2022-08-15 16:58:48
#የበጎ_አድራጎት_ሥራዎች
#ከመና_የአረጋውያን_እና_የአዕምሮ_ህሙማን_መርጃ_ማዕከል
ሰላም ውድ ቤተሰቦቻችን ዘወትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ የምስራች አካባቢ በሚገኘው በጅሮንድ ደረጃ ስር ሰው ከራባቸው የጎዳና ልጆች ጋር በምናሳልፈው ጊዜ እርሶም በዚህ ልዩ ቀን መጥተው የማይረሳ ጊዜን ከጎዳና ልጆች ጋር ያሳልፉ
#በዕለቱ_የምንሰራቸው_ሥራዎች
➠የገላ ማጠብ
➠ የፀጉር ማስተካከል እንዲሁም የሴቶችን ፀጉር መስራት
➠ከሻወር በኋላ የቁርስ ፕሮግራም
ጥቂት ምክንያት አግኝቶብን ሊሰጠን የሚወደውን እንዳናጣ በቤታችን ያስቀመጥናቸውንና የማንጠቀምባቸውን ነገሮች ማለትም
➠ከቤትዎ የማይፈልጉትን የቤተሰብ አልባሳት
➠ለህፃናት አልባሳት
➠ለህፃናት የፀጉር ቅባት
➠ የውርጭ መከላከያ ቫዝሊን
➠የገላ ሳሙና እና የልብስ ሳሙና
➠ የቅዳሜ ቁርስዎን ቢያንስ አንድ ዳቦ
እነዚህን ስጦታዎች እንሻለን። እንዴት መለገስ እንችላለን ለሚለው ጎንደር ላይ ላላችሁ ማዕከል በመምጣት ወይም እኛ ካሉበት ቦታ ድረስ መጥተን መውሰድ እንችላለን። ከጎንደር ውጭ ላላችሁ እና በየትኛውም ሀገር ያላችሁ ደግ አሳቢ ቤተሰቦቻችን እርቀት ሳይገድባችሁ መርዳት ትችላላችሁ ።
ለተቸገሩ ሰዎች መስጠት ማለት ስጦታችንን በሌላ በማንም ሳይኾን በራሱ በፈጣሪ እጅ ማስቀመጥ ነው፡፡
#ለአንድ_ሰው_ፈገግታ_ምክንያት_ይሁኑ
~
አድራሻ፦ጎንደር ቀበሌ 15 ከቅርጫት ኳስ ሜዳው ጎን
09 34 64 13 09
09 34 64 13 10
የ ኢ.ን. ባንክ አካውንት
1000089064868
@menacharity15
@menacharity
136 viewsAbrham Menna, 13:58