Get Mystery Box with random crypto!

#US #SOMALIA አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የ | Mereja today news

#US #SOMALIA

አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች።

የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል።

አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን አሳውቃለች።

በጥቃቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ / ሲቪሎች እንዳልተገደሉ ተመላክቷል።