለከቱበት መነፅር ከተበላሸ የምትመለከቱት ነገር ሁሉ ይበላሻል::
ምልከታችሁ ምን ይመስላል ? ውብ ነው ፉንጋ ? አመስጋኝ ነው ? አማራሪ ? ተስፈኛ ነው? ወይስ ጨለምተኛ?

በጣም እጅግ በጣም ተጠንቀቁ::

የህይውትን በጎ ነገር የሚያጎላ የአመለካከት መነፅር ያዙ አመስግኑ ይቅርበሉ አፍቅሩ ተስፋአድርጉ ስጡ አሁን ውስጥ በደስታኑሩ ከህይወት ወንዝ ጋር ፍሰሱ::

መልካም የስራ የስኬት የደስታ ጊዜ!
t.me/yelbenlenante

ከሆነ ቦታ የተነበበች
88 viewsአብርሃም, 03:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 18:52:10 #3D_ፍቅር !!

"...የግራ እጄን በቀኝ እጇ ይዛ በግራ እጇ አቅፋኛለች።
ስንራመድ ሁለት ሳይሆን አንድ እንመስላለን እቅፍቅፍ ብለን ።
ቀና ብላ ስታየኝ ጥቁር ቸኮላት የመሰለው ውብ ፊቷ ፣ በረዶ የመሰሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ፣ ጥቁር ዞማ ፀጉሯ ፣ ሰርጎድ ብላ የምትታየው ዲምፕሏ ፣ ትላልቅና የሚያማምሩ ዐይኖቿ ... አፍንጫዋ ላይ ያለችው ጌጥ ቀጥ ሊያደርጉኝ ሲሞክሩ እየሳቀች ጉንጬን ሳም ስታደርገኝ በቁሜ እፈዛለሁ፣ እደነዝዛለሁ!!
በዛፎች የተከበበችውንና ቀዝቃዛውን ከዚራን ለፍቅራችን ማድመቂያ አደረግናት።

አብዛኛው ሰው እዚያ ስፍራ የማዘውተሩን ሚስጥር የደረስኩበት ዘግይቼ ነው።
ማታ ማታ ጥንድ ጥንድ ሆነው በሚጓዙ ፍቅረኛሞች ትደምቃለች።
ትኩስ የፍቅር መናኸሪያ ትሆናለች። ከከንፈር ላይ የማር ጠብታን የሚልሱና የሚቀምሱ የሚመስሉ ተሳሳሚዎች፣ ድምፃቸውን ገደብ አልባ በሆነ ሳቅ የሞሉባት ሳቂታዎች በርክተው የሚታዩት ማታ ነው።

በዚህ መንገድ ነበር ብዙውን ጊዜያችንን ጥብቅ'ብቅ ብለን ብዙ ሳቅና ጨዋታ የሞላውን ወሬ እያወራን የምናዘግመው!

ከሩትዬ ጋር ድሬዳዋን ደመቅንባት ... ከግንፍሌ እስከ ቅዳሜ ገበያ ...ከኮንጎ ሜዳ እስከ ደቻቱ ሳባ ዳቦ ....ከሳሬምመጋላ ....ከፍል ውሃቀፊራ ያልተጓዝንበት የለም ።

አንድ ቀን ነምበር ዋን አከባቢ የሚገኘው ፋሲካ ሆቴል ቁጭ ብለን እያወራን ተቅበጠበጠች።
የጠጠጣችው ዋይን መሆኑ አልጠፋኝም።
ሞቅ ብሏታል በዚያ ላይ የለበሰችው ወይን መሳይ ቀለም ያለው ቀሚስ ጭኗን ገለጥ አድርጎ ያሳያል።
የልብሱ አሰራር ከወገቧ ቀጠን ብሎ ሽንጧን ይዞ ዳሌዋ አከባቢ የተወጠረ የልብስ መስቀያ ይመስል ሞላ ብሏል።
ጠይም ከንፈሯን በስሱ ጥቁር የከንፈር ቀለም ተቀብታዋለች።

ምሽቷ በዚያን ሳምንት ካሳለፍናቸው የፍቅርና የፍንደቃ ጊዜያት ምርጧ ምሽት ነበረች።

"....ሙቀቱ ከላይ የለበስኩትን የመኝታ ልብስ እንዳወልቅ አስገድዶኛል።
እንግዳ መሆኔ እንደፈለኩ እንድሆንና እንዳደርግ አልተመቸኝም።

በደብዛዛው የበራችው ዜሮ አምፖል ቤቱን ጭላንጭል ብርሃን እንዲበራ አድርጋዋለች።
ቤቱ ውስጥ የተኙት አብዛኞቹ እራቁታቸውን ናቸው።

ራቁቴን እገላበጣለሁ የበላሁት ለውዝ ከሙቀቱ ጋር ተደምሮ የሆነ ቀስቃሽ ሆነውብኝ ተወጥሬያለሁ።

ውሃ ሰማያዊ የተቀባው የግድግዳ ቀለም ላይ የተሰቀሉት የተለያዩ የቤት ውስጥ ጌጣጌጦች እይታን ይማርካሉ!!

ድሬዳዋ ከቀን ይልቅ ማታ ሞቃት ናት።
ሞቃት ብቻ ናት ከምል ትግላለች ብል ሳይቀል አይቀርም።
ቀን ላይ ጭር ትላለች በተለይ ከ8:00- 10:00 ሁሉም እረፍት ያደርጋል። መቃም የፈለገ በዛፎች ወደ ተከበበችው ከዚራ ጎራ ይልና ከዛፎቹ ስር ጎዝጉዞ ይቅማል፣ ይጫወታል።

ማታ እንደ ዲምላይት ከጫፍ እስከ ጫፍ ድረስ በብርሃን ትጥበረበራለች።

ሩትዬ ሁልጊዜ እጆቿን ትከሻዬ ላይ ጣል ሳታደርግ አትንቀሳቀስም።
አንድ ቀን ቁርስ ልንበላ ከመንገድ ዳር ቁጭ ብለን
ፉል በሳልሳ አዘን እስኪወጣልን ዐይኔን በስስት እየተመለከተች ጉንጬን ሳም እያደረገች እኔ እየተሽኮረመምኩ እያለ አንዱ " ዋው ስታስቀኑ! " አለ

ፊቷ እንደ ሌሊት ጨረቃ ጥርት እንደ ፀሐይ ሙቀት ሲረጭ ተሰማኝ ።
እጆቻችንን አቆላልፈን ምግቡ ሲመጣ አንዳችን ሌላውን እየተጎራረስን መንገድ ዳር የተቀመጡት ሰዎች ሁሉ ይስመርላችሁ እያሉ ይመርቁናል።
ድሬዳዋ የመንገድ ላይ ምግብ መመገድ እንደ አንድ ባህል ተደርጎ የተወሰደ ይመስላል።
ጥዋት ቀለል ያሉ ቁርሶች ...ፉል በድንች ... ፉል በእንቁላል፣ ፉል በሳልሳ ( የአከባቢው መጠሪያ ነው እኛ ጋር ስልስ በመባል ይታወቃል ቲማቲም ተቀምሞ ማለት ነው።) መሰል ምግቦች ተመራጭ ናቸው።

እራት ላይ እንዲሁ የተለያዩ ነገር ግን ድንች የሌለው ምግብ በጭራሽ አይኖርም።
ድንችን ጠዋትም ቀንም ማታም በሚመገቧቸው ምግቦች ስለማትጠፋ 3D ተብላ ትጠራለች።

ከሩትዬ ጋር ድሬዳዋን ክንፍ አውጥተን ቦረቅንባት አንድ ቀን የሆነ ቦታ ልውሰድህ አለችኝ።
እንግዳ መሆኔ ብዙ ቦታዎችን ለማየት ጉጉት አድሮብኝ እሺ ብዬ አብሬያት ሄድኩ!
ድሬደዋ ከተማን ለሁለት ሰንጥቆ የሚያልፈውን የጎርፍ መንገድ ወይም አሸዋ ሜዳ አቀናን ! ደስ ይላል በዚያው ስፍራ ያሉ ቤቶች ዙሪያቸውን በረጃጅም የኮንክሪት አጥር ታጥረዋል ለምን እንደሆነ አልጠፋኝም።

ከዚያ መልስ በድሬዳዋና ሐረር አከባቢ ከሚታወቁት ምግቦች ጣፋጮቹን እየዞርን ፈጀናቸው።

መላዋ ( በስንዴ ዱቂት አልያም በፉርኖ የሚሰራ ጣፋጭ ምግብ !
ሙሸበቅ፣ በቅላባ፣ ሀላዋ( ውስጡ ለውዝ ያለው ጣፋጭ ምግብ)
ፈጢራ (በማር የሚሰራ )
ባጊያ ይሄም በስኳርና በፉርኖ ዱቄት የሚዘጋጅ ...
ሚጣጢስ ብቻ ሁሏንሜ ጣፋጭ ምግብ የተባለ ሁሉ አልቀረንም ....እሱን ጨርሰን በኢትዮጵያ ብቸኛው የተማሪዎች ባንድ የተዘጋጀውን ሙዚቃ ታድመን ፣ ጨፍረን ... ጨረኔ ከጠረኗ ተደባልቆ ..ድክም ብለን መንገድ ላይ ስንሄድ መንገድ ላይ ሶስት ውሃ ሰማያዊ ቀለም ተቀብተው የተቀመጡ እንስራዎች አገኘን አስታውሳው እየሳቀች ይህ በእኛ አጠራር ጃህላ ይባላል እነዚህ የምታያቸው ደግሞ የተፈጥሮ ፍሪጆች ቀመባል ይታወቃሉ አለችኝ።

ከእንስራዎቹ አጠገብ ዕድሜ ጠገብ የዘንባባ ዛፎች አሉ ከውሃው ጎንጨት ስል ቅዝቃዜው ቶንሲሌን ሊቀሰቅሰው ትንሽ ቀረው።

በጉብኝታችን ወቅት ከዚራ አከባቢ የሚገኘውን ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን .... የጃንሆይን ቤተ መንግሥት!!

ልዑል ራስ መኮንን በ 1885 ዓ.ም ቆርቁረው በ 1887 ዓ.ም ቤተመንግሥቱን ሠሩ። ሁለተኛም የኢትዮጵያ መንግስት አልጋወራሽና ባለ ሙሉ ሥልጣን እንደራሴ በነበረበት ጊዜ 1914 ዓ.ም ልዑል ራስ መኮንን የሠሩትን አሻሽለው እና አስፋፍተው ተሰራ።

በሶስተኛውም ጊዜ በ 1947 ዓ.ም ልዑል ራስ መኮንን ከመሠረቱበት ቦታ ላይ የመሠረት መልኩን ሳይለወጥ ልዑል መኮንን ኃይለሥላሴ መስፍነ ሐረር ፕላኑን አሻሽሎ ባቀረበው አይነት ሁለተኛውን ፎቅ ተጨምሮበት እንዲሰራ ፈቅደው ይኸውም ሥራ 1947 ዓ.ም ተጀምሮ በ 1955 ዓ.ም ተጠናቀቀ።

ባሳለፍኳቸው ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በጣም ብዙ የተላመድኳቸው ቤተሰቦቿና አንዳንድ ጓደኞቿን መለየት እንደ ሞት ያህል ይሰማኝ ደመር።

ያንን አጉራሽ ፣ አልባሽ ፣ ሰው የሚጠግብ የማይመስለው ቤተሰቧን ጥሎ መሄድ አልቻልኩም ነገ ዛሬ እየተባልኩኝ ሁለት ቀናትን አሳልፌ በስተመጨረሻ እስከ ናዝሬት ድረስ የባቡር ቲኬት ቆረጥኩ !

እኔና ሩትዬ የምንገናኝ ቢሆንም ቤተሰቦቿንና አንዳንድ ሰዎችን ድጋሚ የማገኛቸው በፈጣሪ ፈቃድ ሴለሆነ ተላቀስን ስመው መርቀው ሸኙኝ።

ገና ባቡር ውስጥ ገብቼ እንደተቀመጥኩ ነበር እያንዳንዱ ሁነት እንደመስታወት ጥርት ብሎ መታየት የጀመረው !

ጉዞውን አብዛኞቹ በእንቅልፍ ቢገፉትም እኔ ግን የሃይማኖት ግርማን " ከዚራ ነው ቤቴ እያልኩ በትኋንና በቁንጫ እንደ ተሰቃየሁ መዳረሻ ላይ ደረስኩ !

እግሬ መሬት ቢረግጥም መንፈሴ ግን እዛው ድሬ ሩትዬ ጋር ነው።

ትዝታዎቹ ክልልል ብለው ይመጡብኛል።

ጠዋት ማታና ቀን ላይ ልክ እንደ ድንቹ 3D ፍቅሯን የምትለግሰኝ!!

ምንም እንኳን እኔ ስፅፈው ባንዛዛውም ትክክለኛውን ስለድሬ መረጃ ስለሰጠኸኝ ደጀኔ ማሙዬ አመሰግናለሁ!!!

አብርሃም ኑናቶ
61 viewsአብርሃም, 15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-13 06:48:55 Good morning
“የሰዉ ልጅ በጣም የሚገርም ፍጡር ነዉ፡፡ ገንዘብ ለማግኘት ሲል ጤናዉን መስዋእት ያደርጋል፡፡ ከዛ መልሶ ጤናዉን ለማግኘት ያለዉን ገንዘብ በሙሉ ያፈሳል፡፡

ስለነገ በጣም ይጨነቅና ዛሬን መኖር ይረሳል ፣ ዉጤቱ ደግሞ ዛሬንም ነገንም እንዳይኖር ያደርገዋል፡፡ ሰዉ አንድም ቀን እንደማይሞት አድርጎ ይመላለሳል ነገር ግን አንድም ቀን ሳይኖር ይሞታል”

""" ዳላይ ላማ""

ስለነገ የሚያውቅ የለምና ዛሬን እራሳችንንም ሌሎችንም ደስተኛ በማድረግ እንኑራት፡፡
ውብ ቀን

t.me/yelbenlenante
72 viewsአብርሃም, 03:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-09 04:46:29 - - - - -
ማፍቀር እራሱ ጥቅም ነው። በማፍቀር መናወዝ መችም የትም ከማይገኝ ስሜት ጋር ያስተዋውቃል። በአንፃሩ ደግሞ ማፍቀር አለመቻል ፀፀት ነው። በሰው ሕይወት ውስጥ ጣልቃ ያስገባል።

- - - - -
#ሐሰተኛ_በእምነት_ስም (ገፅ 120)
#አለማየሁ_ገላጋይ

t.me/yelbenlenante
80 viewsአብርሃም, 01:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-05 12:13:44 ማንበብ ምግባርን ከመግራት አንፃር ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል ብዬ አምናለሁ።
ንባብን እንደልጓም እቆጥረዋለሁ ከስነ-ምግባር አንፃር።ባነበብከዉ ልክ ወደ ውስጥህ ትመለከታለህ።አካሄድህን ትመዝነዋለህ።ቆም ብለህ ትመለከተዋለህ።በአንፃራዊነት ምንም እንኳ በጥናት ባይደገፍም የሚያነብ ሰዉ ከማያነብ ሰዉ የተሻለ ስነምግባር እንደሚኖረው አስባለሁ።
መልካም ቀን!

t.me/yelbenlenante
83 viewsአብርሃም, 09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-31 14:04:55
74 viewsአብርሃም, 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-31 14:04:52 "የማያነብ ሰው ማንበብ ከማይችል ሰው ተለይቶ ሊታይ አይገባውም።" ማርክ ቱዋይን
69 viewsአብርሃም, 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ