@newayekidisat #በሰሙነ_ሕማማት_የሚገኙ_ዕለታትና_ስያሜአቸው ዕለተ ሠሉስ (ማክሰኞ) ይህ ቀን ጌታችን ሰኞ በተናገረውና ባደረገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ዕለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የጥያቄ እና የትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ @newayekidisat ጥያቄውም ጌታ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት ለጸሐፍትና ፈሪሳውያን ይኸውም ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን ‹‹በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?» የሚል ነበር (ማቴ. ፳፩፥፳፫-፳፯)፡፡ ጌታችንም «… እውነት እላችኋለሁ፤ ቀራጮችና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል፤›› ሲል አስተምሯል (ማቴ. ፳፩፥፳፰)፡፡ #forward በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ @newayekidisat @newayekidisat 464 views05:35