Get Mystery Box with random crypto!

ጥምር ግቢ ጉባዔ (በደ/መ/ቅ/ሚካኤል ካ/የፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት ት/ቤት)

የቴሌግራም ቻናል አርማ dmkmc — ጥምር ግቢ ጉባዔ (በደ/መ/ቅ/ሚካኤል ካ/የፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት ት/ቤት)
የቴሌግራም ቻናል አርማ dmkmc — ጥምር ግቢ ጉባዔ (በደ/መ/ቅ/ሚካኤል ካ/የፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት ት/ቤት)
የሰርጥ አድራሻ: @dmkmc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 278
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደ/መ/ቅ/ሚካኤል ካቴድራል ጥምር ግቢ ጉባዔ ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል በደብሩ ሰ/ት/ቤት ስር በሚገኙ የአዲስ ከተማ ፣ የህይወት ብርሃን፣ የአንዳርጌ እና የአቢሲኒያ ት/ቤት የተማሪዎች ግቢ ጉባዔያት ከሰንበት ት/ቤቱ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው፡፡ በዚህም ሃይማኖታዊ ይዘት ያለቸው መርሃ ግብሮችን ለአባላቱ ያደርሳል፡፡ ለመወያያ @DMKMCG ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @DMKMCbot

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-08 20:40:11
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ልዩ የሥልጠና መርሐ ግብር

"ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን (ምሥጢራዊው ፀረ-ተዋህዶ እንቅስቃሴን የተመለከተ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና)"

“ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።”ማቴ ፳፬፥፬

ለሰ/ት/ቤታችን አባላት፣ ጊቢ ጉባዔያትና ለማኀበራት በሙሉ እሁድ ሐምሌ 03/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ምስጢራዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የዕቅበተ እምነት ስልጠና የተዘጋጀ ሲሆን ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላት፣ ማኀበራትና የአካባቢ ወጣቶች በሥልጠናው ላይ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

አድራሻ፦ በካቴድራሉ ትምህርት ቤት አዳራሽ
38 views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:19:48 ስንክሳር ዘወርሃ ሰኔ ሃያ ዘጠኝ(፳፱)




@dmkmc
@dmkmc
@dmkmc
66 viewsedited  18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:01:07
64 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:01:07
46 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:01:06 ከዚህም በኋላ እናቱ ወደርሱ መጥታ አረጋጋቸው በመጋደሉም ደስ ተሰኘችበት። ስለ እርሷም ለመኰንኑ ነገሩት እርሱም ወደ እርሱ አስቀርቦ እያስፈራራ "ለአማልክት ሠዊ" አላት። እርሷ ግን አልፈራችውም ትእዛዙንም አልሰማችም የብረት በትሮችንም አግለው በጎኖቿ ውስጥ እንዲአደርጉ አዘዘ ይህንም በእርስዋ ላይ በአደረጉ ጊዜ ደስ ብሏት ዘመረች ስለ ቅዱስ ስሙም መከራ እንድትቀበል ያደረጋት እግዚአብሔርን አመሰገነችው ከዚህም በኋላ ነፍሷን ሰጠች የሰማዕትነትም አክሊል ተቀዳጀች።

ቅዱስ አባ ሖርንም ከቅባትና ከተቀመመ የነዳጅ ቅመም ጋራ በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት እርሱም ያለ ሕማም ሁኖ እግዚአብሔርን ያመሰግን ነበር ይህንንም ለመኰንኑ ነገሩት እርሱም እጅግ አደነቀ ደነገጠም። ንጉሡ ግን ተቆጣ በእጁም ጦር እንዳያዘ ወደ ብረት ምጣዱ ሒዶ ቅዱስ ሖርን ወጋው ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።

እንዲሁም ወንድሙ አባ ብሶይን ብዙ ሥቃይን ካሠቃዩት በኋላ ራሱን በይፍ ቆረጡት። ሁሉም በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

+ + +
"ሰላም ለማርቆስ ጊዜ ተሠልጠ ዘመኑ። እንዘ ሀሎ ደብረ ቶርማቆ መካኑ። ወንጌል ቅዱሰ እንተ ማቴዎስ ይዜኑ። ሶበ ይብይ ለመልአከ ሰማይ ልሳኑ። መነጠ ፭ቱ እመት ተለዓለ በድኑ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ29።

=>#ሰኔ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማርቆስ ንጉሠ ሮም (ጻድቅ: ንጹሕና ገዳማዊ)
2.ቅዱስ ቴዎድሮስ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
3.ቅዱስ ዓምደ ሚካኤል ኢትዮዽያዊ (ፍልሠቱ)
4."7ቱ" ቅዱሳን መስተጋድላን (አባ አብሲዳ: አባ ኮቶሎስ: አባ አርድማ: አባ ኒኮላስ: አባ ሙሴ: አባ እሴይ: አባ ብሶይ)
5.ቅዱሳን አባ ሖር: አባ ብሶይ: አባ ሖርሳና እናታቸው ቅድስት ይድራ (ሰማዕታት)

=>#ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
6.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)

=>+"+ አቤቱ በኃይልህ ንጉሥ ደስ ይለዋል::
በማዳንህ እጅግ ሐሴትን ያደርጋል::
የልቡን ፈቃድ ሰጠኸው::
የከንፈሩንም ልመና አልከለከልኸውም::
በበጐ በረከት ደርሰህለታልና::
ከከበረ ዕንቁ የሆነ ዘውድን በራሱ ላይ አኖርህ::
ሕይወትን ለመነህ ሰጠኸውም::
ለረጅም ዘመን ለዘለዓለሙ::
በማዳንህ ክብሩ ታላቅ ነው:: +"+ (መዝ. 20:1-5)


+ + +
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3።

#የሚነበበው_ወንጌል ማቴ 2፥1-13።

+ + +
#የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና። ወያስተዴሉ ክረምተ ለምድር። ዘያበቊል ሣዕረ ውስተ አድባር"። መዝ 146፥8።

#የሚነበቡት_መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 3፥13-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 1፥4፥9-18 እና የሐዋ ሥራ 9፥20-23።

#የሚነበበው_ወንጌል ማቴ 16፥24-ፍ.ም።

#የሚቀደሰው_ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጻድቁ ንጉሥ የቅዱስ ቴዎድሮስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችን ይሁንልን።
39 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:01:06 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"

#ሰኔ ፳፱ (29) ቀን።

እንኳን ለንጉሥ ዳዊት ልጅ ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለጻድቁ ለቅዱስ ቴዎድሮስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለከበረ ለቅዱስ ዐምደ ሚካኤል ለሥጋው ፍልሰት በዓል፣ ለንጹሕ ጻድቅ ለሆነ ለሮሜ ንጉሥ ለቅዱስ ማርቆስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ከቆና ገዳም ለሆኑ ለሰባት መስተጋድላን ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዐረፍታቸው በዓል መታሰቢያና ለቅዱሳን ለአባ ሖር፣ ለአባ ብሶይና ለእናታቸው ይድራ ከአንጾኪያ ንጉሥ ሠራዊት ውስጥ ለሆነ ለአባ ሖርሳም ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከክብር ባለቤት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታች ቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ከተወለደበት ከልደቱ (ከበዓለ ወልድ) ከወራዊ ከመታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
#የንጉሥ_ዳዊት_ልጅ_የኢትዮጵያ_ንጉሥ_ቅዱስ_ቴዎድሮስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ በዕውቀትና በተግሣጽ አደገ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት የተማረ ደግሞም ቀስት ማፈናጠርንና ፈረስ ግልቢያን ተማረ ኃይል ያለውም ብርቱ ሰው ሆነ።

ከታናሽነቱም ጀምሮ በእግዚአብሔር ፍቅር ታሠረ ገንዘቡን ለድኆችና ለችግረኞች ይመጸውት ነበር። አብያተ ክርስቲያንንም እጅ መንሻ ከመያዝ ጋራ ይጎበኝ ነበረ በጸሎቱና በጾምም ይጋደል ነበር። ካንዲት ሴት በቀር አላገባም በማንም ላይ ዐመጻና ግፍ ከቶ አልሠራም።

ወደ ኢየሩሳሌም ለመሔድ በአሰበ ጊዜ አባ ማርቆስን አማከረው እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ያውቅ ነበርና "ክፍልህ አይደለም" አለው።

ከዚህም በኋላ ባረፈ ጊዜ በክረምት ወራት በድኑን ሲወስዱ ሞልቶ የነበረው ወንዝ ወዲያና ወዲህ ተከፍሎ ተሻገሩ በቀበሩበትም ቦታ ሕይወትነት ያለው ውኃ መነጨ እስከ ዛሬም አለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ንጉሥ በቅዱስ ቴዎድሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

+ + +
በዚችም ቀን የከበረ ዐምደ ሚካኤል የሥጋው ፍልሰት ሆነ መጀመሪያ በንጉሥ እስክንድር ዘመነ መንግሥት ወደ አባቶቹ መቃብር ዳግመኛም በንጉሥ ልብነ ድንግል ዘመን በአረፈ በአርባ ዓመቱ ፈለሰ አባቶቹ ነገሥታት ወደተቀበሩበት ወደ አትሮንሰ ማርያም አፍልሰው እንዲወስዱት ንጉሡ አዝዞ ነበርና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

+ + +
"ሰላም ለከ ለብሔረ አግዓዚ ንጉሣ። ቴዎድሮስ ዕጓለ አንበሳ። ተዝካረ በዓልከ ዮም በጥብሐ አባግዕ ወእንሰሳ። አኮ ዘገብረት ባሕቲታ እምከ ጽዮን ሞገሳ። ደመናትኒ አንጠብጠቡ ዓሣ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ 29።

+ + +
#የሮሜ_ንጉሥ_ቅዱስ_ማርቆስ፦ ይህም ቅዱስ ንጹሕ ጻድቅ ነበር። በድንግልናው አምስት ዓመት ነገሠ ሕዝቡንም እግዚአብሔርን በመፍራትና በቅን ፍርድ ጠበቀ። እርሱንም ከመውደዳቸው የተነሣ ሚስቱን እንዲአገባ መኳንንቱ አስገደዱት እርሱ ግን በሌሊት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቁሞ ጸለየ "እመቤቴ ሆይ ላንቺና ለማይሻር ንጉሥ ልጅሽ እገዛ ዘንድ ወደ ምሔድበት ምሪኝ" አላት። እርሷም "ወደ ቶርማቅ ተራራ ሒድ እግዚአብሔር ከአንተ ጋራ ይኑር" አለችው።

ከዚህም በኋላ በሌሊት ወጥቶ ሔደ ወደ ባሕር ወደብም በደረሰ ጊዜ ያለ መርከብ ተሻግሮ ወደ ቶርማቅ ተራራ ደረሰ ያም ቦታ ደረቅ ነበረ ከአጋንት ጋራም እየተጋደለ በውስጡ ስልሳ ዓመት ኖረ። ሰኔ 29 ቀን በዐረፈ ጊዜም መላእክት በክብር ቀበሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ንጉሥ በቅዱስ ማርቆስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

+ + +
#በቆና_ገዳም_የነበሩ_ሰባት_መስተጋድላን_ሰማዕታት፦ የእሊህም ስማቸው አባ አብሲዳ፣ አባ ኮቶሎስ፣ አባ አርድማ፣ አባ ሙሴ፣ አባ እሴይ፣ አባ ኒኮላስና አባ ብሶይ ናቸው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጾ እንዲህ ብሎ "አዘዛቸው ክብር ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ግለጡ"።

ያን ጊዜም ወደ መኰንኑ ሊሔዱ ተነሡ መርከብንም አገኙ በመርከቧም ውስጥ አምስቱን መስተጋድላን አገኙአቸውና ከእነርሱ ጋር ተስማሙ ወደ መኰንኑም ደርሰው በፊቱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ታመኑ። መኰንኑም ከእርሳቸው አንዱን ስለ ሀገራቸው ጠየቀው እርሱም ቆና ከሚባል አገር እንደሆኑ አስረዳው መኰንኑም ያሥሩዋቸው ዘንድ አዘዘ።

ከዚህም በኋላ ደግሞ ከእሥር ቤት አውጥተው ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩአቸው ዘንድ ደግሞም በአንገቶቻቸው ከባድ ደንጊያዎችን አንጠልጥለው እንዲአሥሩዋቸው አዘዘ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በውህኒ ቤት ውስጥ ተገለጠላቸው አጽናናቸውም ቃል ኪዳንም ገባላቸው።

ከዚህ በኋላ ንጉሥ ወደ እስክንድርያ ከተማ ላካቸው በዚያም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩአቸው። ከዚህም በኋላ ዝፍትና ድኝ በተመሉ ከሁለት የብረት ምጣዶች ውስጥ ጨመሩአቸው ነበልባሉም ሃያ ክንድ ከፍ ከፍ እስሚል ድረስ ከታች እሳትን አነደዱባቸው ከምጣዶችም ውስጥ አውጥተው በእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመሩአቸው ጌታችንም ዳግመኛ ተገልጾ ያለ ምንም ጉዳት አዳናቸው።

ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ቀርበው ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው መቶ ሠላሳ ሰዎች በጌታችን አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። ከዚህም በኋላ አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃያቸው ወደ እነርሱም አጵሎን የሚሉትን ጣዖት በወንበር እንደ ተቀመጠ አምጥቶ እንዲሰግዱለት አዘዛቸው እነርሱም ግን በእግሮቻቸው ረገጡትና ከመንበሩ ወድቆ ተሰበረ።

መኰንኑም አይቶ እጅግ ተቆጣ እግሮቻቸውንም እንዲቆርጡ አዘዘ የቅዱስ ቀሲስ አብሲዳንን ግን ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ምስክርነቱን ፈጸመ እንዲሁ ደግሞ እሊያ አምስቱንም ራሶቻቸውን ቆረጡ ቅዱስ ኮቶሎስን ግን በእሳት አቃጠሉት ሁሉም የሰማዕትነት አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰባቱ መስተጋድል ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።

+ + +
#ቅዱሳን_አባ_ሖር፣ #አባ_ብሶይና #እናታቸው_ይድራ #ከአንጾኪያ_ንጉሥ_ሠራዊት_ውስጥ_የሆነ_አባ_ሖርሳ፦ እሊህም ወደ እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ በመኰንኑ ፊት ክብር ይግባውና በጌታች ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ መኰንኑም አባ ብሶይን ይዘው ቀኝ እጁንም አሥረው በከተማዎች ሁሉ በበሬዎች እንዲጐትቱት አዘዘ።

ከዚህም በኋላ የተዘረጉ ብረቶችን በእሳት አግለው በሥጋው ውስጥ አደረጉ የግራ እጁንም ቆረጡ እርሳስም አቅልጠው በአፉ ጨመሩ ጊንጦችና እባቦች ወደ ተከማቹበት ውስጥ ጣሉት እነርሱ ግን ከቶ አልቀረቡትም።

ከዚህም በኋላ በብረት በትሮች ይደበድቡት ጀመር እርሱም "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርዳኝ ከዚህ ሥቃይም አድነኝ" ብሎ ጮኸ ጌታችንም አጸናው እንደቀድሞውም ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ አድርጎ አስነሣው።
41 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 22:13:29 ስንክሳር ዘወርሃ ሰኔ ሃያ ስምንት(፳፰)





@dmkmc
@dmkmc
@dmkmc
54 viewsedited  19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:38:35
52 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 21:38:34 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"

#ሰኔ ፳፰ (28) ቀን።

እንኳን ለእስክድርያ (ለግብጽ) አገር ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሦስተኛ ለሆነው ሃያ ስምንት ዓመት ሙሉ በስደትና በመከራ ላሳለፈ ለታላቁ አባት ለአባ ቴዎዶስዮስ ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልና ለአባ ያዕቆብ እል-በረዲ ለመታሰቢያ በዓሉ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰብ፦ ከቅዱስ ባስልዮስና ከቢፋሞን፣ ከባሊዲስና ከኮቶሎስ፣ ከአርዳሚስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

+ + +
#አባ_ቴዎዶስዮስ፦ ይህም አባት ለእስክንድርያ አገር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሦስተኛ ነው። በዚህም ቅዱስ በስሙ በግብጽ ምድር ውስጥ ምእመናን ቴዎዶስዮሳውያን ተብለው ተጠርተውበታል። ይህም የሆነው እንዲህ ነው ሊቀ ጵጵስና ከተሾመ በኋላ ክፉዎች ሰዎች በእርሱ ላይ ተነሥተው በንጉሥ ምክር ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት በእርሱ ፈንታም አስቀድሞ በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዲያቆናት የነበረ ስሙ አቃቅያኖስ የሚባለውን አንድ ሰው ሾሙ እርሱም ለአባ ቴዎዶስዮስ ሊቀ ጵጵስና እንዲገባው ከፈረሙት ቁጥር ውስጥ ነበር።

ይህም አባት ወደ ግርማኖስ አገር ሒዶ ሦስት ወሮች ኖረ በዚያም ወራት በግብጽ አገር ንቡረ እድ አባ ሳዊሮስ ነበር እርሱም በአባቶቻችን ሐዋርያት እንዲሁም በአትናቴዎስና በዮሐንስ አፈወርቅ የደረሰባቸውን መከራ እያስታወሰ ያጽናናቸው ነበር። ከዚያም ተነሥቶ መሊግ ወደሚባል አገር ሔደ በዚያም ሁለት ዓመት ተቀመጠ።

የእስክንድርያ ከተማ ሰዎችም የጠባቂያቸው የቴዎዶስዮስ መመለስ ሺተው በእስክንድርያው መኰንን ላይ ተነሡበት መኰንኑም ወደ መንበረ ሢመቱ መለሰው አቃቅያኖስንም አባረሩት። ይህም ነገር በንጉሥ ዮስጣቲያኖስና አምላክን በምትወድ በንግሥት ታዖድራ ዘንድ ተሰማ ንግሥቲቱም አስቀድሞ የተሾመው በሹመት ወንበሩ ይቀመጥ ብላ ጻፈች።

ሃምሳ ስምንት ካህናትም ጉባኤ አደረጉ "አስቀድሞ የተሾመ አባ ቴዎዶስዮስ ነው" ሲሉም ጻፉ። ያን ጊዜም አቃቅያኖስ በሕዝብ ፊት ቁሞ "ክፋዎች ሰዎች ስለ አስገደዱኝ ይህን ሥራ ለመሥራት ሕግን ተላልፌአለሁ" አለ። ከዚህም በኋላ አቃቅዮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ነገር ግን ክህነትም ሆነ ሊቀ ዲቁና ለዘለዓለም እንዳይኖረው ሕዝቡ አባ ቴዎዶስዮስን ለመኑት። አቃቅያኖስ "አዎ እንዲሁ ይሁን" አለ ይህም አባት ከግዝቱ ፈታው።

ሃይማኖቱን ያጠፋ ንጉሡ ግን በከፋች ሃይማኖቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ ከእርሱ ጋራ የሚስማማ መስሎት በእስክንድርያ ወዳሉ መኳንንቶቹ እንዲህ ብሎ ጻፈ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ በሃይማኖት ከእኛ ጋራ የሚስማማ ከሆነ ሹመት ይጨመርለታል። ለእስክንድር ከተማ ገዥ ይሆናል። ይህ ካልሆነ ከሹመቱ ይሻር።

ይህም አባት ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እንዲህ አለ ሰይጣን "በበረሀ ጌታችንን ብትሰግድልኝ የዓለም መንግሥታትንና ክብራቸውን ሁሉ እሰጥሃለሁ" አለው። ያን ጊዜም ይህ አባ ቴዎዶስዮስ ተነሥቶ ከእስክንድርያ ወጣ ወደ ላይኛው ግብጽም ሔደ በዚያም ሕዝቡን እያስተማራቸው በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ጥቂት ቀኖች ኖረ። ንጉሥም አባ ቴዎዶስዮስ ከእስክንድርያ ከተማ እንደ ወጣ በሰማ ጊዜ እየሸነገለው ወደ እርሱ መልእክት ላከ እንዲህም አለው እኔ ከአንተ ጋራ ልነጋገር ከአንተም ልባረክ እንድትመክረኝም እሻለሁ"።

ከዚህም በኋላ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ ሔደ የጳጳሳት አለቆችና ሕዝቡ ሁሉ ሠራዊቱም ተቀበሉት ከፍተኛ ወንበርም ላይ አስቀመጡት። እርስ በርሳቸውም ስለ ሃይማኖት ተከራከሩ ንጉሡም አብዝቶ ሲሸነግለውና ሲአባብለው ሰነበተ ቅዱስ አባት ቴዎዶስዮስ ከቅዱሳት መጻሕፍት በመጥቀስ ይረታው ነበር። ከእርሱም ጋራ ባልተስማማ ጊዜ ከመንበረ ሢመቱ ወደ ላይኛው ግብጽ አሳደደው። በእርሱም ፈንታ ጳውሎስ የሚባለውን ሰው ሾመው።

ጳውሎስም ወደ እስክንድርያ ከተማ በመጣ ጊዜ ሕዝቡ አልተቀበሉትም ዓመት ሙሉም ኖረ በእጁም ማንም ቊርባንን አልተቀበለም። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ለመናፍቁ ጳውሎስ እስከሚታዘዙ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ አዘዘ። ምእመናንም ከእስክንድርያ በመውጣት ወደ ቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ቆዝሞስና ድምያኖስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዱ ነበር ካህናቱም በዚያ እየቀደሱ ያቆርኳቸው ነበር የአገር ልጆችንም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቋቸው ነበር።

ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲከፍቱላቸው አዘዘ አባ ቴዎዶስዮስም ሰምቶ ንጉሡ እንዳያስታቸው ፈራ ማጽናኛ ቃልን የተመላች መልእክትም ጽፎ በቀናች ሃይማኖት እያበረታቸው ወደ ምእመናን ላካት እንዲህም አላቸው "በዚያ ከሀዲ ጳውሎስ እንዳትታዘዙ ተጠበቁ"።

ይህም አባት ሃያ ስምንት ዓመት በስደት ኖረ። መላው የሹመቱ ዘመን ሠላሳ ሁለት ነበር። ይኸውም በእስክንድርያ አራት ዓመት በስደትም ሃያ ስምንት ዓመት ነው።

ይህም አባት ብዙ ድርሳናትን ደርሷል ምእመናንም በያዕቆብ ዘመን ያዕቆባውያን እንደ ተባሉ በስሙ ቴዎዶስዮሳውያን እየተባሉ ሲጠሩ ኖሩ። መልካም ጉዞውንም ፈጽሞ ሰኔ 28 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 25 ስንክሳር።

+ + +
"ሰላም ለቴዎዶስዮስ ዘተወክፈ ክበዶ። ለሕማም ወለተሰዶ። በቃለ ሃይማኖት እንዘ ይሜህር ውሉዶ። በእንተ ዘገብረ ለክርስቶስ ፈቃዶ። ዐስበ ሐዋርያት ሎቱ ምንተኒ ኢውሕዶ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ 28።

=>#ሰኔ 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አባ ቴዎዶስዮስ ሊቀ ዻዻሳት
2.ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳይ
3.ቅዱስ ባስልዮስ
4.ቅዱስ ባሊዲስ

=>#ወርኀዊ በዓላት
1.አማኑኤል ቸር አምላካችን
2.ቅዱሳን አበው (አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ)
3.ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ
4.ቅድስት ዓመተ ክክርስቶስ
5.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት)

=>+"+ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዓን ናቸው:: መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና:: ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዷችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብጹዓን ናችሁ:: ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ:: ሐሴትም አድርጉ:: ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳደዋቸዋልና:: +"+ (ማቴ. 5:10)

+ + +
#የዕለቱ_ምስባክ፦ "ጸላእኩ ማኅበረ እኩያን። ወኢይነብር ምስለ ጽልሕዋን። ወአሐፅብ በንጹሕ እየውየ"። መዝ 25፥5-6።

#የሚነበቡት_መልዕክታት ቲቶ 1፥7-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥1-7 እና የሐዋ 7፥1-9።

#የሚነበበው_ወንጌል ማቴ 10፥23-32።

#የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችን ይሁንልን።
51 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 07:36:42 ድርሳነ መድኃኔዓለም ወገድለ መብዓጽዮን ዘሰኑይ




@dmkmc
@dmkmc
@dmkmc
53 viewsedited  04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ