Get Mystery Box with random crypto!

@newayekidisat @newayekidisat በሰሙነ ሕማማት የሚገኙ ዕለታትና ስያሜአቸው ዕለ | ንዋየ ቅድሳት

@newayekidisat
@newayekidisat

በሰሙነ ሕማማት የሚገኙ ዕለታትና
ስያሜአቸው

ዕለተ ሰኑይ (ሰኞ)

ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ (የቤተ
መቅደስ መንጻት) እና መርገመ በለስ
የተፈጸመበት ዕለት ነው (ማቴ.፳፩፥፲፰-፳፪፤
ማር. ፲፩፥፲፩፤ ሉቃ. ፲፫፥፲፮)፡፡ ወንጌላዊው
ቅዱስ ሉቃስ፡- ‹‹… ለአንድ ሰው በወይኑ
አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው፡፡ @newayekidisat
ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም
አላገኘም፤›› በማለት በበለስ ስለ ተመሰለው
የሰው ልጅ እና በንስሐ ተመልሶ በሕይወት
መኖር እንደሚገባው እግዚአብሔር ኢየሱስ
ክርስቶስ ማሳሰቡን ያስረዳል፡፡ @newayekidisat በለሷ እንደ
ጠወለገችና እንደ ተቈረጠች ዅሉ፣ ንስሐ
አልገባም አልመለስም የሚሉም የምግባር
ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቈረጡ፤
እንደዚሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ
ቅዱስ በግልጽ ይናገራል፡፡ በለስ የተባለች
ቤተ እስራኤል፤ ፍሬ የተባለ ደግሞ
ሃይማኖትና ምግባር ነው፡፡ ዅላችንም ቤተ
እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት እና ምግባርን
አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ፍሬ
አልባ እንዳንኾን፣ ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር
የመጽሐፉን ቃል መፈጸም ይጠበቅብናል፡፡


#forward በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ
@newayekidisat
@newayekidisat