የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና የቀጠለ..... #በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን __ #መንፈሳዊ_አገልግሎት ማንኛውም ስራ አገልግሎት ብለን ልንጠራው እንችላለን ነገር ግን የሚያስገኙት ዋጋ የተለያየ ነው። ለምን ቢሉ፦ ➀ ጠሪው እግዚአብሔር ነው። (ዮሐ 15፥16) ➁ዋጋው ምድራዊ ብቻ ሳይሆን ሰማያዊም ነው። ➂ በስጋዊ ጥበብ የሚሰራ ሳይሆን በመንፈሳዊ እውቀትና በረድኤተ እግዚአብሔር የሚሰራ ነው። መንፈሳዊ አገልግሎት እንደስሙ ረቂቅ በሆነው መንፈሳዊ ሀይልና ጥበብ ተሞልተው የሚያገለግሉት ህይወት ነው። አገልጋዩም መንፈሳዊ አገልጋይ ይባላል። #የመንፈሳዊ_አገልግሎት_መገለጫዎች ሰማያዊ ዋጋ ታስቦ የሚደረግ ነው አገልግሎቱ በመንፈሳዊ ጥበብ የሚከናወን ነው አገልግሎቱ በትህትና የሚደረግ ነው አገልግሎቱ መስዋዕትነት ያለበት ነው አገልግሎቱ በፍቅር የሚከናወን ነው #መንፈሳዊ_አገልግሎት_በ3_ይከፈላል እራስን ማገልገል ህዝብን/ምዕመንን ማገልገል እግዚአብሔርን ማገልገል ናቸው። #የመንፈሳዊ_አገልግሎት_ተግዳሮቶች መባከን ተስፋ መቁረጥ ግዴለሽነት 4️⃣ ቸልተኝነት ጊዜአዊነትና ነገ ሟች መሆንን መርሳት #የመንፈሳዊ_አገልግሎት_ዋጋ ➀ ምድራዊ በረከትን ይሰጣል ➁ ሰማያዊ ወጋን ይሰጣል ➂ ታሪካዊ ህይወትን ያስገኛል በመጨረሻም፦ #የተማሩትን_በተግባር_መኖር፦ እግዚአብሔር የተማርነውን እንድንኖር ቅዱስ ፍቃዱ ይሁንልን!! የእግዚአብሔር ፀጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስ ህብረት፣ የእመቤታችን አማላጅነት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤትና በረከት በሁላችን ላይ ይሁን አሜንንን ~~~~ #ሼር#ጥያቄ ካላችሁ መጠይቅ ትችላላችሁ ቀጣይ ትምህርታችን ነገረ ሐይማኖት~>አዲስ ኮርስ ነው #ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!! @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan ⓯ 681 viewsKingston Ethiopia, edited 07:35