Get Mystery Box with random crypto!

የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና የቀጠለ..... #በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አም | ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

የመጀመሪያ ኮርስ -ነገረ ክርስትና
የቀጠለ.....
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

__
#መንፈሳዊ_አገልግሎት
ማንኛውም ስራ አገልግሎት ብለን ል
ጠራው እንችላለን ነገር ግን የሚያስገኙት ዋጋ የተለያየ ነው።
ለምን ቢሉ፦
➀ ጠሪው እግዚአብሔር ነው። (ዮሐ 15፥16)
➁ዋጋው ምድራዊ ብቻ ሳይሆን ሰማያዊም ነው።
➂ በስጋዊ ጥበብ የሚሰራ ሳይሆን በመንፈሳዊ እውቀትና በረድኤተ እግዚአብሔር የሚሰራ ነው።
መንፈሳዊ አገልግሎት እንደስሙ ረቂቅ በሆነው መንፈሳዊ ሀይልና ጥበብ ተሞልተው የሚያገለግሉት ህይወት ነው። አገልጋዩም መንፈሳዊ አገልጋይ ይባላል።

#የመንፈሳዊ_አገልግሎት_መገለጫዎች
ሰማያዊ ዋጋ ታስቦ የሚደረግ ነው
አገልግሎቱ በመንፈሳዊ ጥበብ የሚከናወን ነው
አገልግሎቱ በትህትና የሚደረግ ነው
አገልግሎቱ መስዋዕትነት ያለበት ነው
አገልግሎቱ በፍቅር የሚከናወን ነው
#መንፈሳዊ_አገልግሎት_በ3_ይከፈላል
እራስን ማገልገል
ህዝብን/ምዕመንን ማገልገል
እግዚአብሔርን ማገልገል ናቸው።

#የመንፈሳዊ_አገልግሎት_ተግዳሮቶች
መባከን
ስፋ መቁረጥ
ግዴለሽነት
4️
⃣ ቸልተኝነት
ጊዜአዊነትና ነገ ሟች መሆንን መርሳት

#የመንፈሳዊ_አገልግሎት_ዋጋ
➀ ምድራዊ በረከትን ይሰጣል
➁ ሰማያዊ ወጋ
ን ይሰጣል
➂ ታሪካዊ ህይወትን ያስገኛል

በመጨረሻም፦
#የተማሩትን_በተግባር_መኖር፦
እግዚአብሔር የተማርነውን እንድንኖር ቅዱስ ፍቃዱ ይሁንልን!!
የእግዚአብሔር ፀጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስ ህብረት፣ የእመቤታችን አማላጅነት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤትና በረከት በሁላችን ላይ ይሁን አሜንንን
~~~~

#ሼር#ጥያቄ ካላችሁ መጠይቅ ትችላላችሁ
ቀጣይ ትምህርታችን
ነገረ ሐይማኖት~>አዲስ ኮርስ ነው
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

@mahiberekidusan
@mahiberekidusan
@mahiberekidusan